Wednesday, December 6, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ግራ በሚያጋባ ሁኔታ ውስጥ የሚከናወነው የለውጥ ጉዳይ!

(ክፍል ሁለት)

ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

ግራ የገባው ዝብና ምሁር

በአጠቃላይ ሲታይ የኢትዮጵያ ዝብ ከዛሬው የተሻለ ሁኔታ ቢመጣለት በጣም ደስተኛ ነው። ቢያንስ በሰላም ወጥቶ በሰላም መግባትን ይፈልጋል። ይሁንና ያለበትንና የሚኖርበትን ሁኔታ በደንብ ይረዳ አይረዳ፣ ምን ይነት ብረተሰብ ይመኝ እንደሆነና፣ በጭንቅላቱ ውስጥ የሳለው አንዳች የብረተሰብ ሞዴል ይኑረው አይኑረው ለማወቅ በጣም አስቸጋሪ ነው።

ብረተሰብ ታሪክ ውስጥ አንዳች ይነት ርዓትን የሚፈጥሩ አብዛኛውን ጊዜ የፖለቲካ ልጣንን የጨበጡ ናቸው። በአንድ አገር ውስጥ በተለይም ደግሞ አምባገነናዊ አገዛዞች በሰፈኑባቸውና በጥልቀትና በስፋት የሚያስብ የነቃ  የብረተሰብ ክፍል በሌለበት አገር አገዛዞች የሚያወጧቸውና ተግባራዊ የሚያደርጓቸው ፖሊሲዎች በአቦ ሰጡኝ ነው። በተለይም ደግሞ በዓለም አቀፍ ኮሙኒቲው ግዳጅና ምክር ተግባራዊ እንዲሆኑ የሚደረጉ ፖሊሲዎች የተረጋጋና ለፈጠራ የሚያመች፣ እንዲሁም ደግሞ ግብረ ገብነትንና ምግባርን የሚያዳብሩ ማበረሰብ እንዲመረት የሚያግዙ ሳይሆኑ የተቃራኒውን እንዲሆን የሚያደርጉ ናቸው። ካለፉት 28 ዓመታት ጀምሮ በአገራችን ምድር እየባሰበት የመጣና በተለይም ወጣት ሴቶችንና በዕድሜ ገፋ ያሉትን የሚያስፈራና የሚያስቆጣ ሁኔታ ከሰማይ ዱብ ያለ ሳይሆን ልጣንን በጨበጡትና የዝባችንን ዕድል በሚወሰኑትና በውጭ ኃይሎች የተቀነባበረ ሴራ ነው። በተለይም ተግባራዊ የሆነው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ዋናው ዓላማውም ሳይንስና ቴክኖሎጂን በማዳበር የሰፊውን ዝብ ኑሮ በማሻሻል ጥበባዊና የተከበረ አገር መገንባት ሳይሆን፣ ደሃና ለማኝ፣ እንዲሁም ፈሪና አጎብዳጅ ብረተሰብ ለመፍጠር ነው። ከዚህ ስንነሳ ባለፉት 28 ዓመታት ከዚያ በፊት ታይተው የማይታወቁ የአገራችንን እሴቶች የበጣጠሱ ሁኔታዎች በመስፋፋት ዝቡ እንደ ማበረሰብና እንደ ብረተሰብ እንዳይኖር አድርገውታል። የሙስና መስፋፋት፣ ጥቂት ደመወዝ እያለው በጥቂት ዓመታት የብዙ መቶ ሚሊዮኖች ዶላርና ቁጥራቸው የማይታወቁ ንብረቶች ሀብታም መሆን፣ የዕፅ ሱስና የሴተኛ አዳሪነት መስፋፋት፣ የማጅራች መቺዎችና የኪስ አውላቂዎች እንደ አሽን መፈልፈልና ለሰፊው ዝብ ጠንቅ መሆን፣ ተፈጥሮአዊ ያልሆነ የወሲብ ተግባር መስፋፋትና አገሪቱም ለእንደዚህ ይነቱ አያፊ ተግባር ክፍት መሆኗ፣ ሰላዮች እንደፈለጋቸው መዋኘት መቻላቸውና በልጣን ላይ ያሉትንና የተወሰነውን ኤሊት በማባግ ሀብት እንዲዘረፍ ማድረግ. . . ወዘተ. እነዚህና ሌሎች የአገርን ክብር እንዲጣስ ያደረጉት ሁሉ ከሰማይ ዱብ ያሉ የእግዚአብር ቁጣዎች ሳይሆኑ በሰው የተሩ ናቸው። እነዚህ ነገሮች በሙሉ ማን እንደፈጠራቸው፣ ለምንስ እንደዚህ ይነት አፀያፊ ተግባሮች እየተለመዱና ተቀባይነትን እያገኙ መምጣት እንደቻሉ የሚያጠና ድርጅትም ሆነ ግለሰብ ባለመኖሩ በተለይም ሰፊው ዝብ ግራ ተጋብቶ እንዲኖር ተደርጓል። ሳይወድ በግድ ይህ ይነቱ አፀያፊ ተግባር እንደ አንድ የኑሮ ፍልስፍና አድርጎ እንዲቀበለው ሊደረግ በቅቷል።

በዚህ ይነቱ የተዘበራረቀ ሁኔታ ደግሞ በተለይም ወጣቱን የሚያሳስቱና መንፈሱን የሚሰልቡ ሃይማኖት መሰል ነገሮች በመስፋፋት አቅመ ቢስ አድርገውታል። የሰውን ጭንቅላት በማደንዘዝ እንፈውስለን በማለት ገንዘብ በመሰብሰብና ካዲላክ መስል መኪናዎችን በመግዛት የሚንደላቀቁ ‹‹ፓስተሮች›› ነን ባዮች የተከፈተላቸውን በርና የተለቀቀላቸውን ሜዳ በመጠቀም ባለፉት 28 መታት በቀላሉ መፍት የማይገኝለት ወንጀል ርተዋል፡፡ እየሩም ነው። በዚህ ላይ ምሁር ነን በማለት በየቴሌቪዥኑ እየወጡ ቃለ መጠይቅ የሚደረግላቸውና መልስ የሚሰጡ በአገሪቱ ምድር ላይ የሚታየውን ሁኔታ ለምን እንደተፈጠረ ከማስረዳትና መፍት ከመሻት ይልቅ የሚሆን የማይሆነውን በመናገር በተለይም ወጣቱ ሀቁን ከውሸት እንዳይለይ ለማድረግ በቅተዋል፡፡ ዛሬም እያደረጉ ነው።

በመረቱ የምሁሮች ዋና ተግባር አንድ ብረተሰብ ዝብርቅር በሆነና በተበላሸ ሁኔታ ውስጥ የሚገኝ ከሆነ ዝም ብሎ ማየትና በችግሩ ላይ ሌላ ችግር መጨመር ሳይሆን ለእነዚህ ሁኔታዎች ምክንያት የሆኑትን ነገሮች ማጥናትና መፍት መሻት ነው። በተለይም በመንግትና በአገዛዙ፣ እንዲሁም በውጭ ኃይሎች ግፊት ተግባራዊ የሚደረጉትን ፖለቲካዊ፣ የኢኮኖሚና የማበራዊ ፖሊሲዎች በመመርመርና የሚያስከትሉትን ብረተሰብዊና ባህላዊ ጠንቆች ለሰፊው ዝብ በማሳየትና የተሻለ አማራጭ በማቅረብ የዝባቸው አለኝታ መሆናቸውን ማረጋገጥ ነው። ይሁንና ግን ምሁሩ  ለዝብና ለአገር ጠበቃ ከመሆን ይልቅ በዓለም ኮሙኒቲው አማካይነት ተግባራዊ የሚሆነውን የኢኮኖሚም ሆነ ሌላ ፖሊሲዎች ዝም ብሎ የሚመለከት ከሆነ ለሚፈጠረው ምስቅልቅል ሁኔታ መንግት ብቻ ሳይሆን ተጠያቂው እሱም ጭምር ነው። ዝም ብሎ የሚመለከት ምሁር ደግሞ ራሱን ነፃ ያላወጣና በራሱ ፍላጎት የሚገዛ ሳይሆን በውጭ ኃይሎች የሚጠመዘዝና እነሱን የሚያመልክ ነው። ስለሆነም እንደዚህ ይነቱ ምሁራዊ ኃይል ታላቁ የጀርመን ፈላስፋ ኢማኑኤል ካንት እንደሚለው ‹‹በፍላጎቱና በማሰብ ኃይሉ የማይገዛ ነው፤ ሰው መሆኑንም የሰረዘ ነው፤›› እንደዚህ ይነቱ ምሁር ብረተሰብዊ ጥቅምን ማምጣትና አገር ከማስከበር ይልቅ ብራዊ ውርደትን ነው የሚያስከትለው።

ከዚህ ስንነሳ ለፉት ምሳና አርባ መታት የደረሱት አሰቃቂ ድርቶች፣ እንዲሁም ድህነትና ረሃብ ተስፋፍተው የአገራችን መለያዎች መሆናቸው የሚያመለክተው የምሁሩንም ድክመት ነው። ሰፋ ባለና በተወሳሰበ ዕውቀት እንዲያስብ ሆኖ ያልተዘጋጀው ምሁራዊ ኃይል፣ በተለይም እንደ ኢኮኖሚክስ የመሳሰሉትን ትምህርቶች ከአንድ አንፃር ብቻ በማየትና የአገራችንን ችግር ወደ ጠያቂነትና አቅራቢነት ብቻ (Demand and Supply) በመቀነስና የገበያ ኢኮኖሚ የተወሳሰበውን የብረተሰብችንን ችግር መፍቻ አድርጎ በመመልከቱ ለተመሰቃቀለው የአገራችን ችግርና ለድህነትም መስፋፋት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተጠያቂ ነው ማለት ይቻላል። ይህ ብቻ ሳይሆን፣ አብዛኛው ምሁር ወይም ተማርኩ ነኝ የሚለው የሚያደላው ወደ ፖለቲካ ብቻ ነው። የፖለቲካ ጉዳይንም የሚመለከተው ልጣንን ከመጨበጥ አንፃር ብቻ ስለሆነ ፖለቲካ የሚባለው ግዙፍ ጽንሰ ሳብና ሳይንስ ከሌሎች የብረተሰብ ጥያቄዎች፣ ከፍልስፍና፣ ከሳይንስና ከቴክኖሎጂ እንዲሁም ከማበራዊና ከኢኮኖሚ ጥያቄዎች ተነጥሎ በመታየቱ የብረተሰብችንን ችግር መፍቻ መሆኑ ቀርቶ መፋለሚያና ግራ አጋቢ መሪያ ሊሆን በቅቷል።

ከዚህም ባሻገር ዝባችን ግራ የተጋባው በምሁራኑ ብቻ ሳይሆን ተቃዋሚ ነን በሚሉ የፖለቲካ ድርጅቶችም ጭምር ነው። በመጀመያ ደረጃ ተቃዋሚ ነኝ የሚል መደራጀቱንና ከዝብ ጋር ግንኙነት እንዳለው ማረጋገጥ መቻል አለበት። በየቀበሌው፣ በየወረዳዎችና በክፍለ ገር ከተማዎችና በመንደሮችም ጭምር ሰፋ ያለ የአደረጃጀት መዋቅር እንዲኖረው ያስፈልጋል። ተቃዋሚ ነኝ የሚል ድርጅት በምን ይነት ራዕይ ወይም ርዕዮተ ዓለም እንደሚመራ ማሳየት አለበት። ልጣን ላይ ካለው አገዛዝ በምን እንደሚለይ ለሰፊው ዝብ ማሳየት አለበት። ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማበራዊ፣ ባህላዊና የ ልቦና ችግሮች ካሉና ጎልተው የሚታዩ ከሆነ ምክንያቶቻቸውንና እንዴትስ ደረጃ በደረጃ መፈታት እንደሚችሉ መመርመርና መፍት ማቅረብ አለበት። በተለይም ከውጭ የሚመጡ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን በማጥናት፣ ተግባራዊ በሚሆኑበት ጊዜ ሊያስከትሉ የሚችሉትን ብረተሰብዊ ጠንቆች ለሰፊው ዝብ ማስተማርና የተሻለም መፍት ማቅረብ አለበት።  እያንዳንዱ ድርጅት ወይም ፓርቲ የራሱ የሆነ የአገርንና የዓለምን ሁኔታ የሚዳስሱ ሳምንታዊ ጋዜጣና በየወሩ የሚታተምና ሰፋፊ ሀተታዎችን የያዘ መጽት ያስፈልገዋል። የፖለቲካ ድርጅቶች ጋዜጣዎችና መጽቶች የየፓርቲዎችን ራዕይ ማሳያዎችና ማንነታቸውንም የሚገልጹ ናቸው። በዚህ መልክ ያልተደራጀና ራዕይ የሌለው የፖለቲካ እንቅስቃሴ በመረቱ ዝብን ግራ ከማጋባት በስተቀር ለአገራችን የተወሳሰቡ ችግሮች እንደ አማራጭ ሆኖ ሊቀርብ አይችልም። አገራችንም በና መረት ላይ እንድትገነባ የማድረግ ይልና ብቃትም ሊኖረው አይችልም።

ከዚህ ስንነሳ በአገራችን ምድር ከመቶ በላይ የሚሆኑ ተደራጀን የሚሉ ‹‹ፓርቲዎች›› አሉ። ሁኔታውን ለሚከታተለው እነዚህ ሁሉ ድርጅቶች ከረም ጊዜ ምሁራዊ እንቅስቃሴና ጥናት በኋላ ማበራዊና የብረተሰብ ጥያቄዎችን በማንሳትና በማጥናት የተወለዱና ታንፀው የወጡ አይደሉም። በፓርቲ ደረጃ ተደራጀን የሚሉ ሁሉ በተለይም ባለፉት 28 ዓመታት በአገራችን ምድር ተግባራዊ የሆነውን የኒዎሊበራል የኢኮኖሚ ፖሊሲና ጠንቁን በማጥናትና በመጻፍ ዝቡን፣ በተለይም ወጣቱን ለማስተማር የሞከሩ አይደሉም። ስለሆነም በሀብታምና በደሃ መከል ሰፊ የገቢ ልዩነት ሲፈጠርና አብዛኛው ዝብ ወደ ድህነት ዓለም ሲወረወር ዝም ብ የሚመለከቱ እንጂ ድምቸውን በማሰማትና በመጻፍ የዝብና የአገራችን ጠበቃ መሆናቸው አላረጋገጡም። በተለይም አገራችን የአካባቢ ውድመት ሲደርስባት፣ ጫካዎች ሲመነጠሩ፣ ወጣቱን የሚያበላሹ ብልሹ ነገሮች ሲስፋፉ፣ የዕፅ ሱሰኛ እንዲሆን ሲደረግ፣ የተራድኦ ድርጅቶች የሚባሉት በመስፋፋት የአገራችንን እሴቶች ሲያፈራርሱ፣ ከተፈጥሮና ከብረተሰብ ግ ውጭ የሚሆኑ የንፃ አራሮች ሲሩ ዝም ብሎ በመመልከት የአገራችንን ውድመት ማፋጠን ችለዋል ማለት ይቻላል። ስለሆነም ግራ የተጋባው ዝብ አልፎ አልፎ የሚጠይቀው ጥያቄ እንደዚህ ይነቱ ተቃዋሚ ነኝ የሚል ኃይል ለምንድ ነው የሚያስፈልገው? ለምንድን ነው ግራ የሚያጋባን? እያለ ነው። የተቃዋሚው ኃይል ችግር ልክ እንደ አዛዞቻችንም በውጭ ኃይሎች ላይ ያለው አመለካከት የተዛባና በጥናት ላይ የተመረተ አይደለም። አብዛኛው ተቃዋሚ ነኝ የሚለው ኃይል የውጭ ኃይሎች ለአገራችን ዕድገትና መረጋጋት ጠንቅ መሆናቸውን በፍም የተረዳ አይመስልም። በተለይም ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት በኋላ የተዋቀረውን ዓለም አቀፋዊ የሚሊሪ፣ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ኃይል አላለፍና፣ በኢኮኖሚ ፖሊሲዎች አማካይነትም በደካማ አገሮች ውስጥ በመግባትና ተፅዕኖ በማድረግ የሚፈጠሩትን ብረተሰብዊና ማበራዊ ውዝግቦች በደንብ ያላጠና ወይም ያልተረዳ በመሆኑ የካፒታሊስት አገሮችን እንደ ተፈጥሮአዊ አጋርና ዕርዳታ ሰጪ አድጎ ነው የሚመለከታቸው። በሌላ አነጋገር ተቃዋሚው ኃይል ዛሬ በዓለም ላይ የሚታዩት የኢኮሎጂ ቀውሶች፣ የፖለቲካ ውዝግቦች፣ የማበራዊ ሁኔታዎች መናጋትና የአፍሪካ መንግታትም ችግሮችን መፍታት አለመቻል ወዘተ. ዋናው ምክንያት ካፒታሊዝም ልቅ በሆነ መልክ በዓለም አቀፍ ደረጃ መስፋፋቱን የሚቀበል አይደለም። ስለሆነም ተቃዋሚው ኃይል የዓለም ኮሙኒቲው የየአገሮችን ባህልና የተፈጥሮ ሁኔታ እንዲሁም የመንግታትን አወቃቀርና የሰፊውን ዝብ ልቦና ሳያገናዝብ ተግባራዊ እንዲሆኑ ግፊት የሚያደርጋቸው ፖሊሲዎች አገራችን ውስጥ ለተከሰቱትና በጉልህ ለሚታዩት ቀውሶች ዋናው ምክንያት መሆኑን በፍም አይቀበልም። ለማመንም በፍም አይፈልግም። በአብዛኛው ተቃዋሚ ኃይል ምነት የውጭው ኃይል ከበስተጀርባው የሚያውጠነጥነው ምንም ተንኮል የለውም።

አጠቃላዩን የአገራችንን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማበራዊ፣ የባህልና የ ልቦናዊ ቀውሶች ስንመለከት የዝቡ ግራ መጋባት የሚያስደንቀን ሊሆን አይችልም። በአንድ በኩል አንድ አገዛዝ 28 መታት ያህል ከውጭ ኃይሎች ጋር በመተባበርና ከእነሱ ዕርዳታ በማግኘት አገርን ሲያተራምስና የአንድ ትውልድ ዕድል ብቻ ሳይሆን፣ የሁለትና የስት ትውልድ ይወት ሲያበላሽ ዝም ብሎ መመልከት የዝባችንን የንቃተ ህሊና ሁኔታ ያሳያል። በሌላው ወገን ደግሞ ምሁሩ ይህ ይነቱን የትውልድ ጠንቅ ዝም ብሎ መመልከቱና ለዝብ ጠበቃ ሆኖ አለመነሳቱን ስንመለከት የሱንም የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ደረጃ መጠየቃችን የማይቀር ነው። መማር ማለት ዝም ብሎ ማየት ወይም መቀበል አይደለም ብለን የምናምን ከሆነ የትምህርቱንም ይዘትና በአጠቃላይ ሲታይ የአገራችንን የብረተሰብ አወቃቀርና የ ልቦና ሁኔታ የግዴታ መጠየቅ አለብን። እንደ ኅበረሰብና እንደ ብረተሰብ መኖር አለብን የምንል ከሆነ ዛሬ ካለንበት ሁኔታ ባሽገር ማየት ያለብን ይመስለኛል። በምድር ላይ የሚታዩትን ምስቅልቅል ነገሮችና በየቦታው የሚካሄዱትን የእርስ በርስ ጦርነቶች ትችታዊ በሆነ መልክ መመልከትና መመርመር መቻል አለብን። ምክንያቶቻውን ለማወቅ የማያቋርጥ ጥረት ማድረግ አለብን። አሁን ባለን አመለካከትና የማሰብ ኃይል ወደፊትም የምንገፋ ከሆነ በእርግጥም የአገራችንን ውድመት ማጠናችን የማይቀር ጉዳይ ነው። የግራ መጋባትና ዝም ብሎ የማየት ውጤት የመጨረሻ መጨረሻ መጥፋት ነው። እንደ ብረተሰብና እንደ በረሰብ አለመኖር ነው። ከዚህ በመነሳት ነው ከአንድ መት ጀምሮ ይካሄዳል የሚባለውን ‹‹ለውጥ›› መመርመር የሚያስፈልገው። ይህ በአዲሱ የገ ኃይልና በብዙዎቻችንም ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘው ለውጥ የሚባለው ነገር በእርግጥስ እንደሚነገርለት ለውጥ ነው ወይ? ብረተሰብችን ከገባበት ማጥ ውስጥ ሊያወጣው ይችላል ወይ? በዚህ ይነቱ ‹‹የለውጥስ ደት›› የአገራችን መረታዊ ችግሮች ደረጃ በደረጃ ሊፈቱ ይችላሉ ወይ? የሚሉትን ጥያቄዎች ጠጋ ብለን እንመርምር።

ለመሆኑ በኢትዮጵያ ምድር ለውጥ እየተካሄደ ነው ወይ?

በመጀመያ ደረጃ ለውጥ ማለት ምን ማለት እንደሆነ እንመልከት። ለውጥ ማለት አንድ ነገር ከነበረበት ሁኔታ ወደ ሌላ  ነገር ሲለወጥ ተለውጧል ወይም ተቀይሯል ማለት ይቻላል። አንድ የጥሬ ሀብት ውስጣዊ ይዘቱ (Chemical Composition) ሳይቀየር፣ በኃይል (Energy)፣ በሰው የማሰብና የጉልበት ኃይል፣ እንዲሁም በማሽን ድጋፍ ከነበረበት ሁኔታ ለሰው ልጅ ጥቅም ወደ ሚያገለግል ፍጆታ ከተለወጠ ይህንን ለውጥ ብለን እንጠራዋለን፡፡ በዚህ መልክ የምንመገባቸው፣ የምንለብሳቸው፣ የምንጠቀምባቸው የረምና የአጭር ጊዜ ዕድሜ ያላቸው ነገሮች በሙሉ የተለወጡና ወደ ቀድሞ ሁኔታቸውም ሊመለሱ የማይችሉ ናቸው። ራሳቸውም ዛፎችም ሆነ ሰዎች በተወሰነ የተፈጥሮ ግ አማካይነትና በዲያሌክቲካል ደት ነው ከነበሩበት ሁኔታ በመለወጥ ዛሬ የምናየው ደረጃ ላይ ሊደርሱ የቻሉት።

ወደ ብረተሰብም ስንመጣ ይህንን ይነቱን ክንውናዊ ሁኔታ እንመለከታለን። ልክ እንደ ጥሬ ሀብትም ብረተሰብዊ ክንዋኔና ለውጥ በሰው የማሰብ ኃይል ማኑፕሌት በመሆን ነው ከዝቅተኛ ወደ ከፍተኛ ደረጃ ሊሸጋገርና ሊቀየር የሚችለው። አንድን ብረተሰብ ሙሉ በሙሉ በዕቅድ አማካይነት መለወጥ ባይቻልም መልክና ርዓት ማሲያዝ የሚቻለው በማሰበ ኃይል አማካይነት ብቻ ነው። እነዚህም ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማበራዊና ባህላዊ ሲሆኑ የለውጡም ይነትና ውስጠ ኃይል (Dynamism) ማግኘት በአንድ አገር ውስጥ በሰፈነው ዕውቀትና ምሁራዊ ኃይል፣ እንዲሁም መንግታዊ አወቃቀር ይወሰናል። መንግትና በልዩ ልዩ ሙያ የለጠኑ ምሁራዊ ኃይሎች የተገለጸላቸው (Enlightened) ከሆኑ አንድ ብረተሰብ ጥበባዊና ፍትዊ በመሆን ለተከታታዩ ትውልድ የሚተላለፍ ይሆናል። ቴክኖሎጂና ሳይንስ ዋናው የሀብት ማመንጫ ዘዴዎች መሆናቸውን በመረዳት አነሰም በዛም የተረጋጋና ሰላም የሰፈነበት አገር መመረት ይቻላል።

ይሁንና ግን በብረተሰብ ታሪክ ውስጥ እንደታየው አንድን ብረተሰብ መለወጥ ወይም ዘመናዊ ለማድረግ አንድን የጥሬ ሀብት ወደ ፍጆታ ነገር እንደ መለወጥ ቀላል አይደለም። የሰው ልጅ ጭንቅላት የተወሳሰበና አፈንጋጭ ስለሆነ ውስጡ ከተዋቀረውና ከለመደው አስተሳሰብ ቀይሮ አርቆ አሳቢ ለማድረግ በጣም አስቸጋሪ ነው። በተለይም ደግሞ አንድ የተወሰነ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሚሊሪያዊ አወቃቀር ከተዘረጋና የተወሰኑ ሰዎች እሱን በመጠቀም ፍላጎታቸውን ተግባራዊ የሚያደርጉ ከሆነ የነበራቸውን ኢኮኖሚያዊና ማበራዊ ሁኔታ (Economic and Social Status) ላለማጣት ሲሉ መሰናክል ይፈጥራሉ። በዚህ ላይ ደግሞ አንድ ይነት ርዕዮተ ዓለም ጭንቅላታቸው ውስጥ ከከተቱ የበላይነታቸውን ላለማጣት ሲሉ ወደ ኃይል የሚያመዝኑበት ጊዜ አለ። ከዚህም በላይ በተለያዩ ድሮች ከውጭው ዓለም ጋር የተሳሰሩ ከሆነ አንድ ላይ በማበር ወደ ውስጥ ፍትዊ አስተዳደርና ጥበባዊ የሆነ የኢኮኖሚ ርዓትና ጠንካራ አገር እንዳይገነባ መሰናክል ይፈጥራሉ። የተለያዩ ምክንያቶችን በመፍጠርና በቡድን በመደራጀት የተወሰነው የብረተሰብ ክፍል ከመረታዊ ጥያቄና ፍላጎት እንዲያፈነግጥ ያደርጋሉ። የሰው ጭንቅላት በማያስፈልግ ነገር እንዲጠመድ በማድረግ የራሳቸውን ጨዋታ ይጫወታሉ። የሚሆን የማይሆን ነገር በመፍጠር በአንድ ድርጅትም ሆነ በአንድ አገር ውስጥ በዝብ መከል አለመተማመን እንዲፈጠር ያደርጋሉ። አንድ ዝብ ይሉን ሰብሰብ አድርጎ ለአንድ ዓላማ እንዳይነሳ የማይሆን ነገር ይነዛሉ። በዚህም ምክንያት የተነሳ አንድ ዝብና አዲስ የወጣት ትውልድ ለውጥ እያለ ከፍተኛ መስዋዕትነት ቢከፍልም የመጨረሻ መጨረሻ ልጣን በሌላ ኃይል በመያዝ የለውጡ ፍላጎት ደብዛው ይጠፋል። ይህንን ጉዳይ የጥቢው አብዮት በመባል በሚታወቀው በቱዚያና በግብ እንዲሁም በሊቢያ የተካሄደውንና ምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የምንመለከተው ቅ ነው። በተለይም ከመጀመያውኑ በሳይንስ፣ በቲዎሪና በፍልስፍና የማይመረኮዝና ዓላማውም የማይታወቅ ትግል የመጨረሻ መጨረሻ እንደሚከሽፍ የታወቀ ጉዳይ ነው። ለማንኛውም ከአንድ ዓመት ጀምሮ በአገራችን ምድር ይካሄዳል ስለሚባለው ለውጥ አንዳንድ መረታዊ ነገሮችን እንመልከት፡፡ ለውጥ ሲባል ታች በተዘረዘሩት መልክ የሚታይና የሚካሄድ መሆን አለበት። ለውጥ ሲባል፣ ከታች ወደ ላይ የሚያድግ (Organic Growth) ነውሁለገብ (Holistic) መሆን አለበት። ለቲካዊ፣ መንግታዊ፣ የተቋማት፣ የኢኮኖሚ፣ የማበራዊ፣ የከተማና የመንደሮች ግንባታንና ሌሎችንም አንድን አገር እንደ አገር የሚያስቆጥትን ነገሮች ሁሉ የሚያጠቃልል ነው። ተከታታይነት (Sustainable) ያለው መሆን አለበት። በመንፈሳዊ ተሃድሶና ውነተኛ ዕውቀት የሚደገፍና ሚመራ መሆን አለበት። ሰፊውን ዝብ ያሳተፈና ለሰፊው ዝብ ጥቅም የሚሆን መሆን አለበት። አገር አቀፍ በሆኑ ተቋማት (Institutions) የሚመረኮዝ መሆን አለበት። እነዚህም ዘመናዊና የተቀላጠፉ ተቋማት መሆን አለባቸው፡፡ በየጊዜው በአዳዲስ የልጠና ዘዴዎች መሻሻል አለባቸው። የአገርንየሰውና የጥሬ ሀብቶች የሚያንቀሳቅስና በራስ መተማመን (Selfreliance) የሚያዳብርና የሚደገፍ መሆን አለበት። ማንኛውም ይወት ያለው ነገር አትክልንም ጨምሮ ውስጥ ባላቸው ኃይል የማደግ ችሎታ አላቸው። የውጭው ሁኔታ አጋዥ ነው። ለምሳ ዘር ሲዘራ ባለው ውስጣዊ ኃይል ርን፣ ግንድንና ቅጠላ ቅጠሎችን ያበቅላል። ከዚያም በኋላ ፍሬ ይሰጣል። ፀይ፣ ዝናብና ሚኒራሎች አጋዦች ናቸው። ሲበዙ ግ አትክል የማፍራት ኃይላቸው ይቀንሳል ወይም ይሞታሉ።

ለውጥ ሲባል በመጀመ ደረጃ ዝብን ረታዊ ፍላጎቶች ማለትም፣ የተሟላ ምግብን፣ መጠለያን ወይም ቤትን፣ ክምናን፣ ትምህርትና ማግኘትንና ሌሎች እንደ ልብስ  የመሳሰሉትን የሚያካትትና የሚያሟላ መሆን አለበት፡፡ እነዚህን ማሟላት የማይችል ለውጥ አይባልም። ለውጥ ሲባል ትናንሽና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ቋቋምና በማኑፋክቸር በመደገፍ ዝባዊ ወይም ራዊ ሀብት የሚዳብርበት ሁኔታ ሲፈጠር ነው። ይህ ይነቱ ሁኔታ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄድ መሆን አለበት። ውነተኛ ኢኮኖሚያዊና በራዊ ለውጥ ሊመጣ የሚችለው በኒዎሊበራል ኢኮኖሚ ፖሊሲ አማካይነት አይደለም፡፡ ዓይነተኛ ለውጥ ሊመጣ የሚችለው በመንግ የተደገፈ ሁለገብ ፖሊሲ ተግባራዊ ሲሆን ብቻ ነው። ስለሆነም ውነተኛ ለውጥ የውጭ ኃይሎችን ወይም የዓለም ኮሙኒቲውን ጣልቃ ገብነት የሚፃረር ነው። የመንግት መኪና ሙሉ በሙሉ ከመጨቆኛ መሣሪያነቱ ሲላቀቅና የዝብ አለኝታ የሆነ መንግታዊ መዋቅር ከተዘጋጀ ስለለውጥ ማውራት ይቻላል። ስለሆነም እንደዚህ ይነቱ መንግት ከውጭ ኃይሎች ተፅዕኖ ሙሉ በሙሉ የዳ ሊሆን ይችላል። ይህ ይነቱ አገዛዝ ፍትዊነትን በአገር አቀፍ ደረጃ የሚያበስር መሆን አለበት። ውነተኛ ለውጥ በግለሰብዊ ነፃነትና ተሳስቦ በመኖር የሚገለጽ ሲሆን፣ አርቲፊሻል የሆነ የብረሰብና የማንነት ጥያቄዎች ለመረታዊ ለውጥና ለልጣኔ ጠንቆች ናቸው። አንድ አገር ሁለንታዊ በሆነ መልክ እንዳያድግ የሚያግዱ ናቸው። የነፃነትን ብርሃን የሚያጨልሙ ናቸው።

ከነዚህ መረታዊ ሳቦች ስንነሳ ነው አንድ መት ያህል በአገራችን ምድር ለውጥ እየተካሄደ ነው የሚባለውን አነጋገር መመርመር ያለብን። በእርግጥ ዶጠቅላይ ሚኒስትር ዓብ አህመድ (ዶ/ር) ልጣን ከጨበጡ ጀምሮ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የፖለቲካ እስረኞች ለመፈታት ችለዋል። የእነዚህ ሰዎች መፈታት በዝብ ግፊትና ትግል፣ እንዲሁም በብዙ መስዋዕትነት የተገኘ ድል ነው። የአገዛዙ ቡራኬ አይደለም፡፡ አገዛዙም በድሮው መልኩ ሊቀጥል እንደማይችል የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ ስለሆነም ይህንን የመሳሰለውን የእስረኞችን መልቀቅና ሳብን የመግለጽ ነፃነት መፈቀዱ በዝብ ተጋድሎ የተገኙ ውጤቶች ናቸው። ይሁንና አጠቃላዩን የፖለቲካ ሁኔታ ስንመለከት በተለይም 28 መታት ያህል ዝብን ሲገድሉ፣ አገርን ሲያተራምሱ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት፣ ብረሰብን ከብረሰብ ጋር ሲያጋጩና የአገርን እሴት ባፈራረሱት ላይ ምንም ይነት ጋዊ ዕርምጃ አልተወሰደም። በተጨማሪም የመንግቱ መኪና ለጊዜው ብ እንዲል የተደረገ እንጂ ከመጨቆኛ ባህው በመላቀቅ ሞክራሲያዊ ባህ ሲላበስና የዝብ አለኝታ እንዲሆን ሲዋቀር አይታይም። ዝብን ሲገድሉና ሲያሰቃዩ የነበሩ አንዳንዶቹ ከነበሩበት ቦታ ወደ ሌላ በመቀየር በሌላ መልክ ራቸውን እየሩ እንደሆነም የምንገነዘበው ቅ ነው።

በብዙ አገሮች ውስጥ አርጀንቲና፣ ቺሌና ብራዚል ድረስ እነዚህ አገሮች ከወታደራዊ አገዛዞች ወደ ሲቪል አገዛዝ ቢሸጋገሩም እስካሁን ድረስ በትርምስ ዓለም ውስጥ የሚገኙበት ዋናው ምክንያት በመንግት መኪናውና በፖለቲካው አወቃቀር ላይ መረታዊ የሆነ መሻሻል ባለመታየቱ ነው። በብረተሰብ ታሪክ ውስጥ መንግታዊ አወቃቀር ነቀል በሆነ መልክ ባልተሻሻለበት ወይም ለውጥ ባልተደረገበትና ባልተካሄደበት አገር ሰፋ ያለ ብራዊ ኢኮኖሚ መገንባትና የባህልም ለውጥ ማምጣት እንደማይቻል የታወቀ ጉዳይ ነው። ‹‹ሳ መጠንባት የሚጀምረው ከራሱ ላይ ነው›› እንደሚባለው አነጋገር የፖለቲካና የመንግት ጥያቄ መረታዊ በሆነ መልክ እስካልተፈታ ድረስ የተወሳሰቡት የአገራችን ችግሮች በፍም ሊፈቱ አይችሉም። በሌላ ወገን ደግሞ የአገራችንን የመንግት መኪና አወቃቀር ስንመለከት በተለይም 1940ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ የተዋቀረው መንግታዊ መኪና ኢቮሊሽናዊ [ዝግመታዊ] በሆነ መልክ ከታች ወደ ላይ ከአገር ግንባታና ከዝብ ፍላጎት አንፃር በመታየት በተገለጸላቸው ሰዎች የተገነባ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ የውጭ ኃይሎች ተፅዕኖ ነበረበት። ስለሆነም ይህ ይነቱ መንግታዊ አውቃቀር ከፊዩዳላዊ ርዓቱ ጋር በመቀናጀት ለዕድገትና ለነፃነት እንቅፋት እንደሆነ ይታወቃል። ከዚህም ባሻገር ኢኮኖሚው ውስጠ ይሉ ደካማ ስለነበር አዳዲስና የተገለጸላቸው ኃይሎችንና ምሁራንን በማፍራት በመንግቱ መኪና ላይ ግፊት ማድረግ አይቻልም ነበር። በዚህም ምክንያት የተነሳ ነው የየካቲቱ አብዮት ሊከሽፍ የቻለው። በአንፃሩ ራሳቸውን ችለው ወደ ልጣን ላይ የመጡ ኃይሎች፣ እንደ ሶየት ብረትና ቻይና የመሳሰሉ አገሮች ውስጥ አብዮቱ ከሞላ ጎደል ሊሳካና እነዚህም አገሮች ወደ ኃያል መንግትነት ሊለወጡ የቻሉት የመንግቶቻቸውን መኪናዎች ደረ በደረጃ ዘመናዊ በማድረግ ወይም በመለወጣቸው ነው። በተጨማሪም የነዚህ አገሮች የመንግት ተቋማት በውጭ የስለላ ኃይሎች አልተተበተም። ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚደረበትና አንድ ሰው ለውጭ ኃይሎች ሰላይ በመሆን አገርንና መንግትን የሚበድል ራ ከራና ከተያዘ በሞት ይቀጣል። እጅ ከፍንጅ ካልተያዘ ደግሞ በልዩ ዘዴ ትክክል ተደርጎበት ይገደላል።

ከዚህ ሁኔታ ስንነሳ የዶ/ር ዓብይ አገዛዝ የመንግቱን መኪና ራዲካል በሆነ መንገድ ሊለውጥ የማይችልበት ሁኔታ አለ። በመጀመያ ደረጃ የውጭው ኃይል ግፊት አለ። የውጭው ኃይል በእንደዚህ ይነቱ ለዕድገት ጠንቅ በሆነ የመንግት መኪና አማካይነት ነው ድህነቱና የሰላም ጦቱ እንዲራዘም የሚያደርገው።  ምሁሩና ተቃዋሚ ኃይል ስለመንግት መኪናና ሞክራሲያዊ ባህሪ ስለመላበሱ ጉዳይ ይህንንም ያህል የተገለጸላቸው አይደሉም። የመንግት መኪና እንደ ታቦት የማይነካና የማይሻሻል ተደርጎ ነው የሚቆጠረው። ይህንን ትተን ወደ ኢኮኖሚ ጥያቄዎች ስንመጣ የዶ/ር ዓብይ አገዛዝ አሁንም ቢሆን ዝባችንን ካደኸየውና አገራችንን ካተራመሰው የኒዎሊበራል ኢኮኖሚ ፖሊሲ ለመላቀቅ አልቻለም። እኔ እስከሚገባኝ ድረስ ውነተኛ ብራዊ ሀብትን ሊፈጥር በሚችል የፖለቲካ ኢኮኖሚ ፖሊሲና ድህነትን በሚፈለፍል የኢኮኖሚ መከል ያለውን ልዩነት አገዛዙም ሆነ የፖሊሲ አውጭዎች የተረዱ አይመስለኝም። በሌላ ወገን ደግሞ የኢኮኖሚ ቲዎሪንና ፖሊሲን አስመልክቶ በአገራችን ምሁራን ዘንድ ምንም ይነት ውይይት አይካሄድም። የኢኮኖሚ ችግሮች በገበያ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ብቻ ነው ሊፈቱ የሚችለው የሚለው አስተሳሰብ በሁሉም ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘ ይመስላል። ስለሆነም የሚወራው ስለጂዲፒ ማደግና አለማደግ ነው እንጂ ድህነትን ስለመቅረፍና በምንስ ፖሊሲ አማካይነት ነው? ብራዊ ኢኮኖሚ መገንባት የሚቻለው በሚለው መረታዊ ጥያቄ ላይ ውይይት ሲካሄድ አይታይም። ምሁሩም ሆነ መንግዝቡ በማይገባው ቋንቋ ነው የሚያወሩት። ዝባችን ስለጂዲፒ ማደግና ስለዶር መጥፋትና አለመጥፋት ሳይሆን የሚያስበው እንዴት አድርጌ ከድህነት ልወጣ እችላለሁ? እያለ ነው ሌት ተቀን የሚያስበው። ልጆቼንና ራሴን ምን ነገር ነው የምመግበው? እያለ ነው የሚጨነቀው። የትስ አድራለ? ከቤቴስ ነገ እፈናቀላለሁ ወይ? በማለት ነው የሚያወጣውና የሚያወርደው። ስለሆነም የመንግት ዋና ተግባር ለዝብ በማይገባው ቋንቋ መናገርና በማይሆን ነገር ላይ መረባረብ ሳይሆን በቀላሉ ሊገባውና ችግሩን በሚያቃልልለት ጉዳይ ላይ ነው መረባረብ ያለበት።

ከዚህ ስንነሳ የአገዛዙ ግራ መጋባት ይህንን ያህልም የሚያስገርመን አይደለም። አገዛዙ በውጭ ኃይሎች ወይም ኤክስፐርቶች እየተመከረ የሚያካሂደው ፖሊሲና የመንግትን ሀብት ወደ ግል ማዘዋወር በመረቱ የሰፊውን ዝብ የድህነት ዘመኑን የሚያራዝም እንጂ የዝባችንን መረታዊ ችግሮች ሊፈታ የሚችል አይደለም። አብዮት ያካሄዱ አገሮችንና በመንግት ጣልቃ ገብነት አማካይነት መረታዊ ለውጥ የታየባቸውን አገሮች ሁኔታን ስንመለከት እነዚህ አገሮች በሙሉ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ አላካሄዱም። እንደ ቻይና የመሳሰሉት አገሮች ከኋላ መያዝ የሚለውን ስትራቴጂና በራስ መተማመን የሚለውን ፖሊሲ በመከተል ነው የኋላ ኋላ ለገበያ ኢኮኖሚ ለውጥ የሚሆኑ መረቶችን ሊዘጋጁ የቻሉት፡፡ ታውቆም ይሁን ሳይታወቅ በዚህ ይነቱ ሰፊውን ዝብ በማንቀሳቀስ ስትራቴጂና የኢንዱስትሪ ተከላ አማካይነት ነው ቻይና ከድህነትና ከረሃብ ልትላቀቅና ዛሬ ደግሞ ወደ ኃያል መንግትነት ለመሸጋገር የምታመራው፡፡ ቻይና እዚህ ይነት ደረጃ ልትደርስ የቻለው ሌሎች አገሮችን በመለመንና በዕዳ በመተብተብ ሳይሆን በራስ በመተማመን ብቻ ነው። የሰሜን ኮያም ዛሬ ባልስቲክ ሚሳይል መራት የቻለችው በቁጭትና በራስ በመተማመን ነው። አሜሪካኖች በከፈተቱ ጦርነት ወደ አራት ሚሊዮን የሚጠጋ ዝብ አልቋል። አገሪቱ እንዳለ ወድማ ነበር። ከዚህ አሳዛኝ ሁኔታ በመነሳት ነው የተወሳሰቡ ቴክኖሎጂዎችን መራት የቻለችው። በአብዮቱ ጊዜ የተሟላ የማሽን ኢንዱስትሪና የመሪያ ፋብሪካ ለኢትዮጵያችን ለግሳለች።  ጃፓንም ሆነ ጀርመን ቀደም ብለውም ሆነ ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት በኋላ ወደ ሁለገብ የአገር ግንባታና የቴክኖሎጂ ዕድገት መሸጋገር የቻሉት በተጠና የመንግት ጣልቃ ገብ የኢኮኖሚ ፖሊሲ አማካይነት ነው እንጂ በእነ ዓለም የገንዘብ ድርጅትና (IMF) በዓለም ባንክ በመከርና በውጭ መዋዕለ ንዋይ አማካይነት አይደለም። በአውሮፓ የካፒታሊስት ኢኮኖሚ ዕድገት ታሪክ ውስጥ እንግሊዝ፣ ፈረንይ፣ አሜሪካና ጀርመን በሌላ የውጭ ከረንሲ በመመካትና በመበደር አይደለም ሰፋ ያለ የኢኮኖሚ ዕድገት ሊጎናፉና ዓለምን ለመቆጣጠር የቻሉት። በዘመኑ ዶላርና ዩሮ የሌሎች አገሮችን ዕድገት አጨናጋፊ መሪያዎች ናቸው። ማታለያ መሪያዎች ናቸው። ውስጣዊ ዋጋ (Intrinsic Value) የላቸውም። በታሪክና በአገር ግንባታ ውስጥ በዕዳና በዕርዳታ ተመክቶ ያደገ አገር የለም። ታላላቅ ልጣኔዎች በሙሉ ዶላርና ዩሮ ከመፈጠራቸውና የዓለም ንግድ መገበያያ መሪያዎች ከመሆናቸው በፊት ተመርተዋል። ከተማዎች ካቴድራሎችና መስጊዶች እንዲሁም ቤተ መንግቶች ተገንብተዋል። የዕደ ጥበብ ራዎችና ንግድ በየአገሩ አብበዋል። እነዚህ ሁሉ የተገነቡትና ማደግ የቻሉት ቀስ በቀስ ማደግ ከጀመረው የውስጥ የ ክፍፍል ጋር ተያይዞ ካደገው የአገር ውስጥ ገንዘብ ጋር በመተሳሰር ነው። ስለሆነም ዶላርና ሮ የተዘበራረቀ ሁኔታ ከመፍጠርና ድህነትን ከማራዘም በስተቀር ርዓት ወዳለው ጥበባዊ ወደ ሆነ የአገር ግንባታ ሊሸጋገሩን በፍም አይችሉም።

የምዕራብ አውሮፓን፣ የጃፓንን፣ የደቡብ ኮያን፣ የሶየት ብረትን፣ ዛሬ ደግሞ የሩሲያን፣ የሲንጋፖርንና የአንዳንድ አገሮችን የተስተካከለና የተሟላ የኢኮኖሚ ዕድገት ፖሊሲ ስንመለከት ከታች ወደ ላይና ከላይ ወደ ታች በጣልቃ ገብ ፖሊስ አማካይነት ነው እዚህ ይነቱ ደረጃ ላይ ሊደርሱ የቻሉት። የጀርመንን ሁኔታ ስንመለከት ጀርመን ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት በኋላ ስኬታማ ውጤት ልታመጣ የቻለችው በመጀመያ ደረጃ መረታዊ የዝብ ፍላጎቶች ከተመለሱ በኋላ ነው። ሰፊውን ዝብ መንገድ ላይ እንዲጣል በማድረግና በጎጆ ቤት ውስጥ እንዲኖር በማድረግ አይደለም የአንድን አገር ኢኮኖሚ በጠንካራ መረት ላይ ሊገነባ የሚችለው። በአገራችንና በብዙ አፍሪካ አገሮች ውስጥ ያለው የአስተሳሰብ ግድፈት የኢኮኖሚ ጉዳይ ከዝብ ፍላጎት ጋር ለመያያዝ ባለመቻሉ ነው። የሚተከሉት ኢንዱስትሪዎችም ሆኑ ተግባራዊ የሚሆነውም የእርሻ ፖሊሲ የውጭ አገሮችን ፍላጎት ለማርካት እንጂ በተቀዳሚ የዝባቸውን ፍላጎት ለማርካት አይደለም። በዚህም ምክንያት የተነሳ አገዛዞች የፕላንቴሽን ኢኮኖሚ በማካሄድ ድህነቱና መዘበራረቁ እንዲራዘሙና ዝብም እንዲናቅ በማድረግ ላይ ናቸው። በተጨማሪም ሆቴል ቤቶችን በመራት ከፍተኛ ሀብት ይወድማል። አንድ አገር ወ አስረሽ ምችነት እንድትለወጥ ትደረጋለች። ይህ ማለት ግን ጊዜውን ጠብቆ እንደ አስፈላጊነቱ ሆቴል ቤቶች አይሩ ማለት አይደለም። ዝብን ሜዳና ቆሻሻ ውስጥ እየጣሉ ሆቴል ቤቶችን መራት ከፍተኛ ወንጀል ነው። የልጣኔና የዕድገት ምልክት ሳይሆን የኋላ ቀርነት ምልክት ነው። የዚህ ሁሉ ዋናው ችግር የአገራችን አገዛዞች ልጣን ሲይዙ በመጀመያ ደረጃ ዋናው ዓላማቸው ምን እንደሆነ አለመታወቁ ነው። በሁለተኛ ደረጃ፣ ለተወሳሰቡት ችግሮች መነሻዎቻቸው ምንድናቸው? በሚሉት ጉዳዮች ላይ ጥናት ስለማይካሄድ ነው። ስለሆነም የዶ/ር ዓብይ አገዛዝ ከተሳሳተ የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት (Macroeconomic Imbalances) በመነሳት ነው የአገራችንን የተወሳሰበ ችግር ለመፍታት የሚቃጣው፡፡ እንደሚታወቀው ይህ ይነቱ መዛባት የመሠረታዊ ኢኮኖሚው አወቃቀር (Strucctural Crises) ነፀብራቅ (Manisfestation) ነው እንጂ በራሱ ለቀውሱ ዋና ምክንያት አይደለም። የዓለም የገንዘብ ድርጅትና የዓለም ኮሙኒቲው የአንድን አገር የኢኮኖሚ አወቃቀር በተሳሳተ መልክ ነው የሚረዱትና የሚያነቡት፡፡ በአስተሳሰባቸው ውስጥ ብረተሰብዊ አወቃቀርና የፖለቲካ ኃይል ላለፍ (Social Formations and Political Power Relationships) የሚባል ነገር የለም። እነዚህ ነገሮች ድህነትን በመፈልፈልና ኋላ ቀርነትን በማፈርጠም የሚኖራቸውን ሚና በፍም አይገነዘቡም፡፡ ስለዚህም ድህነትና ኋላ ቀርነት ጉዳያቸው አይደለም፡፡ ስለሆነም የዓለም የገንዘብ ድርጅት የሚባለውና የዓለም ኮሙኒቲው አዳዲስ አገዛዞችን በማሳሳትና ጫና በማድረግ ቀውሱ ጥልቀት እንዲያገኝና የመፍቻ ዘዴም እንዳይገኝለት ያደርጋሉ። ይህን ይነቱን ፖሊሲ 60 መታት በላይ ተግባራዊ ሲያደርጉ የቆዩበትና የበላይነታቸውም መግለጫ ስለሆነ የግዴታ ድህነትና አጠቃላይ የሆነ የኢኮኖሚ ቀውስ እንዲፈጠር ያደርጋሉ። ስለሆነም አገዛዙ ከዚህ ይነቱ ድህነትን ፈልፋይ ከሆነ የኢኮኖሚ ፖሊሲ እስካልተላቀቀ ድረስ የኢትዮጵያ ዝብ ውነተኛ ነፃነቱን ሊቀዳጅ በፍም አይችልም።

በአጭሩ የዶ/ር ዓብይ አገዛዝ ከላይ የዘረዘርኳቸውን 13 መረተ ሳቦች ሊያሟላ የሚችል አገዛዝ አይደለም፡፡ ስለለውጥ ያለውም አስተሳሰብ የተዛነፈና ኢሳይንሳዊ ነው። የአገራችንን ብራዊ ነፃነት የሚያስከብርና ዝባችንም ውነተኛ ነፃነትን የማግኘት ኃይሉ እየመነመነ ይሄዳል ማለት ነው። ስለሆነም ነው የዶ/ር ዓብይ አገዛዝ በዓለም አቀፍ ኮሙኒቲው ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘውና ተስፋ የሚጣልበት አገዛዝ እየተባለ የሚወደሰውረታዊ ለውጥ ለማምጣት ደፍ ደፍ በማለቱና ድህነትን ለመጨረሻ ጊዜ ከአገራችን ምድር ለማስወገድ ባለው የተወሳሰበ ስትራቴጂ አይደለም የሚመገነው። መረታዊ ለውጥ የማምጣት ፍላጎት ያለው ኃይል ቢሆን ኖሮና ፍንጭም ቢያሳይ እንደ ታንዛኒያው ፕሬዚዳንት ጆን ማጉፉሊ ዘመቻና ዛቻ ይካሄድበት ነበር። ለማንኛውም በአገራችን ምድር መረታዊ ለውጥን ማምጣትና አለማምጣት መቻል በዶ/ር ዓብይ አገዛዝ ላይ ብቻ የሚሳበብ አይደለም። የዶ/ር ዓብይ አገዛዝ ከድሮዎች አገዛዞች በተለይም ከወያኔ አገዛዝ የወረሳቸው የተወሳሰቡ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማበራዊና ባህላዊ ቀውሶች አሉ። እነዚህ ቀውሶች ከአገዛዙ አቅም በላይ የሆኑ ብቻ ሳይሆኑ ሁላችንም ለዚህ ይነቱ አስቸጋሪ ሁኔታ የተዘጋጀን አይደለንም። ከመጮህና ከመተቸት በስተቀር አማራጭ የሆነ ሁለገብ ፖሊሲ አዘጋጅተን ማቅረብ አልቻልንም። አንዳንዶቻችን ከመንግቱ ጋር ተለጥፈን ዝም ብለን መጓዝን የመረጥን አለን። ሌሎች ደግሞ ከመተቸትና የማይሆን ጥያቄ ከማቅረ በስተቀር ያለውን ችግርና ምንጩን በመረዳት መሰረታዊ የሆነ መፍትሄ ሲያቀርቡ አይታይም። ይህም ማለት ያለው ድክመት በሁላችንም ዘንድ ነው። ስለዚህ ችግሩ ሁላችንን የሚመለከትና አዲስ አስተሳሰብ እንድናፈልቅና እንድናዳብር የሚጋብዘን ነው ማለት ነው። ከዚህ በመነሳት ሰሞኑን የተወረወሩ አንዳንድ ሳቦችን በመዳሰስ ጽፌን ለመደምደም እፈልጋለሁ።

ተስፋ የሚጣልበት ወይም የከሸፈ መንግ (Failed State)!

ሰሞኑን በሁለት ግዙፍ ምሁራንና የአገራችን ተቆርቋሪ ነን በሚሉ ሁለት ጽፎች ለንባብ ቀርበው በተለይም በውጭው ዓለም የምንኖረውን ኢትዮጵያዊያኖች ግራ አጋብተውናል፡፡ ሁለቱም ዶ/ር ዓብልጣን ላይ ከወጡ በኋላ አገር ቤት በመግባት አንዳንድ ቦታዎችን ያዩና በውይይትም ሆነ በጥናት የተሳተፉ ናቸው። አንደኛው የዶ/ር ዓብይን አገዛዝ የከሸፈ ነው ሲል፣ ሌላው ደግሞ ተስፋ የተጣለበትና በዓለም አቀፍ ኮሙኒቲውም ሆነ በታወቁ ጋዜጦች ተቀባይነትን ያገኘና የሚወደስ ወጣት መሪ ነው በማለት የጦፈ ክርክር ተካሂዷል። ሁለቱም አቅራቢዎች አስተያየታቸውን በቲዎሪም ሆነ በኢምፔሪካል ደረጃ ሳያረጋግጡና መቋጠሪያ ሳይገሩን ዘግተውታል። ሁለቱም ተቃራኒዎች የአሜሪካን ቲፎዞዎችና በአሜሪካ የበላይነት የሚያምኑ ናቸው። በመረቱ የሚያጣላቸው ነገር አልነበረም። ሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊዮርጊስና ፕሮፌሰር አል ማርያም በመባል የሚታወቁና ብዙ መጣጥፎችንም ለንባብ ያቀረቡና የሚያቀርቡም ናቸው።

ከሻለቃ ዳዊት እንነሳ። ሻለቃ ዳዊት ጥቂት ሳምንታት ኢትዮጵያ ውስጥ ከቆየ በኋላ ያየውንና ለማንበብ የቻለውን አሜሪካ ከተመለሰ በኋላ የዶ/ር ዓብይን አገዛዝ የከሸፈና ጥታንም ማስጠበቅ ያልቻለ መንግት ወይም አገዛዝ ነው በማለት ይከሰዋል። የላይ ላዩን ሲታይ ይህ ውንጀላ ትክክል ነው ብሎ መቀበል ይቻላል። ይሁንና ሻለቃ ዳዊት የዶ/ር ዓብይ አገዛዝ የከሸፈ አገዛዝ ነው ሲል ያላቸውና ለማየትም ያልቻላቸው አያሌ ጉዳዮች አሉ። አንድ መንግትና አገዛዝ ምን ምን ነገሮች ሲጎድሉት ነው የከሸፈ አገዛዝ የሚባለው? ምን ምን ነገሮች ሲሟሉ ነው ያልከሸፈስ ወይም የተሳካለት አገዛዝስ ተብሎ ሊወደስ የሚችለው? በተጨማሪም ይህ ሁኔታ እንዴት ሊከሰት ቻለ? ከመቅጽበት ወይስ እየተማቸ የመጣ? በአገዛዙ ብቻ የተፈጠረ ወይስ የውጭ ተፅዕኖ ያለበት? ሚሉትን መረታዊ ጥያቄዎች በማንሳት አላስተማረንም እንድንወያይም አላደረገንም። ለማንኛውም የሻለቃ ዳዊትን ጽፍ ላነበበ ሰውየው ንፁህ በንህ መልክ የሚሊታሪ ሰው እንደሆነና ከሚሊታሪ ሎጂክ አንፃር እንደተመለከተው መረዳት ይቻላል። ይህም ማለት አጻጻፉና አመለካከቱ እንዲሁም ግንዛቤው ለአንድ ብረተሰብ እንደ በረሰብ ለመያያዝና ለመጠንከር የሚያስፈልጉትን ሰፋ ያለና በሳይንስና በቴክኖሎጂ እንዲሁም በማኑፋክቸር ላይ የተመረተን አገር እንደ መነሻ ወይም እንደ መነፃፀሪያ አድርጎ በመውሰድ አይደለም ሊያስተምረን የተነሳው። በዚህም ምክንያት የተነሳ የሰውን ልጅ ምንነትና በተሟላ የነፃነት ዓለም ውስጥ መኖርን እንደ አስፈላጊና ይህም ጉዳይ የአንድ አገር መንግት መረታዊ ተግባር መሆኑን በመገንዘብ  አይደለም የአገዛዙን ድክመት የሚነግረን፡፡ ከዚህም በላይ ስለተቋማት አስፈላጊነት በፍም አላነሳም። በተቋማትና በብቃትነታቸው አማካይነት ብቻ ነው በአንድ አገር ውስጥ ሰፋ ያለ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ሊመጣ የሚችለውና መረጋጋትም የሚኖረው።

እንደሚታወቀው ወይም ደግሞ ምናልባት አንዳንዶቻችን ጥናት አድርገን እንደሆን የዛሬው አስቸጋሪ ሁኔታ ወይም የውድቀት ጉዳይ ዛሬውኑ በዶ/ር ዓብይ የአንድ መት አገዛዝ ዘመን ከመቅጽበት የተፈጠረ አይደለም። ጉዳዩ የብዙ መቶ መታት ታሪክ ያለው ሲሆን፣ የአገራችን አስቸጋሪ የብረተሰብ አወቃቀር ታሪክ ነፀብራቅ ነው ማለት ይቻላል። በተለይም የዛሬው ያልተሳካለት መንግት ጉዳይ መረቱ የተጣለው አፄ ኃይለ ላሴ ከስደት ከተመለሱና ልጣንን ከጨበጡ በኋላ ነው ማለት ይቻላል። በጊዜው የኢትዮጵያ መንግት መኪና ዘመናዊና ፊዩዳላዊ በሆኑ የአራር ዘዴዎች የሚገለጽ ነበር። ዘመናዊ የሚባለው በአዲስ አበባ ብቻ ላይ የተስፋፋ ሲሆን፣ በአብዛኛው ክፍለ ገሮች ውስጥ ዘመናዊ ተቋማት ያልነበሩና ሰፊው ዝብም ካለምንም አጋር የሚኖር ነበር ማለት ይቻላል። በአፄው የአገዛዝ ዘመን የነበረውን የአዲስ አበባንም ሁኔታ ስንመረምርም የተዘበራረቀና ተቋማትም ያልተሟሉ ነበሩ። የከተማው ዕቅድና የተቋማቱ ጉዳይ የተዘበራረቀው የኢኮኖሚ ነብራቆች ናቸው ማለት ይቻላል። ይህም ማለት የአፄው አገዛዝ 20ኛው ክፍለ ዘመን አንድ መንግት ለአገሩ ማድረግ የሚገባውን የኢኮኖሚ፣ የማበራዊ፣ የባህላዊ፣ የ ልቦናና ሌሎች ለአንድ ብረተሰብ የሚያስፈልጉ ተቋማትን መዘርጋት ያልቻለና ምንም ያልታየው ነበር። ከዚህ ሁኔታ ስንነሳ አንዳንድ የረም ጊዜ ታሪክ ያላቸው የእስያ አገሮች ካለፉት ርዓቶች በመማርና ሰፋ ያለ ተቋማትን በመዘርጋትና በየጊዜው የመሻሻልን አስፈላጊነት በመረዳት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ፣ በዚያው ዘመን የአፄው አገዛዝ ይመካ የነበረው ንህ በንህ በወታደሩና በጥታ ኃይሉ ብቻ ነበር። ወደ ገጠርና ወደ ክፍለ ገር ከተማዎችም ስንሄድ የተዘበራረቁ ሁኔታዎችና ፊዩዳላዊ ርዓቶች እንደነበሩ እንረዳለን። በዚህም ምክንያት የተነሳ የአፄው አገዛዝ የሰፊው ዝብ ጉዳይ የማያገባውና የአንድን መንግት መረታዊ ተግባሮች ያልተረዳ ነበር ማለት ይቻላል። በየጊዜው በተደጋጋሚ የተከሰተውን ረሃብና በገጠሮችና በአንዳንድ ከተማዎች የተስፋፋውን ድህነትና የሴተኛ አዳሪነት እንደ አሸን መፍለቅ ስንመለከት በጊዜው የአፄው መንግትም የከሸፈ መንግ (Failed State) ነው ብሎ መደምደም ይቻላል። የአፄው አገዛዝ ከፍተኛ የሆነ የርዕዮተ ዓለም ተቀባይነት ቢኖረውምና የሚመለክም አገዛዝ ቢሆንም አገዛዙና ሚኒስተሮቹ ከዝብ እርቀው የሚኖሩ ነበሩ። ሌላውን ትተን የኢኮኖሚና የእርሻ ሚኒስሮች በተለያዩ ቦታዎች በመዘዋወር የዝቡን አኗኗርና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችን የሚያጠኑና ምን ምን ነገሮች መደረግ እንዳለባቸው ጥናት እንዲደረግ ትዕዛዝ የሚሰጡና የሚከታተሉ አልነበሩም። ከዚህ አጭር ሀተታ ስንነሳ የኢትዮዝብ የራሱ የሆነ መንግትና አገዛዝ አልነበረውም። ዝም ብሎ ብቻ አንገቱን ደፍቶ የሚኖርና አምላክ ሆይ ደህና ቀን አምጣልኝ ብሎ የሚጸልይና የሚለምን ዝብ ነበር። እንደዚህ ይነቱን አገርና ዝብ ነው አፄውና አገዛዛቸው ጥለውልን የሄዱት።

ይህንን ጉዳይ አብዮቱ ከፈነዳ በኋላ ከሞላ ጎደል ለማረም አንዳንድ የጥገና ለውጦች በመወሰድ ተፎካካሪ የመንግት መዋቅሮች ተተክለው ነበር። ገበሬውና ራተኛው በሙያ ማበሩ መደራጀት፣ የቀበሌ ማበራት መቋቋምና የሴቶችና ወጣቶች መደራጀትና ሳባቸውን መግ ሰፊውን የገጠር ኗሪ ዝብ ለማስተማር የተደረገው ዘመቻና በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶች በገጠር ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ መሰራትና ቀስ በቀስ የፊዩዳሉ ርዓት መንኮታኮት የሚያረጋግጡት በጊዜው አገራችን ወደ ተሻለ ዘመናዊነት በመሽጋገር ላይ እንደነበረች ነው። ይህ ይነቱ ለውጥ በውስጥና በውጭ ኃይሎች የተቀነባበረ ሴራ ሊከሽፍና አገራችንም የጦር አውድማ ለመሆን በቅታለች። በዚህ ይነቱ አገርን የማፈራርስ ሴራ ውስጥ በጊዜው አንዳንድ ለአሜሪካ ያደሩ ወጣት መኮንኖችም ተሳትፈውበታል። ወያኔም እንዲገባ ሁኔታውን አመቻችተውለታል።

ከዚህ ስንነሳና እነ ወያኔ ልጣን ከያዙ በኋላ ተግባራዊ የሆነው የክልል አስተዳደር ለዘመናዊና ለተቀላጠፈ ተቋማት መቋቋም አመቺ ሁኔታ እንዳይፈጠር አግዷል። በየክልሉ ዋና ከተማዎች ምሁራዊ እንቅስቃሴ መዳበር አልቻለም። የየክልሉ አስተዳዳሪዎች ራሳቸውን ከማደለብና ሀብት ከመዝረፍ በስተቀር የ ክፍፍል እንዲዳብር ለማድረግ አልቻሉም። በአንፃሩ በተለይም በኦሮያ ክልል የተስፋፋው የአበባ ተከላ አካባቢውን ሊያደቀው ችሏል። ድህነትና ውድቀት ር ሊሰዱ ችለዋል። በአጭሩ ያልተገለጸላቸው የየክልሉ አስተዳዳሪዎች አካባቢዎቻቸውን ዘመናዊና የለጠነ ማድረግ አልቻሉም። ሰፋ ያለ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲዳብር ማድረግ አልቻሉም። የባህል ማዕከሎችም በማቋቋምና በተለይም ወጣቱን በማስተማር የዝቡ የማሰብ አድማስ እንዲሰፋና እንዲዳብር ለማድረግ አልቻሉም። ይህ ይነቱ ሁኔታ በሌለበት ደግሞ ተቋማትን መመረት አይቻልም። ተቋማት በሌሉበት ቦታ ደግሞ ዝቡ የሚመካበት ነገር ስለማይኖረው በቀላሉ ለአደጋ መጋለጡ የማይቀር ግዴታ ነው። ወጣቱም በሙያ ልጠናና በራ እስካልተወጠረ ድረስ በቀላሉ የልዩ ልዩ ነገሮች ሰለባ መሆኑ የማይቀር ጉዳይ ነው። ይህ በራሱ ደግሞ ለጽንፈኛ ኃይሎች አመቺ ሁኔታን ይፈጥርላቸዋል። በአጭሩ የዶ/ር ዓብይ አገዛዝ የከሸፈ ነው ወይም ማስተዳደር አልቻለም ስንል ይህ ሁኔታ እንዴት እንደተፈጠረ ደረጃ በደጃ ማጥናትና የተሻለ ሳብም መሰንዘር አለብን። ሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊዮርጊስ ነገሩን ከብዙ ሁኔታዎች አንፃር ሳይመለከትና ሳይመረምር የሰነዘረው አስተያየት ሳይንሳዊ ግንዛቤ የሚጎድለው ነው። አቀራረቡ አሳሳች ነው። ለአገር ተቆርቋሪ ነኝ ብሎ ለማስመሰል የተጻፈና በሰፊው እንዳናስብና ስሜታዊ እንድንሆን የሚጋብዘን ነው።

የፕሮፌሰር አል ማርያም አቀራረብ ደግሞ እንመልከት። ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረ ማርያምም እንደ ሻለቃ ዳዊት አንዳንድ ቦታዎችን ተመልክቷል። ከሻለቃ ዳዊት ይልቅ ፕሮፌሰር አልማርያም ከዶ/ር ዓብይ ጋር የጠበቀ ግንኙነት አለው። በዚህም የተነሳ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ከሻለቃው ለየት ባለ ሁኔታ እንዲመለከተው ተገዷል። በእሱ ምነትም የዶ/ር ዓብይ አገዛዝ የከሸፈ አገዛዝ ሊባል የሚችል አይደለም። ኢትዮጵያ በታሪኳ ውስጥ መልካም ራዕይ ባለውና በዓለም ኮሙኒቲው ዘንድ ተቀባይነትን ባገኘ ወጣት መሪ የምትመራ አገር ነች ብሎ የተቀበለና የሚያምን ነው። በዚህም ምክንያት የተነሳ በዓለም ላይ አሉ የሚባሉ ጋዜጦች ሁሉ ዶ/ር ዓብይን ያደንቁታል በማለት ለማረጋገጥ ሞክሯል። ለተቀሩትም የአፍሪካ አገዛዞች ምሳሌ ለመሆን የበቃና ተፅዕኖም ሊያሳድር የሚችል ነው የሚል ምነት አለው።

በመረቱ እንደዚህ ይነቱ አባባል ከአንድ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር የሚጠበቅ አጻጻፍ አይደለም። አንድ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁርና ብዙ መጽፎችን ያነበበ በሌሎች የሚመራና እነሱን እንደ ምስክርነት መውሰድ ያለበት ሳይሆን፣ በራሱ ህሊና የሚገዛ መሆን አለበት። በምድር ላይ የሚታዩትን ነገሮችና አገዛዙ ተግባራዊ ሊያደርጋቸው የሚፈልጋቸውን ፖሊሲዎች መመርመር አለበት። የአገዛዙን ርዕ ዓለም መመርመር አለበት። ከዚህም በመነሳት የሚታዩትን ችግሮች በምን ይነት የኢኮኖሚ ፖሊሲ ለመቅረፍ እንደተነሳ ማጥናት አለበት። በአጠቃላይ ሲታይ ብራዊ አጀንዳውንና ራዕዩን ማጥናት አለበት። ከዚያ በኋላ የራሱን ግምገማ መስጠት ይችላል። ይህንን ሳያደርግ የዝምላችሁ ተቀበሉ አጻጻፍ የአምባገነንነትን ባህ ያሳያል። እኔ ምሁር ስለሆንኩ ከእኔ በላይ ማንም የሚያውቅና ፍርድም የሚሰጥ ስለሌለ ሁላችሁም አፋችሁን ዝጉ የሚል አጻጻፍ ነው ፕሮፌሰሩ ያስነበበን። ያም ተባለ ይህ፣ የፕሮፌሰሩ ዋና ድክመት አንድን መሪ እንደ ሙሴ ማየቱ ነው። እሱ ብቻ ነው ችግሩን መፍታት የሚችለው ብሎ ማመኑ ነው። በሌላ ወገን ግን ፕሮፌሰሩ የአገራችንን ሁኔታ ወረድ ብሎ በየቆሻሻ ቦታዎች ያሉትን ሁኔታዎች እየተዘዋወረ ቢያጠናና እዚያው አንድ ሁለት ቀን ቢያድር ኖሮ ምናልባት የችግሩን ውስብስብነት ሊገነዘበው በቻለ ነበር። ቤተ መንግት ገብቶና አድሮ ሲወየሚኖር አስተያየት ሁል ጊዜ ሚዛናዊ ፍርድ ለመስጠት ያስቸግራል፡፡ የወያኔ አፍቃሪ ፈረንጆችም አዲስ አበባ ሄደው አገዛዙ ራተንና ሌሎች ዘመናዊ ሆቴል ቤቶች ውስጥ ጋብዟቸው ሲመለሱና የኢትዮጵያን ሁኔታ ሲጠየቁ ይሰጡን የነበረው መልስ አገሪቱ በጣም ተለውጣለች፤ ድህነትም በጣም ቀንሷል በማለት ነበር፡፡ በዚህ መልክ አብዛኛው ዝብ በድህነት ዓለም ቢኖርም አንዳንድ ሰዎች ከራሳቸው ምቹ ሁኔታና አቀባበል በመነሳት ሌላውም ሰው እንደ እነሱ ተመችቶትና ተደስቶ የሚኖር ይመስላቸዋል።

በአጭሩ የሁለቱን ምሁሮች አቀራረብ ስንመለከት አጻጻፋቸው ሶፊስቲያዊ ነው። ኃይል ያለው ትክክል (Might is Right) ነው የሚለውን የአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝምን የአመጽ ፖለቲካ የሚያንፀባርቁ ናቸው። አስተሳሰባቸው በእሱ ሎጂክ ውስጥ የተዋቀረ ነው። ወደ ውስጥ በመግባት በአገራችን ውስጥ የተፈጠረውን አስቸጋሪ ሁኔታ በመቃኘት አይደለም ሁለቱም ምሁሮች ብሶታቸውንና ደስታቸውን የሚጽፉልን። ሁለቱም የአገራችንን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማበራዊና የባህል ዕድገትና አወቃቀር በዲያሌክቲካዊ መነጽር በማየት የዛሬው ሁኔታ እንዴት ሊፈጠር እንደቻለ ሊስረዱን በፍም አልቻሉም። እንደ ሌሎች አብዛኛዎች የአፍሪካ አገሮችም ኢትዮጵያም የግሎባል ካታሊዝም መስዋዕት መሆኗን የተገነዘቡ አይደሉም። ስለ ዓለም አቀፍ የፖለቲካ፣ የሚሊታሪና የኢኮኖሚ አወቃቀር ያላቸው አስተያየት ግልጽ አይደለም። በተለያየ ጊዜ ልጣንን የተቀዳጁ አገዛዞች በኢምፔሪያሊዝምንና በግሎባል ካፒታሊዝም ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ሚሊታሪያዊ አወቃቀር ውስጥ በመካተት እንደሚታሹና ዝቦቻቸውም የድህነት ሰለባ እንደሆኑ በፍም የተገነዘቡ አይመስልም። ይህንንና የአገራችንን አስቸጋሪ የብረተሰብ ታሪክ ደት ነው ሻለቃ ዳዊትም ሆነ ፕሮፌሰር ገብረ ማርያም ሊመለከቱና ሊገነዘቡ ያልቻሉት፡፡ የአንድን አገር ተጨባጭና የፖለቲካ ሁኔታ በሳይንስና በንድፈ ሳብ በመደገፍ መተንተን ካልቻልን የግዴታ የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ ነው የምንደርሰው፡፡

መደምደሚያ

የአገራችን ሁኔታ በጣም አስቸጋሪ ነው። ድክመቱ የሁላችንም ነው። ዛሬ የምናየው የተወሳሰበ ችግር እየተደራረበ የመጣ ነው። በተለያዩ ጊዜያት አገራችንን ይገዙ የነበሩ ኃይሎች ተግባራዊ ያደረጓቸው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች በሙሉ ዝባችንን የሚያስተሳስሩ አልነበሩም። የሳይንስንና የቴክኖሎጂን፣ የተቋማትን መገንባት፣ የከተማዎችን ጥበባዊ በሆነ መልክ መራት፣ የ ክፍፍል መዳበርና በተለያዩ የኢኮኖሚ መስኮች መከል መተሳሰር ያለባቸው መሆናቸውን ለመገንዘብ ባለመቻላቸው አገራችንና ዝባችንን አዝረክርከውና አድክመው ሄደዋል። የብራዊ ውርደት አከናንበውናል። ሰፋ ያለና በራሱ የሚተማመን ምሁራዊ ኃይል እንዳይዳብርና የዝባችንና የአገራችን አለኝታ እንዳይሆን ለማድረግ በቅተዋል። አገዛዞቻችን በራሳቸው ዓለምና ለራሳቸው የሚኖሩ እንጂ ከዝባቸው ጋር የሚያስተሳስራቸው አንዳችም ነር አልነበረም። ስለሆነም ዝባችንን አደንቁረውና በውስጥ ኃይሎች እንድንቦረቦርና እንድንዳከም አድርገውን ሄደዋል። ይህ በራሱ ደግሞ ለዚህኛው ወይም ለዚያኛው የውስጥ ኃይል የመንቀሳቀሻ መድረክ በመፍጠር ከውስጥ ጦርነት አውጀውብናል። ብራዊ ስሜት እንዳይዳብርና በአንድነት ተነስተን ጠንካራ አገር እንዳንመርት ተደርገናል። ከዚህ ስንነሳ ሁኔታውን በሌላ የምሁራዊ መነር መመልከትና መመርመር ያለብን ይመስለኛል። አገር ልትፈርስ ነው እያሉ መጮኽ በራሱ የሚያመጣው ጥቅም ምንም ነገር የለም። ጭንቅላታችንን በአዲስ ምሁራዊ አስተሳሰብ እስካላነንና እስካላደስን ድረስ የአገራችን ሁኔታ ከመቶ ዓመት በኋላም በዚህ መልክ መቀጠሉ የማይቀር የታሪክ ግዴታ ነው። አሁን ባለን አመለካከትና ጩኸት ለዝባችንና ለአገራችን ፋይዳ ያለው ነገር ልንራ አንችልም። የጨለማውንና የድነቱን ዘመን ከማራዘም በስተቀር አዲስ ኢትዮጵያን ልንገነባና ለመው ትውልድ ማስተላለፍ አንችልም።

ዋናው አስቸጋሪ ነገር በሁላችንም ዘንድ ያለው እጅግ ወደ ኋላ ቀር አስተሳሰብ  ነው። ጭንቅላታችንን በኋላ ቀር አስተሳሰብ በመወጠሩ የተነሳ የነገሮችን ዕድገትና ውስብስብነት እንዳናይ ተገደናል። በዚህ ላይ ያልተገለጸላቸውና ፊዳላዊ የሆኑ ኃይሎችና አክቲቪስቶች የፖለቲካውን መድረክ በመያዛቸው በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠርን ዝብንና ወጣትን እያታለሉ ነው። የፖለቲካው ሜዳ ሁሉም እንደፈለገው የሚዋኝበት ሆኗል። ሁሉም ለአገር ተቆርቋሪ ነኝ ባይ ነው። እዚያው በዚያው ደግሞ የውጭ ኃይሎችን የሚማጽን ነው። የርዕዮተ ዓለም ጥራት የሌለውና አገራችን በምን ምን መሪያዎች መገንባት እንዳለባት የተገለጸለት አይደለም። በዚህ ይነት ሁኔታ ውስጥ ግልጽ አስተዋጽኦ ማበርከት በፍም አይቻልም። ደቀ መዝሙሮችን ማፍራትም አይቻልም። በተለይም በውጭ ኃይሎች የሚደገፉትንና የሚንቀሳቅሱትን መቋቋም በፍም አይቻልም። እነዚህ ኃይሎች ህልማቸው የውጭ ኃይሎችን ጥቅም ማስጠበቅ ስለሆነ በአገራችን ምድር ውነተኛ ነፃነትና ብልጽግና እንዳይመጣ አጥብቀው የሚታገሉ ናቸው። በዚህ ይነት ያልተስተካከለ ትግል ውስጥና፣ አብዛኛው ደግሞ ከዕውቀት ይልቅ የላይ ላዩን የሚጋልብ ከሆነ ስለ አገርና አንድነት መጠበቅ ማውራት በፍም አይቻልም። ጥያቄው ይህንን ሁኔታ እንዴት መስበር ይቻላል? ነው። ስለነም ለዚህ መልስ መፈለግ ያለብን ይመስለኛል። መልካም ግንዛቤ!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_imgspot_img
- Advertisment -

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

Related Articles