Saturday, April 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትበፈረንሣይ በሙስና ተጠርጥረው የተያዙት የካፍ ፕሬዚዳንት ተለቀቁ

በፈረንሣይ በሙስና ተጠርጥረው የተያዙት የካፍ ፕሬዚዳንት ተለቀቁ

ቀን:

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) ፕሬዚዳንት አህመድ አህመድ፣ የዓለም እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ማኅበር (ፊፋ) በፈረንሣይ በሚያካሂደው ጉባዔ ለመታደም ባቀኑበት ወቅት፣ የፈረንሣይ ፖሊስ ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዘ ለምርመራ ቢያስራቸውም ባለፈው ዓርብ ግንቦት 30 ቀን 2011 ዓ.ም. ክስ ሳይመሠረትባቸው መለቀቃቸው ተሰምቷል፡፡ 

ይህም ሆኖ ፕሬዚዳንቱ በሙስና ወንጀል ያስጠረጠራቸው፣ ከጀርመኑ የስፖርት ትጥቅ አምራች ፑማ ኩባንያ የጨረታ ውጤት ጋር በተያያዘ የቀረበባቸው ቅሬታ እንደሆነ ታውቋል፡፡ ፑማን ጨምሮ ሌሎችም ትጥቅ አምራቾች በተወዳደሩበት ጨረታ፣ 830 ሺሕ ዶላር መደለያ በመቀበል የፑማን የጨረታ ውጤት ውድቅ አድርገዋል፡፡ ለተቀናቃኙ ቴክኒካል ስቲል ኩባንያ ጨረታውን አሳልፈው ሰጥተዋል የሚል ክስ ሲቀርብባቸው ቆይተዋል፡፡ ፕሬዚዳንት አህመድ ይህንን ውንጀላ ሲያስተባብሉ ቢቆዩም በ69ኛው የፊፋ ጉባዔ ለመታደም ወደ ፈረንሣይ ባቀኑበት ወቅት ነበር በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው በነፃ መለቀቃቸው የታወቀው፡፡

‹‹ውሳኔዎች በሙሉ በጋራና ግልጽነት በሰፈነበት አግባብ ነው የተወሰኑት፤›› በማለት የቀረበባቸውን ውንጀላ አስተባብለዋል፡፡ ፊፋም ራሱን እንዲህ ካሉ የወንጀል ተግባራት ማፅዳቱን በማስታወቅ የሚስተር አህመድን መታሰር በማስመልከት ዝርዝር መረጃ እንዲሰጡት የፈረንሣይ መርማሪዎችን ጠይቆ ነበር፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...