Sunday, June 4, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

በሳይንስና በፍልስፍና መነጽር መታየት ያለባቸውና መልስ የሚያስፈልጋቸው የብሔረሰብ የጭቆናና የማንነት ጥያቄዎች

ክፍል ፫

ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ላሴ ከሁለተኛው የኢትዮጵያና የጣሊያን ጦርነት በኋላ ልጣናቸውን እንደገና ሲጨብጡ አንዳንድ የግንባታ ርምጃዎችን ቢወስዱም፣ የተከሏቸው ኢንዱስትሪዎች በሙሉ የማደግና የመስፋፋት ባህአልነበራቸውም፡፡ በዚህም ምክንያት የተነሳ በአገር አቀፍ ደረጃ ሰፋ ያለና የተወሳሰበ የውስጥ ገበያ (Home Market) ሊዳብርና ሊያድግ አልቻለም፡፡

ይህ ሁኔታ በጊዜው ብቅ ማለት የጀመረውን የኅብረተሰብ ኃይል ወደ ነጋዴነት ብቻ እንዲያዘነብል ገፋፋው። በዚህ ላይ በየቦታው የቀለጠፈና ዘመናዊ ቢሮክራሲና ሌሎች ለአገር ግንባታ የሚያገለግሉና ዝቡን ሊያቅፉ የሚችሉ ተቋማት ባለመገንባታቸው በየክፍለ ገሩ ያለው የሰው ጉልበትና የጥሬ ሀብቶችን በማንቀሳሰ  ሰፋ ያለ ዝቡን የሚጠቅም ግንባታ ማካሄድ አልተቻለም፡፡ የየክፍለ ሮቹምዎች የተማሩ ስላልነበሩ በራሳቸው ተነሳሽነት የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን በማውጣትና ትናንሽና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎችን እንዲቋቋሙ በማድረግ ለሰፊው ሕዝብ፣ በተለይም ደግሞ ለወጣቱ የሥራ መስክ መክፈት አልቻሉም። በዚህም ምክንያት የተነሳ በየቦታው በባህል ረገድ ኋላ ቀር ሁኔታ የሚታይበትና ሰፊው ሕዝብም አጋዥ ያልነበረውና በራሱ ኃይል ብቻ ጥሮ ግሮ የሚኖር ነበር። ከአውሮፓ የኅብረተሰብ አገነባብ ታሪክ የምንማረው ነገር ካፒታሊዝም ራሱን እስኪችል ድረስ አብዛኛዎች ነገሮች፣ ማለትም የከተማ ግንባታ፣ የመሠረተ ልማት መስፋፋት፣ የኢንዱስትሪዎች መቋቋምና ድጎማ ማግኘት፣ ልዩ ልዩ ተቋማትና ትምህርት ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች ይስፋፉና ይገነቡ የነበረው በመንግት አማካይነት ነው። በዚህም ረገድ ነው ቀስ በቀስ የገበያ ኢኮኖሚ የሚባለው ነገር ሊያብብ የቻለው። ወደ አገራችን ስንመጣ አገዛዙ የሚመራበትን የኢኮኖሚ ፖሊሲ አለማወቁ ብቻ ሳይሆን፣ በምሁራን ደረጃም ለአገር በሚጠቅም ቲዎሪና ፖሊሲ ነክ ነገር ላይ ምንም ዓይነት ክርክር ስለማይደረግ በአገዛዙ ላይ ጫና ማድረግ አይቻልም ነበር። በመሆኑም ቀስ በቀስ በመንግት ላይ ግፊት ሊያደርግና የፖሊሲ መሻሻል እንዲኖር ትምህርት የሚሰጥ ምሁራዊ እንቅስቃሴ አልነበረም። የምዕራብ አውሮፓን የካፒታሊዝም ዕድገትና የማበራዊ ሁኔታዎችን መሻሻል ስንመለከት ግን ሁሉም ነገር ይፈልቁ የነበረው በምሁራን አማካይነት ነበር። በተለያዩ ቲዎሪዎችና ፖሊሲዎች ዘንድም የጦፈ ክርክር ስለሚደረግ መንግታት በጭፍን አንዱን ፖሊሲ ብቻ ተግባራዊ የሚያደርጉበት ሁኔታ አልነበረም። ወደ አገራችን ስንመጣ ግን በነበረው ምሁራዊ ክፍተትና ውስን የሆነ ፖሊሲ ምክንያት የተነሳ አገዛዙ ሰፋ ብሎ እንዲያስብና አብዛኛውን ሕዝብ የሚጠቅም ብራዊ ፖሊሲ እንዲነድፍና ተግባራዊ እንዲሆን አላስቻለውም፡፡ በዚህም ምክንያት የተነሳ በአገራችን ውስጥ ያልተስተካከለ ዕድገት መስፋፋቱ ብቻ ሳይሆን ያለንን የጥሬ ሀብትና የሰው ኃይል በሚገባ መጠቀም አልተቻለም፡፡

በሌላ ወገን ግን ይህ ዓይነቱ የዕድገት ክፍተት እያለ 1940ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ መታየትና ማደግ የጀመረው በተለያዩ መልኮች የሚገለጸው ባህል ብራዊ ስሜታችንን እንዳዳበረውና የኢትዮጵያዊነትን ስሜት እንዳደመቀው ለማንኛችንም ግልጽ ነው። ጣሊያን ድል ከተመታና ከተባረረ በኋላ ነው በተለይም የተለያዩ ሙዚቃዎች ሊዳብሩና ዝቡን ሊያስተሳስሩት የቻሉት፡፡ የእነ ጥላሁን ገሠሠ፣ መሙድ አህመድና ብዙነሽ በቀለ ወዘተ. የመሳሰሉት ዘፋኞች የዘመናዊነት ውጤቶች ናቸው ማለት ይቻላል። የአገር ባህል ሙዚቃም ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነው መዳበርና አገርን ማዳረስ የቻለው። በ ፍ ደረጃም አያሌ ባይባልም ትችታዊ አመለካከት ያላቸው መጽፎች በመታተምና በመራባት ለንቃተ ህሊና መዳበር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ ችለዋል። የቴአትር ሥራዎችም በመዳበርና በመታየት እስከተወሰነ ደረጃ ድረስ የተወሰነውን የኅብረተሰብ ክፍል ጭንቅላት ማደስ ችለዋል። እነዚህና ሌሎች ባህላዊ ነክ ፈጠራዎች፣ እንደ ምግብ የመሳሰሉት በመስፋፋትና አብዛኛው ሕዝብ እንዲመገበው ማድረግ ቀስ በቀስ ብራዊ ሥነ ምግባር እንዲዳብርና በመንፈስ እንድንያያዝ ሊያደርጉን በቅተዋል። ይሁንና ግን በኢኮኖሚው የውስጠ ኃይል ደካማነት የተነሳ በአገሪቱ ውስጥ አጠቃላይ የሆነ የባህል ዕምርታ ሊታይ አልቻለም። እዚያው በዚያው ይንን ዓይነቱን ብራዊ ባህል የሚቀናቀኑ ነገሮች በመፈጠራቸው ሰፋ ያለ ማኅበራዊ ቅራኔም ይታይ እንደነበር ግልጽ ነው። 

ባጭሩ በጊዜው የታየው ኋላ ቀርነት 90 ከመቶ በላይ የሚቆጠረውን ሕዝብ የሚመለከት ነበር። አገዛዙ ከአማራ ብሔረሰብ የተውጣጣ ስለነበር ለአንድ ብሔረሰብ ያደላል የሚለው ተራ ቅት እንጂ ተጨባጩን ሁኔታ የሚያንፀባርቅ አልነበረም። እንዲያውም ኋላ ቀር የሚባለው ክፍል አብዛኛው የአማራው ግዛት ነበር። በዚህም ምክንያት ነው በወሎና በሰሜኑ አንዳንድ ቦታዎች በተደጋጋሚ ረሃብ ይከሰት የነበረው። በችግር ይሰቃይ የነበረው ጎንደሬው፣ ጎጃሜውም ሆነ የወሎ ሰው ሥራ ለመፈለግ ወደ ደቡቡ ክፍለ አገሮች ነበር የሚያቀናው። ይህ ዓይነቱ የጊዜውን ሁኔታ ያላገናዘበና፣ በተለይም ደግሞ ካፒታሊዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲስፋፋ የሚያመጣውን ያልተስተካከለ ዕድገት ሳያጤኑ የትግሬና ዛሬ ኦሮሚያ ተብሎ የሚጠራው በዕድገት ወደ ኋላ የቀረና ጭቆና የሰፈነበት ነበር ብሎ ማራገብ ከውነተኛው ሁኔታ የራቀ ነበር። አፄ ኃይለ ላሴና አገዛዛቸው ለአማራው
ሞክራት ሆነው ለሌላው ደግሞ ኢሞክራሲያዊ አገዛዝ ሊያራምዱ የሚችሉ አልነበሩም ባህያቸውም አይፈቅድም ነበር። በሌላ አነጋገር የሞክራሲና የነፃነት ጦት፣ ጭቆናና ኋላ ቀርነት ጠቅላላውን ሕዝብና ሁሉንም ክፍለ ገሮች የሚመለከት ነበር። ስለሆነም ነው የየካቲቱ አብዮት የፈነዳውና የመሬት ለአራሹም እስከተወሰነ ደረጃ ድረስ ተግባራዊ ሊሆን የበቃው። በጊዜው አሥራ ስምንት ወራት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ነው በጠቃላይ ሲታይ አገሪቱን በማዳረስ ከፍተኛ የሆነ ብራዊ ባህ ያለው ሥራ የተራውና፣ ሕዝብን ማደራጀትና መብቱንም አውቆ አዲስ የአራርና የአደረጃጀት ሥልት እንዲማር ከፍተኛ ትግል የተደረገው።  በጊዜው ዝቡም በጎሳው ሳይሆን እንደ አንድ ሕዝብ በመነሳት ነው አዲሲቱ ኢትዮጵያን ለመገንባት ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈለው። ይሁንና ግን ይህንን የማይፈልጉ የውስጥና የውጭ ኃይሎች አንድ ላይ በመጣመር በዝባችንና በአብዮቱ ላይ ዘመቻ ከፈቱባቸው። ጉግ ማንጉግን ከኢትዮጵያ ውስጥ ማስወገድ ያስፈልጋል በሚለው ቅስቀሳ የተወናበደው መሳፍንት፣ የሚሊታሪና የሲቪል ብሮክራት፣ እንዲሁም የነፃ አው ድርጅቶች ነን የሚሉና ራሱም የማርክሲዝምን ሌኒንዝም ርማ አንግቤያለሁ የሚለው በአንድነት በመነሳትና ከአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝም ድጋፍ በማግኘት አጠቃላይ ጦርነት አወጁ። በዚህ የተወናበደውና ከሥር በሲአይኤ ይገዘገዝ የነበረው የወታደራዊ አገዛዝ ራሱም ጦርነት በማወጅ በብዙ ሺች የሚቆጠሩ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን አለቁ። ይህ የእርስ በእርስ መተላለቅ ለወያኔና ለሻቢያ የፖለቲካ ክፍተት ፈጠረላቸው። ሥልጣን እንዲጨብጡና ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለአገራችን የመቶ ዓመት የቤት ሥራ መስጠት ቻሉ።  በዚህ ድርጊታቸው የብልጣ ብልጥ ሥራ የሩ መሰሏቸው ነበር። ያልገባቸው ነገር ቢኖር ለራሳቸውም ነው ጉድጓድ የቆፈሩትና ዛሬ ዝባቸውን ወደ ከፍተኛ ችግር ውስጥ የከተቱት። አንዳንድ የኦሮሞ ኤሊትም ይህንን ዓይነቱን ድርጊት እየደገመና ድንቁርናውን እያስመሰከረ ነው። እነዚህ ሁሉ ያልገባቸው ነገር ቢኖር የሚያካሄዱት ኢሳይንሳዊ ቅስቀሳና የናሽናሊዝምን ስሜት ማራገብ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው ጥቁር ሕዝብ ላይም ነው ጦርነት ያወጁት። ተግባራቸውም ቆሜለታለሁ የሚሉትን ቸውን የሚጠቅም ሳይሆን የረብ አገሮችንና የኢምፔሪያሊስት ኃይሎችን ነው። በዚህ ድርጊታቸውም የሥልጣኔና የዕድገት ህልማችን እንዳለ ይወድማል። ጠቅላላው ዝባችን ወደ ዲንጋይ ዘመን እንዲወረወር ይደረጋል። በኢትዮጵያ ምድር ውስጥ የእርስ በእርስ ጦርነት ቢከሰት አገራችንና ዝባችን ብቻ ሳይሆኑ የሚጠቁት የአካባቢው አገሮችም በከፍተኛ ደረጃ ይጎዳሉ። አገራችንም የግብ፣ የሱዳን፣ የረብ አገሮችና የስለላ ድርጅቶች መጫወቻ ትሆናለች። ታሪኳና ባህሏ ይወድማሉ። ይንን ዓይነቱን አሉታዊ ውጤት ነው ወያኔዎችና ዛሬ ጊዜው የእኔ ነው ብሎ እዚህና እዚያ የሚራወጠው አንዳንድ የኦሮሞ ኤሊት ግልጽ ሊሆንለት ያልቻለው።

በዚህ ዓይነቱ የታሪክ ወንጀል ሳይንሳዊና ፍልፍናዊ ባህ ሳይኖረው ዝም ብለው የኢትዮጵያዊነትን ስሜት የሚያራግቡ ኃይሎችም ተጠያቂዎች ናቸው። አብዮቱ ሊከሽፍ የቻለውና አገራችንም እዚህ ዓይነቱ ደረጃ ላይ ልትደርስ የበቃችው ለአሜሪካ ባደሩና ለሱ በሚሩ ኢትዮጵያውያን ኃይሎች ነው። እነዚህ ናቸው ከውስጥ ሆነው አገዛዙን በመገዝገዝ አገራችንን ራቁቷን ያስቀሯት። እነዚህ የድሮ የራዊቱ አባላትና አሁንም ለአሜሪካ የሚሩ አንዳንድ ግሰቦች ወጣቱንና ሰፊውን ሕዝብ በማወናበድ በሌላ መልክ ደግሞ ፀረ ኢትዮጵያ ድርጊታቸውን እያጧጧፉት ይገኛሉ። እነዚህ ብቻ ሳይሆኑ ከኢትዮጵያዊነት ይልቅ አሜሪካዊነትን የሚያስቀድሙ በአርባዎቹና በሃምሳዎቹ መታት ዕድሜ የሚገኙ የፖለቲካ መድረኩን በማጣበብ ኢሳይንሳዊና ፍልስፍና አልባ ቅስቀሳ በማድረግ ሕዝብን ግራ እያጋቡ ነው። በአጭሩ በፍልስና ላይ የተመረኮዘና ሳይንሳዊ መሠረት ያለው ትግል ስለማይካሄድ ሁሉም በተወሰኑ መፈክሮች ላይ በመሰባሰብ በተለይም ወጣቱን እያሳሳተው ነው። ይንን ዓይነቱን ውዥንብርና ለሥልጣን ላይ ለመውጣት የሚደረግ እሽቅድምድሞሽን መልስ ለማሲያዝና ጥራት ያለው ትግል ለማካሄድ በጣም አስቸጋሪ ነው። ማንም የሚማም ያለ አይመስለኝም። ሁሉም የመረጠው ዝም ብሎ መደናገርን እንጂ ጥራት ያለውንና ተከታታይ ትግልን ማካሄድ አይደለም። ጥያቄው ከእንደዚህ ዓይነቱ የተዘበራረቀና የተወናበደ ሁኔታ እንዴት መውጣት ይቻላል?  የሚለው ነው። ከሁሉም በላይ ከላይ የዘረዘርኩትን በብሔረሰብ አኳያ የሚካሄደውን፣ ከሳይንስና ከፍልስፍና ውጭ የሚደረገውን ትግልና ቅስቀሳ እንዴት መግታት ይቻላል? የሚለው ነው አስቸጋሪው ጉዳይ። በእኔ ምነት የተገለለት ኃይል እስከሌለ ድረስ የአገራችን ጉዳይ እጅግ አስቸጋሪ ይሆናል። ስለዚህ ይህንን ሁኔታ ሊያስቀለብስ የሚያስችል ስትራቴጅ መቀየስ የሚያስፈልግ ይመስለኛል።

የብሔረሰብ ወይም የጎሳ፣ የማንነት ጥያቄና የዋና ከተማ ጉዳይ

በመረቱ ብሔረሰብ ወይም ደግሞ ጎሳ ሳይንሳዊ መሠረት የለውም። ጽን ሳቦቹ ሊገለጹ የሚችሉ አንድ በጣም ውስን የሆነ ተገልሎና በሥራ ክፍፍል ያልተደራጀ ከሆነና በጣም በጠባብ አካባቢ የሚኖር የሰው ስብስብ ከሆነ ምናልባት ጎሳ ወይም ብሔረሰብ ብሎ መጥራ ይቻል ይሆናል። በሶሻል ሳይንስ እንደዚህ ዓይነቱ በባህል፣ በሥራ ክፍፍልና በሌሎች እንደ ዕል በመሳሰሉት. . .  ወዘተ. የማይገለጽ የሰው ልጅ ያልተነጣጠለ (Undifferentiated) ተብሎ ይጠራል። እንደዚህ ዓይነቱ የሰው ልጅ ደግሞ በአሁኑ የግሎባል ካፒታሊዝም ዘመን በተወሰኑ፣ እንደ ካሜሩን በመሳሰሉ ጫካዎች ውስጥ የሚኖሩ ፒግሚዎች ተብለው በመጠራት የሚታወቁና በፓፕዋ ኖይጊዩኒዋ (Papua Neuguinea) ውስጥ ከዘመኑ ሥልጣኔ ተነጥለው ለሚኖሩ መጠሪያ ሆኖ ሊያገለግል ይችል ይሆናል። ወደ አገራችን ስንመጣ ግን ይህ ዓይነቱን ተነጥሎና በጋብቻ ሳይተሳሰሩና ሳይዋለዱ የሚኖሩ ፈልጎ ማግኘት በጣም አስቸጋሪ ነው። ይህም ማለት በአገራችን የታሪክ ሒደትና በኅብረተሰብ ግንባታ ውስጥ መሰበጣጠሮች፣ መዘዋወሮችና፣ ከአንደኛው ጎሳ መጣ የሚባለው፣ በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ በግለሰብም ሆነ በጥቅል የተወለደበትንና ያደገበትን አካባቢ ጥሎ የሄደው ሌላ ቦታ ሄዶ አዲስ ኑሮ ሲመርት በሥራ ወይም በንግድ አማካይነት ግንኙነት ይፈጥራል ይጋባል ይዋለዳልም ይራባልም። በዚህ ምክንያት የተነሳና በአንድ አገር ውስጥ ቀስ በቀስ እያለ በሚዳብረው የሥራ ክፍፍልና ንግድ፣ እንዲህም የከተማ ግንባታና የንግድ እንቅስቃሴ አማካይነት የተነሳ አዲስ ኅብረተሰብዓዊ ግንኙነት (Social Relationship) ይፈጠራል ማለት ነው። አንደኛው አንጥረኛ፣ ሌላው ነጋዴ፣ የተወሰነው ደግሞ የፋብሪካ ሠራተኛ፣ እንዲሁ ደግሞ ሌላው የቢሮ ሠራተኛና ቢሮክራት በመሆንና፣ እንዲሁም በሌላ ሙያ በመልጠን ከድሮው ባህላዊ ከሚባለው አስተሳሰብ እየተላቀቀ በመምጣት አዲስ ዓይነት የፍጆታ አጠቃቀምና አነጋገርም ይለምዳል ማለት ነው፡፡ ልቦናውም ይቀየራል ማለት ነው። በዚህ መሠረት በአንድ አገር ውስጥ በገቢ ወይም በመደብ (Income or Social Classes) የሚገለጽ የኅብረተሰብ ክፍል በመጠር ድሮ በጎሳ መልክ ይታይ የነበረው ግለሰብም ሆነ በጥቅል የሚጠራው እየሟሟ ይሄዳል። የለም በብሔረሰብ ብቻ የሚገለጽ ሰው ነው ያለው የሚባል ከሆነ ደግሞ እንደዚህ ዓይነቱ ግለሰብም ሆነ በጥቅል የሚጠራ ውስጣዊ ኃይል የለውም ማለት ነው። የማሰብ፣ የመፍጠር፣ መሪያዎችን የመሥራትና በንግድ አማካይነት የሚገለጽ ተግባርም ሊያዳር አይችልም ማለት ነው።

ወደ ተጨባጩ የአገራችን ሁኔታ ስንመጣ ከትግራይ በስተቀር ሌሎች ዛሬም መጠሪያችን ይኛው ወይም ያኛው ብሔረሰብ ነው ብሎ ራሳቸውን የሚገልጹ ከሌላው ሳይጋቡ አልኖሩም ማለት ይችላል። በተለይም ከ15ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የክርስትና ሃይማኖት ወደ ደቡ ክፍል ሲስፋፋ ደብተራዎችና ቄሶች ለአስተማሪነት በመሄድና እዚያው በመኖር ከሌላው ጋር ተጋብተዋል፣ ተዋልደዋልም። እንደዚህም ግራኝ አህመድ ባደረሰው ልቂት የተነሳ ከፍተኛ ክፍተት ስለተፈጠረ ኦሮሞዎች ከአንድ ቦታ በመነሳት ተስፋፍተዋል። በአንዳንድ ቦታዎች የነበሩ ሥልጣኔዎችንና ነገታትን በመደምሰስ ብዙ ቦታዎችን በቁጥጥራቸው ሥር አውለዋል። ከተቀረውም ሰው ጋር በመጋባት ተዋልደዋል። ይህም ማለት ዛሬ የኦሮሞ ኤሊት ነኝ ብሎ ችግር የሚፈጥረው በሙሉ ከዚህ ወይም ከዚያኛው ብሔረሰብ ጋር ሳይጋባና ሳይዋለድ በንህ መልኩ የሚገኝ አይደለም። ዛሬ የፖለቲካውን ሜዳ የሚቆጣጠሩትና ያዙኝ ልቀቁኝ የሚሉት ሁሉ በአባታቸው  ወይም  በእናታቸው ከአማራ ወይም ከሌላው ብሔረሰብ የሚወለዱ ናቸው። ይሁንና ግን ድርቅ በማለትና የጭቆናንና የመበደልን ርማ በማንገብ የኦሮሞ ብሔረሰብ ተሸማቆ እንዲኖር ተደርጓል ተጨቁኗል በቋንቋውም እንዳይናገር ተከልክሎ ነበር ይሉናል። በዚህም መልክ የተረት ተረት በማውራት የፖለቲካ ቴአትር በመሥራት ከሳይንስና ከቴክኖሎጂ፣ እንዲሁም ለሰው ልጅ ዕድገት ከሚጠቀሙ ከባህላዊ ነገሮች እንድንቅና ለኅብረተሰብ ዕድገት በማይጠቅሙ ነገሮች ላይ ብቻ እንዳንረባረብ እያስገደዱን ነው። ዋና ዓላማቸው ጠቅላላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በእንደዚህ ዓይነቱ ሳይንሳዊ መሠረት በሌለው ነገር ላይ በመጠመድ ደንቁሮ እንዲኖር ለማድረግ ያሰቡ ይመስላል። ተልኮአቸውም የአንድ የውጭ ኃይልን ዓላማ ለማሳካት ይመስላል። አገርን መበታተንና ጥሬ ሀብትን ማዘረፍ። ተጨቁነናል የሚሉ ከሆነ ደግሞ እንዴት ማማር እንደቻሉና ወደ አውሮፓና ወደ አሜሪካ በመምጣት የተንደላቀቀ ኑሮ እንደሚኖሩ ሊያስረዱን በፍም አይችሉም።

ለማንኛውም ካለን ማረጋገጫ ቀደም ብለው የነበሩና አሁንም በይወት የሚኖሩ አንዳንድ የኦሮሞ ብሔረሰብ አቀንቃኞች ሃዘል ብላት ከሚባል ለጀርመን የስለላ ድርጅት ይራ ከነበረና የኢትዮጵያ ጠላት ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንደነበራቸውና በእሱም እንደሚበወዙ የተረጋገጠ ጉዳይ ነው። ሰውው ከሞተም በኋላ ኢትዮጵያን ለመበታተን የሚሩና ከአንድ ከሰሜን ጀርመን፣ ኸርማንስቡርግ ከሚባል ከተማ ካለ የፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያን ማንኛውንም ዕርዳታ እንደሚያገኙ የታወቀ ጉዳይ ነው። ቄሶቹም በየጊዜው ወደ ኢትዮጵያ ይመላለሳሉ። በተለይም ባለፉት 27 መታት ወያኔ ያመቸቻቸውን ሁኔታ በመጠቀም የኦሮሞን ናሺናሊዝም ሊያግሉት ወይም ሊያሞቁት ችለዋል።  በአጭሩ ታሪኩ እንደዚህ ሲሆን፣ የእነዚህ ኤሊቶች ዓላማ ቆመንለታል ለሚሉት ብረሰባቸው ሥልጣኔ ማምጣት ሳይሆን የአበባና የቡና ተካይ፣ እንዲሁም ለጀርመንና ለተቀረው የአውሮፓ ገበያ ልዩ ልዩ ፍራፍሬዎችን ተካይና ባርያ አድርጎ ለማስቀረት ነው ዋናው ዓላማቸው። ዓላማቸው ከዚህ ውጭ አይደለም ሊሆንም አይችልም።

ወደ ማንነት ጥያቄም ስንመጣ በጣም አስቸጋሪና ግልጽ ያልሆነ ጉዳይ አለ። ማንነት በምንድነው የምጸው? ዘለዓለማዊ ወይስ ጊዜያዊ ነው? በቋንቋ፣ በባህል፣ በ ልቦና፣ በምግብ፣ በአለባበስ ወይስ በሌላ ነገር የሚገለጽ? ንን ጉዳይ በቀላሉ ለማስረዳት ያስቸግራል። የማንነትን ወይም የአይደንቲቲን ጥያቄ የሚያነሱ በተለይም የፋሺም ወይም የቀኝ ዝንባሌ ያላቸው ሰዎች ናቸው። እነዚህ ይነቶች በጀርመን፣ በፈረንሣይና እንዲሁም በአንዳንድ የአውሮፓ አገሮች እያደጉ የመጡና በተለይም ጥቁርን የሚጠሉ ናቸው። ዘራችን ንህ ስለሆነና የማሰብ ኃይላችንም ከሌላው የተሻለ ነው ብለው ስለሚያምኑ ከሌላው ጋር በመጋባት ዘራችን መበላሸት የለበትም በማለት ቅስቀሳ ያደርጋሉ በአንዳንድ ቦታዎች ሰው ይደበድባሉ ወይም ይገድላሉ። ከዚህ ስንነሳ በአገራችን ምድር የማንነትን ጥያቄ የሚያነሱ በመረቱ ከእነዚህ ናዚዎች የሚለዩበት ነገር የለም። በሌላ ወገን ደግሞ የማንነትን ጥያቄ የሚያነሱ ከሆነ እነሱ ያልፈጠሯቸውን ነገሮች በሙሉ መጠቀም፣ መብላትና መጠጣት የለባቸውም። ይህን የሚያደርጉ ከሆነ ደግሞ ማንነታቸውን ረተዋል ማለት ነው።  ብዙም ሳያስቡ፣ ሳያወጡና ሳያወርዱ የሚናገሯቸው ነገሮች በሙሉ ችግር ከመፍጠር በስተቀር ለመፍት የሚያገለግሉ አይደሉም። ስለዚህ በሳይንስ ከማይደገፍ አስተሳሰብ መላቀቅ አለባቸው። በመረቱ የፖለቲካ ዓላማ አለኝ የሚል ግለሰብም ሆነ ድርጅት ከሳይንስ፣ ከቲዎሪና ከፍልስፍና ውጭ ማሰብ የለበትም፡፡ ይህንን በግለሰብ ደረጃ ሊያደርግ ወይም ከጓደኛው ጋር በመሆን ሊያወራ ይችላል፡፡  በሌላ ወገን ግን እንደ መቀስቀሻና ማስተማሪያ መሪያ እጠቀማለሁ የሚል ሆነ መቀጣትና መከልከል ያለበት ነው። ስለሆነም ማንኛውም በብሔረሰብ የተደራጀ የፖለቲካ ዓላማ አለኝ የሚል የግዴታ መከልከል አለበት፡፡ በመረቱ በብሔር ደረጃ የተደራጀ ሞክራት ሊሆን በፍም አይችልም፡፡ ሳይንስን ሊያዳብር አይችልም የማኅበራዊ ጥያቄዎችንም ሊያነሳና እንደ መታገያ ሊያደርግ አይችልም። በአጭሩ በብሔረሰብ የተደራጀ ኃይል የሥልጣኔ ጠንቅ ነው፡፡ የአንድ አገር ሕዝብ እንዳይሰባሰብና በጋራ ታሪክ እንዳይራ የሚያግድ ነው፡፡ የተፈጥሮንና የኅብረተሰብን ሕግ የሚፃረር ነው፡፡ 

ወደ ዋና ከተማ ስንመጣ፣ በመረቱ ይህ ነገር ማወዛገብ የለበትም ጉዳዩም ለውይይት መቅረብ ያለበት አይደለም፡፡  በመጀመያ ደረጃ በአንድ ብሔረሰብ ውስጥ መንደር ካልሆነ በስተቀር ብዙ ነገሮችን ሊያሟላ የሚችል ከተማ ሊመሠረት አይችልም፡፡ በሁለተኛ  ደረጃ፣ የከተማ ዕድገት እንደ ኅብረተሰብም ታሪካዊ ደት አለው፡፡ በመሆኑም ከተማዎች ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ ሰዎች የሚገነቡትና ልዩ ዕምርታን (Melting Points) የሚሰጡት የታሪክ ውጤት ነው፡፡ የከተማዎችን ዕድገት ስንመለከት በተደራጁ ገዎች የሚመረቱና በሒደት እያደጉ የሚመጡና የአንድ ብሔረሰብ መለያ ሆነው ሊቀሩ የሚችሉ አይደሉም፡፡ ከተማን ከተማ የሚያሰኘው ከተለያየ ቦታ የሚመጡ ሰዎች መጥተው ሲከትሙና የራሳቸውን የባህል ማተም ሲያደርጉበት ነው፡፡ በዚህም የተነሳ እንደየ ሁኔታውና እንደ አገዛዞች የማሰብ ኃይል የተነሳ ልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ኃይሎች የራሳቸውን የውስጥ ኃይል በማዳበር ከተማዎችን የፈጠራና የልዩ ልዩ ባህል መገናኛዎች ያደርጋሉ፡፡ ከዚህ ስንነሳ አዲስ አበባን የአንድ ብሔረሰብ መኖሪያ ለማድረግ የሚሞከረው ሙራ ወይም በዲሞግራፊ የዝቡን ቁጥር ለመቀየር የሚደረገው ሽር ጉድና አሻጥር የአጭር ጉዞ አመለካከት ነው፡፡ አንድን ሕዝብና የከተማን ዕድገትን ማቀጨጭ ነው፡፡ የሚገርመው ጉዳይ የውጭ ኩባንያዎች ወደ አዲስ አበባ በመምጣትና መሬት በመከራየት አፓርትመንቶች በመሥራት ቅርምት ውስጥ ገብተዋል፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ ነዋሪው ሕዝብ እንዲገፋ በመደረግ ላይ ነው፡፡ በአገራችን ምድር ዘረኝነት እየተካሄደ ነው ማለት ይቻላል፡፡   

መደምደሚያ

ከላይ ከሞላ ጎደል ለማሳየት እንደሞከርኩት አንድን አገርና ኅብረተሰብ ለመመረት ብዙ ውጣ ውረዶችን መጓዝ እንደሚያስፈልግ ነው፡፡ በተለይም ደግሞ በኅብረተሰብና በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ንቃተ ህሊና ወይም ራስን በራስ ማግኘት ከፍተኛውን ሚና ይጫወታሉ፡፡ ከጭንቅላታችን ውጭ የምናደርገው ነገር የለም፡፡ የሰው ልጅ ዕድገት ከታቻ ወደ ላይ ቀስ በቀስ የሚጓዝ ሲሆን አብዛኛውን ዜ በደመ ነፍስ የሚደረግ ሒደት ነው፡፡ የሰው ልጅ እንደ ጦጣ ዛፍ ላይ ከመንጠልጠል አልፍፎ አዳኝ ሆኖና አራሽ እስኪሆንና በሥራ ክፍፍልም እስኪያልፍ ድረስ ብዙ ውጣ ውረዶችን አሳልፏል፡፡ ከፍልስፍና ጋር የኋላ ኋላ ደግሞ ከተፈጥሮ ሳይንስና ከሌሎች ዕውቀቶች ጋር የተለማመዱና ጥልቅ ምርምር ማድረግ የጀመሩ ጭንቅላታቸውን ሰብሰብ አድርገው አንድን ማኅበረሰብ ሲመርቱ፣ እንደኛ ያለው አገር ደግሞ እስከተወሰነ ደረጃም ድረስ ታሪክ ቢኖረው በውስጣዊ ድክመት የተነሳ ከዝቅተኛው ወደ ከፍተኛው ደረጃ መሸጋገር አልቻለም፡፡ የፖለቲካ ሥልትን በማዳበርና ከውጭ የሚመጣውን በብዙ መልክ የሚገለጸውን አሳሳች ዘዴ መክቶ ለመመልስ ባለመቻል ከውስጥ በተታላይ ኃይሎች በመፈልፈል ለብራዊ ነፃነትና እንዲያም ሲል ለኢኮኖሚ ዕድገት ጠንቅ መሆን ተቻለ፡፡ የዚህ ዓይነቱ ክፍተት ለጥራዝ ነጠቅ ኤሊቶች አመቺ ሁኔታ ፈጠረላቸው፡፡

በኅብረተሰብ ግንባታ ውስጥ እንደተረጋገጠው ለጠንካራ ኢኮኖሚ፣ በተለይም ለሳይንስና ለቴክኖሎጂ አትኩሮ የማይሰጥ አገዛዝና ምሁር የመጨረሻ መጨረሻ አገሩን ያስበላል፡፡ ይህ አንደኛው ሲን፣ በመሰበጣጠርና በመበታተን የሳይንስና የቴክኖሎጂ ባለቤት መሆን አይቻልም፡፡ የአንድ ሕዝብም በተለያየ መልክ የሚገለጽ ችግር በሳይንስና በቴክኖሎጂ አማካይነት ብቻ ነው ሊፈታ የሚችለው፡፡ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ደግሞ በአገር ደረጃ ነው የሚዳብሩት እንጂ በክልል ደረጃ አይደደለም፡፡ ምክንያቱም ማንኛውም ብሔረሰብ በክልል ደረጃ የሚወሰንና አትድረሱብኝ የሚል ከሆነ የማደግና የመበልግ ኃይሉ እጅግ ዝቅተኛ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ወደ ንጋ ዘመን እንመለስ ካልተባለ በስተቀር አቃላይ ዕድገት ሊመጣ የሚችለው በአገር አቀፍ ደረጃ ብቻ ነው፡፡ሳብ መንሸራሸር ሲኖር፣ የሰው ኃይልና ካፒታል እንዲሁም ዕቃዎች ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መሽከርከር ሲችሉ ብቻ ነው አንድ ክልልም ሆነ አንድ አገር ሊያድግ የሚችለው፡፡ ስለሆነም እያንዳንዱ ጭንቅላቱ ውስጥ ከተከለው አጉል ጥላቻና ተንኮል፣ እንደዚሁም ቂም በቀል እስካልተላቀቀ ድረስ በማንኛውም ክልልም ሆነ በአገር ደረጃ በፍም ዕድገት ሊኖር አይችልም፡፡ ከዚህ ስንነሳ ምርጫችን ሁለት ነው፡፡ ይ ሥልጣኔ፣ አሊያም የንጋይ ወይም ደግሞ የኋላ ቀርነቱን ዘመን መምረጥ። መልካም ግንዛቤ!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው  [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_imgspot_img
- Advertisment -

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

Related Articles