Saturday, June 10, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
በሕግ አምላክየፌዴራል ፍርድ ቤቶችን ‹‹አውቶሜት›› ማድረግ ፍትሕን ተደራሽ ከማድረግ አንፃር ያለው አንድምታ

የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን ‹‹አውቶሜት›› ማድረግ ፍትሕን ተደራሽ ከማድረግ አንፃር ያለው አንድምታ

ቀን:

በብስራት ተክሉ

የሕግ የበላይነትን ለማስጠበቅ ከሚያስፈልጉ ነገሮች መካከል አንደኛው ርድ ቤቶችን በሚገባ ማጎልበት ነው፡፡ ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ርድ ቤቶች ሕግ ሕይወት አግኝቶ የሚተረጎምባቸውና ፍትሕን የሚሹ ፍትሕን የሚያገኙባቸው ተቋማት መሆናቸው ነው፡፡ የዜጎችን የዕለት ተለትንቅስቃሴ ተከትሎ መብታቸውን ሊነካ የሚችለውን አስፈጻሚውን አካል በዋናነት የሚቆጣጠሩትም ቢሆኑ ርድ ቤቶች ናቸው፡፡

ርድ ቤቶች የዜጎችን ፍትሕ የማግኘት መብት አስጠብቀዋል ሊባል የሚችለው ነፃና ገለልተኛ ሆነው ጥራቱን የተጠበቀ ውሳኔ በአጭር ጊዜ መስጠት ሲችሉ ነው፡፡ ይህ ካልተፈጸመ ፍትሕንደተነፈገ ይቆጠራል፡፡ንግሊዛዊው የመንግሥትላፊ ሰር ዊልያምንደገለጸው ‹‹የዘገየ ፍትሕንደተነፈገ ይቆጠራል››፡፡

ርድ ቤቶች ነፃና ገለልተኛ ሆነው ጥራቱን የጠበቀ ውሳኔ በአጭር ጊዜንዲሰጡ ካስፈለገ የፍርድ ቤቶችን አቅም በሰውይልና በቴክኖሎጂ ማጎልበት የግድ ነው፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ርድ ቤቶችን በቴክኖሎጂ መደገፍ በምን መልኩ ሊሆን ይገባዋል? የሚለውን የሚዳስስ ይሆናል፡፡ ይኸውም በተለየ ዳኞችና የፍርድ ቤት የድጋፍ ሠራተኞች ዘመኑ በደረሰበት የአውቶሜሽን ቴክኖሎጂ በምን መልኩ ሊገዙ ይገባል? የሚለውን ይዳስሳል፡፡ ለዚህም ጽሑፉ የተዘጋጀው በተለያዩ አገሮች የተተገበሩ የፍርድ ቤት አውቶሜሽን ሥራዎ­ ያሳኳቸውን ግቦች መሠረት አድርጎ ነው፡፡

በእርግጥም ርድ ቤቶቻችንን አውቶሜት በማድረግ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በፍርድ ቤት የዕለት ተለት ሥራ ላይ ሙሉ በሙሉ ለማዋል ካስፈለገ የፍትሐ ብሔርና የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕጎቻችንን ቴክኖሎጂውን ለመጠቀም በሚያስችል መልኩ ልናሻሽል ይገባል፡፡ ይኸውም በተለየ ከኤሌክትሮኒክ ፋይሊንግና ከተገልጋዮች ኤሌክትሮኒክ ሲግኒቸር ጋር ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮችን ሊገዙ የሚችሉ የሕግ ድንጋጌ­ዎችን በሥነ ሥርዓት ሕጎቻችን ውስጥ ስለሚያስፈልጉን ነው፡፡ አሁን በመሻሻል ላይ ያለው የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕግ አርቃቂ ቡድን በማሻሻል ሒደቱ ለወደፊት ሊመጣ የሚችለውን አውቶሜሽን መሠረት ያደረጉ ድንጋጌችን በረቂቅ ሕጉ ውስጥ ሊያካትት ይገባል፡፡

በቀጣይ ይህ ጽሑፍ ‹‹አውቶሜሽን ምንድን ነው?›› ‹‹ፍርድ ቤቶችንና የፍትሕ ሥርዓቱንስንዴት ሊረዳ ይችላል?›› የሚሉ ጭብጦችን አንስቶ ዳሷል፡፡

‹‹አውቶሜሽን›› ጽንሰ ሐሳብ

አውቶሜሽን የዘመኑ ቴክኖሎጂ ካፈራቸው ዕውቀቶች መካከል አንዱ ነው፡፡ በአውቶሜሽን የተዋጀ የቴክኖሎጂ መተግበሪያ የሚሰጠው ግልጋሎትም ከተራ ቴክኖሎጂ­ዎ ራቀበራሱ ውሳኔዎ­ችንና መደምደሚያ­ዎችን የሚሠራ የኮምፒዩተር ሥርዓት ያለው ቴክኖሎጂ ነው፡፡ በአጠቃላይም አውቶሜት የተደረገ የኮምፒዩተር ሥርዓት ሦስት ዋና ዋና ነገሮችን ሊተገብር ይችላል፡፡ ይኸውም በአካባቢው ማለትም በኮምፒዩተር ሥርዓቱ ውስጥ የሚሰጡትን መረጃዎ­ ያቀናጃልንዲሁም ያደራጃል፡፡ የተሰጠውን መረጃ ያብላላል (It Processes a Given Data) ያገኘውን መረጃ መሠረት አድርጎ ለሰዎ­ መረጃ ይሰጣልንዲሁም የሚፈለገውን ሥራ ሠርቶ ያቀርባል፡፡ ይኸውም አውቶሜሽን ስንል ዘመኑ በሰጠን ማናቸውም ቴክኖሎጂ መጠቀም ማለት ብቻ አለመሆኑን ያስገነዝባል፡፡ አውቶሜሽን የቴክኖሎጂ ፍሬ የሆኑትንንደ ኮምፒዩተር፣ ኔትዎ­ርክ፣ ኢንተርኔትና ስካነር ያሉትን የቴክኖሎጂ ውጤቶች በነጠላ ከመጠቀም በዘለለ የኮምፒዩተር ሥርዓታቸው በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስግዞ ሰነዶችን ማደራጀት፣ መተርጎምና አብራርቶ ሠርቶ የተለየ መደምደሚያና ውጤትን የሚሰጥ ሥርዓትን ያካትታል፡፡

የፍርድ ቤት አሠራርን አውቶሜት በማድረግ ዓቃቤ ሕጎች፣ ጠበቆችንዲሁም ሌሎች የፍርድ ቤት ባለጉዳዮች ወደ ርድ ቤት በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው መዝገብንዲከፍቱ ማድረግ ይቻላል፡፡ ይኸውም የተለያዩ አቤቱ­ታዎችን ማያያዝን ያጠቃልላል፡፡ የመዝገብ መከፈትን ተከትሎ የኮምፒዩተር ሥርዓቱ ከሰው ንክኪ ውጪ ተገቢውን ችሎት ይመድባል፡፡ መዝገቡ የተመደበለት ችሎትም አስፈላጊውን ማጣራት አድርጎ መዝገቡንዲቀጥል ያለንደሆነ የኮምፒዩተር ሥርዓቱ ችሎቱ ያለበትን የሥራ ጫና መሠረት አድርጎ በመዝገቡ ላይ ቀጠሮ ይሰጣል፡፡ንዲህንዲህ ያለ ይኸው ሥርዓትንደ አግባቡ አስቀድመው የሚሰጡትን መሠረታዊ መረጃ­ዎ መሠረት በማድረግ ቀለል ያሉ የወንጀልና የፍትሐ ብሔር ፍርዶችን፣ ውሳኔ­ዎችን፣ ብይኖችንና ትዕዛዞችን በራሱ ሠርቶ ያትማል፡፡

ከላይ ለመዳሰስ የሞከርኳቸውን የአውቶሜሽን ሥርዓት ፍሬ­ዎ ዛሬ ላይ የተቋደሱ ያሉት በዕድገት ደረጃቸው ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱት አገሮች ብቻ አይደሉም፡፡ ይልቁንስ በማደግ ላይ ያሉ የአፍሪካ አገሮች ጭምር ወደዚሁያመሩ ይገኛሉ፡፡ ለዚህም በዋቢነት በምሥራቅ አፍሪካ በኬንያ፣ በኡጋንዳና በአንጎላ ርድ ቤቶች ያለውን ልምድ ማየት በቂ ነው፡፡

የሌሎች አገሮች ልምድንደሚያሳየው ከሆነ አውቶሜሽን የፍርድ ቤትን ሥራን በእጅጉ ያቀላል የፍርድ ቤቶችን ተደራሽነትም ያረጋግጣል፡፡ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን ከማስፈን አንፃርም ቢሆን ከፍተኛ ሚናንንደሚጫወትም የተለያዩ ጥናቶች የተረጋገጠ ነው፡፡ በዚህም ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ለመዋጋትም ሁነኛ መፍትሔ ነው፡፡  በቀጣይ ክፍል አገራችን ኢትዮጵያ ርድ ቤቶችን አውቶሜት ባደርግንደ አገር የፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ልናገኛቸው የምንችላቸውን ፍሬዎ­ንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡ በተጨማሪም መተግበሪያው ለዳኞች የተለያዩ ትዕዛዞችንና ቀለል ያሉ ውስብስብ ክርክር የሌለባቸውን ጉዳዮች በቀላሉ በሚሞሉ ፎርሞች ትዕዛዞችንና ፍርዶችን አትሞ ያወጣል፡፡ የፍርድ ቤትን አሠራር ሥርዓት ቀላል የሚያደርግ ስለሆነም ይግባኝ የመጠየቅን ሥርዓት በእጅጉ ያቀላል፡፡ ይኸውም በቀጣይ በሰፊው ይብራራል፡፡

የአውቶሜሽን ገፀ በረከቶች

ኤሌክትሮኒክ ፋይሊንግ

በአውቶሜሽን የታገዘ የፍርድ ቤት ሥርዓት ከፋይል አከፋፈት ጀምሮ ያሉ ሥራችን ከግለሰቦች ንክኪ ያላቅቃሉ፡፡ በዚህም የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ቢሮውና ጠበቆች በቀጥታ የኮምፒዩተር ኔትዎ­ርክን በመጠቀም በፈለጉት ቦታ ሆነው የፍርድ ቤት ክስ ሊመሠርቱ ይችላሉ፡፡ የተከፈተው መዝገብ ተገቢውን ፎርማሊቲ ያሟላ ስለመሆኑ በሬጅስትራሩ ተረጋግጦ መዝገቡ የይለፍ ፍቃድን ሲያገኝ ኮምፒዩተሩ በቀጥታ በየምድብ ችሎቱ የሚገኙ ችሎቶችን ጫናና የጉዳዩን ዓይነት በማየት መዝገቡን ወደ አንድ ችሎት ይመራዋል፡፡ መዝገቡ የተመራለት ችሎት ዳኛም መዝገቡን አጣርቶ የይለፍ ወይም የይሻሻል የሚል ትዕዛዙን በኮምፒዩተር ሥርዓቱ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ይሰጣል፡፡ ምላሹን ተከትሎም የኮምፒዩተር ሥርዓቱ ከሰው ንክኪ ውጪ ሆኖ የችሎቱን ጫና መሠረት በማድረግ በኮምፒዩተር በተጣራው አጀንዳ መሠረት ቀጠሮ ይሰጣል፡፡

በኮምፒዩተር ሥርዓት የሚከፈት እያንዳንዱ ፋይል በተለያየ የመረጃ ቋት ውስጥ ይቀመጣል፡፡ በዚህም የተከፈቱ መዝገቦችና በውስጣቸው የተካተ~ ማስረጃ­ዎችን ከመጥፋትና ከመሰወር ይታደጋል፡፡ በዚህ ሥርዓት ለሚከፈቱ መዝገቦች የዳኝነት ሒሳብ በኢንተርኔት ባንኪንግ፣ በክሬዲት ካርድ ወይም በሞባይል ባንኪንግ እንዲከፈልባቸው ማድረግ ይቻላል፡፡ መተግበሪያውም ቢሆን ይኸው ስለመፈጸሙ ሊያረጋግጥ የሚችል አቅም ያለው ሆኖ የሚሠራ ነው፡፡

በፍርድ ቤት የሚደረጉ ክርክሮችና የምስክር ቃል በድምፅና በጽሑፍ በቀጥታ ለዳኛው ተደራሽንዲሆን ማድረግ

ርድ ቤቶችን በቴክኖሎጂ ማገዝ አንደኛው ዓላማ ዳኞች በችሎት ላይ ሰዓታቸውን በመጻፍንዳያሳልፉ ነው፡፡ በተለይም በክስና ምስክር መስማት ቀጠሮ­ዎ ላይ ዳኞች ሙሉ ትኩረታቸውን ክርክር ባስነሳው ጭብጥንዲሁም በተከራካሪ ወገኖችና በምስክሮቻቸው ላይ አድርገው ጉዳዩን በሙሉ ትኩረትንዲረዱ ማስቻል ነው፡፡ ይህንን ለማሳካት በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ርድ ቤት በሚገኙ የቀጥታ ክሶች ላይ ክስና ምስክር የሚሰማው በድምፅ መቅረጫ መሣሪያ በማገዝንዲሆን ተደርጓል፡፡ ይኸውም በፌዴራል መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በሚገኙ የንግድ ችሎቶችና አንዳንድ የወንጀል ችሎቶች ላይ ተፈጻሚ ነው፡፡

ከላይ ለመግለጽንደሞከርኩት ይኸው አሠራር ክስና ምስክር በሚሰማበት ወቅት ዳኛው ከጽሑፍ ሥራ ተላቆ ተከራካሪ ወገኖችና ምስክሮቻቸው ሊጠየቁ የሚገባቸውን ጥያቄ­ችን አገናዝቦንዲያዘጋጅ ይረዳዋል፡፡ በዚህ ብቻም ሳይወሰን ዳኛው የተከራካሪ ወገኖችንና የምስክሮቻቸውን አጠቃላይ ሁኔታ በችሎትንዲመረምርድል ይሰጠዋል፡፡

ርድ ቤቶችን አውቶሜት ማድረግ አሁን ካለው የፍርድ ቤት የክስና ምስክር መስማት ሒደት በተጨማሪነት በችሎት የተቀረፀው ቃል በድምፅና በጽሑፍ ተገልብጦ በኮምፒዩተር ሥርዓቱ መሠረት ለዳኛው ሁሌም በአቅራቢያውንዲኖር ያደርጋል፡፡ ይኸውም ዳኛው በማናቸውም ወቅት በመዝገቡ ላይ ለሚሠራቸው ሥራዎ­ ተገቢው ግብዓት በአቅራቢውንዲኖር ይረዳዋል፡፡ በዚህም የውሳኔዎ­ችን ጥራት ለማስጠበቅ ይቻላል፡፡

የፍርድ ቤት ሰነዶችን ማዘጋጀት

የፍርድ ቤት ሥራን ለማሳለጥ የሚሠሩ መተግበሪያዎ­ ዋነኛ ተግባር ሊሆን የሚችለው በቀላሉ ሰነዶችን የማደራጀትንዲሁም መሠረታዊ መረጃ­ዎችን በመቀበል ቀለል ያሉ ሊባሉ የሚችሉ ፍርዶችን ትዕዛዞችንንዲሁም ብይኖችን ሠርቶ ማተም ፡፡

በአውቶሜሽን የታገዘ የፍርድ ቤት ሥርዓት ሲኖረን የተለየ ቋሚ ፎርም ያላቸውን ሰነዶች በቀላሉ መሠረታዊ መረጃን በመስጠት ብቻ በኮምፒዩተር ሥርዓቱ ትዕዛዝ፣ ፍርድ ወይም ብይን ሠርቶንዲያወጣ ለማድረግ ይቻላል፡፡ ለምሳሌ ያህል አብዛኛውን ጊዜ መዝገቦችንደተከፈቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚጠየቁንደ
ግድ፣ ማስከበርና ጊዜያዊ ቀለብ የመሳሰትዕዛዞችን መሠረታዊ የሆኑ መረጃ­ዎችን ለኮምፒዩተር ሥርዓቱ በመስጠት ብቻትመውንዲወጡ ማድረግ ይቻላል፡፡ ለዋቢነትም የኮምፒዩተር ሥርዓቱ ለግድ የቀረቡትን ንብረቶች ዝርዝር መረጃ በመቀበል ብቻ ንብረቶችንዲታገዱ ወይምንዲከበሩ ለማድረግንዲችል ተደርጎ የሚሠራ ነው፡፡ ከጊዜያዊ ቀለብ ጋር የተያያዙ ክርክሮችንና ትዕዛዞችንም በተመሳሳይ መንገድ በቀላሉ በኮምፒዩተር ሥርዓቱ ማሠራት ይቻላል፡፡

ወደ ወንጀል ጉዳዮች ስንመጣም መተግበሪያው በተመሳሳይ የመያዣና የብርበራ ትዕዛዞችን፣ በምንነት ላይ መሠረት ያደረጉ የጥፋተኝነት ውሳኔንንዲሁም የቅጣት ዓይነትና መጠንን በሚሰጠው መሠረታዊ መረጃ መሠረት ሠርቶ ሊያወጣ ይችላል፡፡ ለምሳሌ ያህል መተግበሪያው ተገቢውን የወንጀል ድንጋጌ የቅጣት ማቅለያና የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶችን በመቀበል በቀላሉ ቅጣትን ለመወሰንንዲችል ሆኖ የሚሠራ ነው፡፡ እንደዚህ ያሉ ጥራታቸውን የጠበቁ መተግበሪያ­ዎ በሥራ ላይ ሲውሉ የዳኞችን ጉልበትና ሰዓት ከመቆጠብም በተጨማሪ በፍርድ ቤቶች ለሚሰጡ ትዕዛዞችና ፍርዶች ጥራት ሁነኛ አስተዋጽኦ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡

ተገቢውን ሕግና ውሳኔ መጠቆም

የፍርድ ቤት ሥራን አውቶሜት ከተደረገ የመተግበሪያው አንዱ በጎ ጎን ሊሆን የሚችለው ከተያዘው ጉዳይ ጋር ቀጥተኛ ተያያዥነት ያላቸውን የሕግ ድንጋጌ­ዎችንና የፍርድ ቤት ውሳኔ­ ለዳኞች መጠቆም መቻሉ ነው፡፡ መተግበሪያ­ዎ የተለዩ ውስን የሕግ ቃላትን ወይም ሐረጎችን መሠረት በማድረግ ከመረጃው ጋር የተያያዙ መሠረታዊ ድንጋጌ­ዎችን ወይም የፍርድ ቤት ውሳኔ­ዎችን ለዳኛው ሊጠቁሙ ይችላሉ፡፡ በዚህም ዳኞች መተግበሪያውን በመጠቀምየሠሩት ያለውን ሰነድ የተመለከቱ ወሳኝ የሕግ ድንጋጌዎ­ንዲሁም የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎ­ ጠቋሚ መረጃ ከኮምፒዩተር ሥርዓቱ ሊያገኙ ይችላሉ፡፡

ይኸው ቴክኖሎጂ ዳኞች ሕጎችንና የፍርድ ቤት ውሳኔ­ዎችን በመፈለግ ጊዜያቸውንንዳያባክኑ ይረዳቸዋል፡፡ በተጨማሪም ወሳኝ የሆኑ የመረጃ ግብዓቶችን በመስጠት ዳኞችን ስህተት ከመሥራት ሊደግፉና የፍርድ አሰጣጥ ጥራትና ቅልጥፍና ደረጃን ያሳድጋል፡፡

የጉዳዮችን መጓተት መቅረፍና የተጠያቂነት ሥርዓትን መዘርጋት

ርድ ቤቶችን በቴክኖሎጂና አውቶሜሽን መደገፍ ጉዳዮችን ከመጓተት ይታደጋል፡፡ በርካታ  አገሮችም ቢሆኑ የረዥም ጊዜ ውዝፍ የፍርድ ቤት ፋይሎችን በፍጥነት ለማቃለልና የፍርድ ቤት ሙግት ሥርዓታቸውን ለማሳለጥ ተጠቅመውታል፡፡ የአውቶሜሽን ሥርዓቱ ይህንን የሚያደርገው በቀጠሮ አሰጣጥና በመረጃ ረገድ ግልጽና የማይዋዥቁ መርሆዎች ተግባራዊ በማድረግ ነው፡፡

በፍርድ ቤቶች ውስጥ አውቶሜሽንን ተግባራዊ በማድረግ የቀጠሮ አሰጣጥ ሥርዓትን በኮምፒዩተር የታገዘ ለማድረግ ይቻላል፡፡ ማናቸውንም የመልስ መስጫ፣ ክስ መስማት፣ ምስክር ማሰሚያና የመሳሰሉትን ቀጠሮዎ­ የኮምፒዩተር ሥርዓቱ ከሰው ንክኪ ውጪ ሆኖ የችሎቱን ጫና በራሱ በማገናዘብ ቀጠሮን ይሰጣል፡፡ በዚህም የጉዳዮችን አላግባብ መጓተት ይቀርፋል፡፡  በዚህ መልኩ የተደራጀው ሥርዓት ቀጠሮ በመስጠት ብቻ ሳይወሰንያንዳንዱ ችሎት በቀጠሮ ቀን ሊሠራ የሚገባውን ሥራ ስለመሥራቱ ማረጋገጫ ይሰጣል፡፡ ዳኞችም ቢሆኑ ያለምክንያት የቀጠሮ ቀንንንዲቀይሩ አይፈቅድም፡፡ ዳኞችና ሌሎች የፍርድ ቤት ሠራተኞች ቀጠሮ ለመቀየር ቢፈልጉ የሚቀይሩበትን ምክንያት በኮምፒዩተር ሥርዓቱ ላይንዲገልጹ ያስገድዳል፡፡ ቀጠሮ የሚለወጥባቸው ምክንያቶችም በሥርዓቱ ላይ ተለይተው ይወስናሉ፡፡ በዚህም ርድ ቤቶች ያለበቂ ምክንያት የቀጠሮ ለውጥንንዳያደርጉ ይገድባል፡፡

የአውቶሜሽን ሥርዓቱን በቀጥታያንዳንዱ ችሎትና ሠራተኛ የሚሠራውን ሥራ በቀጥታ በፍርድ ቤቱ ላፊ­ዎ ቢሮአቸው ውስጥ ሆነው እንዲከታተሉም ይፈቅዳል፡፡ በተለይም በፍርድ ቤት በቀጠሮ ላይ አላግባብ በተደጋጋሚ እየተቀጠሩ የቆዩ መዝገቦችን የአውቶሜሽን ሥርዓቱ ለይቶ ኃላፊዎ­ ሪፖርት ስለሚያደርግ አላግባብ ጉዳዮች እንዳይጓተቱ ይረዳል፡፡ ይኸውም የፍርድ ቤ ኃላፊዎ­ ያለአግባብ ጉዳዮች የሚጓተቱባቸውን ችሎቶችና የሥራ ክፍሎች ለይተው ተገቢውን የማስተካከያ ዕርምጃ እንዲወስዱ ያስችላቸዋል፡፡ ይኸውም የፍርድ ቤትላፊዎ­ የፍርድ ቤት ሥራን በተዋጣ መንገድንዲመሩ ያግዛል፡፡ በአጠቃላይም የአውቶሜሽን ሥርዓትን በፍርድ ቤቶች ውስጥ መዘርጋት ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበትን የፍርድ ቤት ሥርዓትንድንዘረጋ ሁነኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡

የይግባኝና የሰበር ችሎትን ሒደት ማሳለጥ

በአውቶሜሽን የገዛ የዳኝነት አካልን መገንባት ከላይንደተጠቀሰው መደበኛ የክርክር ሒደትን ያሳልጣል፡፡ በዚህ ብቻም ሳይወሰን የይግባኝና ሰበር ማመልከቻ ሒደቶችን ያሳልጣል፡፡ ይኸውም ማለት በመደበኛ የይግባኝና ሰበር ክርክሮች አካሄድ ላይ በመደበኛ ክርክር የሚሰጠውን ግልጋሎት መስጠቱንደተጠበቀ ሆኖ የሥር ርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ በአጭር ጊዜ ለላይኛው ርድ ቤት ከሰው ንክኪ ውጪንዲደርስ ለማድረግ ያስችላል፡፡

አሁን ባለው መደበኛ አሠራር ማናቸውም ተከራካሪ ወገን ይግባኝ ለማለት ቢፈልግ የሥር ርድ ቤት መዝገብ ግልባጭ ኮፒ ተደርጎንዲሰጠው ለቀናት መጠበቅ ግዴታው ነው፡፡ በሰበር ችሎት ሒደትም የሥር ርድ ቤት መዝገብንዲቀርብ የሚያዝባቸው ጊዜያት አሉ፡፡ የሥር ርድ ቤት መዝገብን ዋናውን ወይም ኮፒውን ለይግባኝ ሰሚው ርድ ቤት ወይም ለሰበር ችሎት በመሸኛ የመላክ ሒደት የሰው ጊዜንና ጉልበትን የሚጠይቅ ነው፡፡

ርድ ቤቶችን አውቶሜት ብናደርግ አሁን የይግባኝ አከፋፈት ሥርዓቱ የሚጠይቀውንንግልት በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ይቻላል፡፡ ምክንያቱም ርድ ቤቶች አውቶሜት ከተደረጉ ሁሉም የፍርድ ቤት ሰነዶች በኮምፒዩተር ሥርዓቱ ውስጥ ይገኛሉ ማለት ነው፡፡ ማናቸውም ይግባኝ ማመልከቻ ሲቀርብም የታችኛው ርድ ቤት በቀጥታ ለይግባኝ ሰሚው ወይም ለሰበር ችሎቱ የሥር ርድ ቤት መዝገብን በኮምፒዩተር ኔትዎርክ ሥርዓት በተወሰኑ ደቂቃ­ ውስጥ ሊልክ ይችላል፡፡ ይኸውም ርድ ቤቶች ቀልጣፋና ጥራቱን የጠበቀ አሠራርን በይግባኝና ሰበር ሥርዓቶች ላይንዲዘረጉ ያስችላቸዋል፡፡

ማጠቃለያ

በአሁኑ ወቅት በርካታ አገሮች የፍርድ ቤት ሥራን ለማዘመን ሲሉ ፍርድ ቤቶቻቸውን አውቶሜት በማድረግ ላይ ይገኛ፡፡ ከላይ ለመጥቀስንደ ሞከርኩት የፍርድ ቤትን አሠራር በተወሰነ ረገድ በመቀየርና በቴክኖሎጂንዲደገፍ በማድረግ በፍርድ ቤቶች ውስጥ ግልጽ የሆነና ተጠያቂነትን መሠረት ያደረገ ሥርዓትን ለመገንባት ችለዋል፡፡ በዚህም ፈጣንና ጥራት ያለው አገልግሎትን ለባለጉዳዮች ለመስጠት ችለዋል፡፡

ጥናቶችንደሚያሳዩትም የአውቶሜሽን ሥርዓቱ አንዴ ከተዘረጋ በኋላ የዚሁ ቴክኖሎጂ ሥርዓት መኖር የፍርድ ቤትን ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል፡፡ የዳኞችንና የድጋፍ ሠራተኞችን የሥራ ጫና በማቅለልም ፍትሕ በአጭር ጊዜንዲገኝ ይረዳል፡፡ ቴክኖሎጂው ከሚያቀርባቸው በርካታ ገፀ በረከቶች በተጨማሪ ግልጽና ተጠያቂ የሚያደርግ ሥርዓት በመዘርጋት የፍርድ ቤት ሥራዎ­ ጥራትንዲጠበቅና ከሙስናንዲፀዱም ያደርጋል፡፡ ስለሆነም የፌዴራል ርድ ቤቶች ይህንንላፊነት በመውሰድ ቀልጣፋና ጥራት ያለውን ፍትሕ ለማዳረስ ሲባል የአውቶሜሽን ሥራውን ሊያስጀምሩ ይገባል፡፡ መንግሥትና ሌሎች ርድ ቤቶችን በማገዝ ላይ ያሉ ተቋማትም ቢሆኑ የፍትሕ ሥርዓቱን ለማዘመን ሲሉ መሠረታዊ በሆነው በዚሁ የቴክኖሎጂ ማሻሻያ ላይ ተገቢውን ወጪ በማውጣት የፍትሕ ሥርዓቱን ሊደግፉ ይገባል፡፡

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊው የሕግ አማካሪ ጠበቃ ሲሆኑ፣ ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ጸሐፊውን በኢሜል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አያሌ የውኃ “ጠርሙሶች”ን በጫንቃ

መሰንበቻውን በአይቮሪ ኮስት መዲና አቢጃን የምትኖር አንዲት ሴት፣ በሚደንቅ...

ወልቃይትን ማዕከል ያደረገው የምዕራባዊያን ጫና

በትግራይ ክልል የተከሰተው የዕርዳታ እህል ዘረፋ የዓለም አቀፍ ተቋማት...

ከቀጣዩ ዓመት በጀት ውስጥ 281 ቢሊዮን ብሩ የበጀት ጉደለት ነው ተባለ

ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከቀረበው 801.65 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ በጀት...