- Advertisement -

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ

ታዋቂው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ዳንኤል በቀለ (/) የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማክሰኞ ሰኔ 25 ቀን 2011 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ  ከቀረቡለት አጀንዳዎች መካከል፣ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በዕጩነት የቀረቡትን ኮሚሽነር ሹመት ማፅደቅ ነበር።

በምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ ለሚመራው ዕጩ አቅራቢ ኮሚቴ በዕጩነት ቀርበው ከነበሩት 88 ግለሰቦች መካከል፣ ባላቸው የትምህርት ዝግጅትና የሥራ ልምድ ተመዝነው ብቁ ሆነው የተገኙት ዳንኤል (/) መሆናቸው ተገልጿል።

ዕጩ ሆነው የቀረቡት ዳንኤል (/) ከኮሚሽነር ኃላፊነታቸው በተጓዳኝ ሌሎች ሥራዎችን ለማከናወን እንዲችሉ እንዲፈቀድላቸው ጥያቄ አቅርበው የነበረ ቢሆንም፣ ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ፋታ የማይሰጡ በመሆናቸው ጥያቄያቸውን ለጊዜው እንደማይቀበለው፣ ነገር ግን ወደፊት የሥራ አፈጻጸማቸው ታይቶ ሊፈቀድላቸው እንደሚችል በመግለጽ ጥያቄውን ውድቅ አድርጎታል።

በዚህም መሠረት ግለሰቡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ሆነው እንዲሾሙ የቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ ምክር ቤቱ ተቀብሎ፣ በአንድ ተቃውሞ በአብላጫ ድምፅ አፅድቆታል። በመሆኑም ተሿሚው የቀድሞውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር (/) ይተካሉ።

ተሿሚው ኮሚሽነር ከኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ ሕግ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በቅርቡ የያዙ ሲሆን፣ 1997 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ተካሂዶ በነበረው አገር አቀፍ ምርጫ ማግሥት በተፈጠረው ፖለቲካዊ ቀውስ ለእስር ተዳርገው ነበር።

- Advertisement -

ከእስር ከተለቀቁ በኋላ ከአገር በመውጣት የዓለም አቀፉ ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምሥራቅ አፍሪካ ኃላፊ ሆነው በኬንያ ያገለገሉ ሲሆን፣ በኋላም መቀመጫውን በአሜሪካ ያደረገው የታዋቂው ሒዩውማን ራይትስ ዋች የአፍሪካ ዳይሬክተር ሆነው እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ አገልግለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (/) ሥልጣን ላይ ከወጡ በኋላ ባደረጉት የአሜሪካ ጉዞ ወቅት /ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድን እንዲመሩ ጥያቄ አቅርበውላቸው ጥያቄውን መቀበላቸው የሚታወስ ሲሆን፣ በዚሁ ወቅትም በተመሳሳይ ዳንኤል (/) የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር እንዲሆኑ ያቀረቡላቸውን ጥያቄ ተቀብለው ነበር፡፡ የዶክትሬት ትምህርታቸውን እስኪያጠናቅቁና ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽነርነት ዕጩ የሚመለመልበት ሕጋዊ ሥነ ሥርዓት እስኪፈጸም ድረስ ሹመታቸው መዘግየቱን፣ የሪፖርተር መረጃዎች ያመለክታሉ።

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ህወሓት ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ ፈቃዱ ታገደ

-የቦርድ ትእዛዝ አክብሮ ካልተገኘ ከሶስት ወር በኋላ እንደሚሰረዝ ተገልጿል የምስረታ 50ኛ በዓሉን ለማክበር ቀናት የቀሩት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ህጋዊ ፈቃዱ...

የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ...

የጋዛ ውዝግብ በአፍሪካ ቀንድ ላይ የደቀነው ሥጋት

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማችና የቀድሞ የመካከለኛው ምሥራቅ የፖሊሲ አማካሪያቸው ጄርድ ኩሽነር፣ ከአሥር ወራት በፊት ነበር ፍልስጤሞችን ከጋዛ አንስቶ ሌላ ቦታ ስለማስፈር በይፋ ሲናገር...

አይኤምኤፍ ብሔራዊ ባንክ ገለልተኛ ሆኖ እንዲሠራ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን ይፋ አደረገ

‹‹ማዕከላዊ ባንክ ውሳኔዎቹን በመረጃ ላይ ብቻ ተመሥርቶ ካላሳለፈ አገሪቱንም ሆነ ኢኮኖሚውን አይጠቅምም›› ክርስታሊና ጆርጂዬቫ፣ የአይኤምኤፍ ማኔጂንግ ዳይሬክተር የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

የኢትዮጵያ ሠራዊት በሶማሊያ ሰላም ማስከበር እንዲሳተፍ ምክክሩ መቀጠሉ ተገለጸ

የ38ኛው አፍሪካ ኅብረት ጉባዔ ከ35 በላይ መሪዎች ይታደማሉ ተብሏል የኢትዮጵያ ሠራዊት በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሳተፍ በአፍሪካ ኅብረት ማዕቀፍ ምክክሩ መቀጠሉን፣ ሒደቱ በመልካም ውጤት እንደሚቋጭ...

ገንዘብ ሚኒስቴር መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ያለውን የዕዳ ሽግሽግ ድርድር አይኤምኤፍ አረጋገጠ

አበዳሪዎች የክፍያ ጊዜ ለማራዘም የአገሮች ፋይናንስ አቋምን ጨምሮ የሰላም ሁኔታ እንደሚጠና ተገልጿል የገንዘብ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ ከቡድን ሀያ አባል አገሮች የጋራ ማዕቀፍ ሥር ከተካተቱ አገሮች...

አዳዲስ ጽሁፎች

ህወሓት ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ ፈቃዱ ታገደ

-የቦርድ ትእዛዝ አክብሮ ካልተገኘ ከሶስት ወር በኋላ እንደሚሰረዝ ተገልጿል የምስረታ 50ኛ በዓሉን ለማክበር ቀናት የቀሩት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ህጋዊ ፈቃዱ...

የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የካቢኔ አባል የሆነ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ ስልክ ደውሎላቸው ሰሞኑን በተካሄደው ድርጅታዊ ጉባዔ ዙሪያ እያወሩ ነው]

ሰላም ክቡር ሚኒስትር፡፡ ሰላም ሰላም፣ እንዴት ነህ? ቢዘገይም እንኳን አደረስዎት ክቡር ሚኒስትር። ለምኑ? ለፓርቲዎ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ እንኳን አደረስዎት ማለቴ ነው። ቆየ እኮ ከተጠናቀቀ? አስቀድሜ ቢዘገይም ያልኩት እኮ ለዚያ ነው...

የጋዛ ውዝግብ በአፍሪካ ቀንድ ላይ የደቀነው ሥጋት

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማችና የቀድሞ የመካከለኛው ምሥራቅ የፖሊሲ አማካሪያቸው ጄርድ ኩሽነር፣ ከአሥር ወራት በፊት ነበር ፍልስጤሞችን ከጋዛ አንስቶ ሌላ ቦታ ስለማስፈር በይፋ ሲናገር...

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በውክልና ለግሉ ዘርፍ ለማስተላለፍ ያቀዳቸው አገልግሎቶች

የከተማው አስተዳደር ካቢኔ ሰሞኑን ባሳለፈው ውሳኔ የተመረጡ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በሦስተኛ ወገን ለማሠራት የሚያስችለውን ደንብ በማፅደቅ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ታውቋል፡፡  አስተዳደሩ ደንቡን ከማጽደቁ አስቀድሞ በሦስተኛ ወገን...

የተገራ ስሜት!

እነሆ መንገድ ከስታዲዮም ወደ ጦር ኃይሎች። በጥበቃ የተገኘ ለበርካታ ዓመታት ያገለገለ ሚኒ ባስ ታክሲ ውስጥ ተሳፍረናል፡፡ ምሁር መሳይ ተሳፋሪ አጠገቡ ለተቀመጠ የዕድሜ እኩያው ማብራሪያ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን