Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ሴቶችን ተጠቃሚ በማድረግ ተሻሻለ

የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ሴቶችን ተጠቃሚ በማድረግ ተሻሻለ

ቀን:

ላለፉት 15 ዓመታት በሥራ ላይ የነበረው የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/96፣ አካል ጉዳተኞችንና ሴቶችን ተጠቃሚ አድርጎ ተሻሻለ፡፡ 

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 27 ቀን 2011 ዓ.ም. ባደረገው አራተኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 47ኛ መደበኛና ዘጠነኛ ልዩ ስብሰባው ያሻሻለው የሠራተኛና አሠሪ አዋጅ፣ ስድስት አንቀጾችን ማሻሻሉም ታውቋል፡፡

በአሠሪና ሠራተኛ መካከል ያለውን ግንኙነት በማጠናከርና ምርታማነትን እንዲጨምር ማሻሻሉ ተገቢ መሆኑ የተገለጸው ይኸው አዋጅ፣ በተለይ በነፍሰ ጡር የወሊድ ፈቃድ አሰጣጥ ላይ የምክር ቤቱ አባላት ሰፊ ውይይት አድርገውበታል፡፡

በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንዲት ነፍሰ ጡር ሴት ከምትወልድበት ቀን ቀደም ብሎ አንድ ወር፣ የሥራ ቀናት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ እንድትወስድ ይደነግጋል፡፡ ከወለደች በኋላ 60 የሥራ ቀናት ወይም የሁለት ወራት የድህረ ወሊድ ፈቃድ አንዲሰጣት ይደነግግ ነበር፡፡

በተሻሻለው የድንጋጌ አንቀጽ ድኅረ ወሊድ ወደ ዘጠና ቀናት ወይም ሦስት ወራት ከፍ እንዲል ተደርጓል፡፡ ከምትወልድበት ቀን በፊት የነበረው 30 የሥራ ቀናት ግን እንደነበር ፀንቷል፡፡

ከድኅረ ወሊድ በኋላ እንዲጨመር የተደረገው፣ ‹‹90 የሥራ ቀናት›› እንዲባል ክርክር ተደርጎበት ነበር፡፡ በመሆኑም የተጠየቀው አንቀጽ ፋብሪካዎችና የመንግሥት ያልሆኑ ተቋማት ቅዳሜና እሑድ፣ እንዲሁም የበዓል ቀናት ሥራ ስለሚሠሩ፣ በእነዚህ ተቋማት የሚሠሩ ሴቶችን እኩል ተጠቃሚ ስለማያደርግና ወጥ የሆነ አሠራር ለመዘርጋት ሲባል ‹‹ለ90 ተከታታይ ቀናት›› የሚለው ሐረግ መወሰዱ ተገልጿል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...