- Advertisement -

ኢሰመጉ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን አስታወቀ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከአንድ ዓመት በፊት ሥልጣን መያዛቸውን ተከትሎ ከሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አንፃር ተጀምሮ የነበረው ተስፋ ሰጪ ዕርምጃ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሲሸረሸር ቆይቶ ሁኔታው አሁን ላይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) አስታወቀ፡፡

ጉባዔው ይህን ሥጋቱን የገለጸው ሐሙስ ሐምሌ 11 ቀን 2011 ዓ.ም. በዋና ጽሕፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሆን፣ በመግለጫውም ወቅታዊ የአገሪቱን ሁኔታ ከሰብዓዊ መብቶች አንፃር መገምገሙን አስታውቋል፡፡

በዚህም መሠረት ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በባህር ዳርና በአዲስ አበባ በአማራ ክልልና ከፍተኛ አመራሮችና በወታደራዊ ሹማምንት ላይ ግድያ ከተፈጸመ በኋላ፣ በመንግሥት እየተወሰዱ ባሉት ዕርምጃዎች ቅሬታውን ገልጿል፡፡

 ‹‹ከለውጡ በፊት የነበረውን የጭቆናና የአፈና ሥርዓት በሚያስታውስ መልኩ መንግሥት በተለይ ድርጊቱ በተፈጸሙባቸው ከተሞች እየተወሰደ ያለው መጠነ ሰፊ እስራት፣ እየታየ ያለውን ተስፋ የሚያደበዝዝ ተግባር ነው፤›› ሲል ክስተቱን ተከትሎ ያሉ መጠነ ሰፊ እስራቶችን ኮንኗል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የእስራት ዘመቻው የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችንና አባላትን፣ እንዲሁም በመንግሥት ላይ ጠንካራ ጥያቄዎችን የሚያነሱ ግለሰቦችን ማካተቱ የለውጥ ሒደቱን ወደኋላ እንዳያጓትተው የሚል ሥጋት እንዳለው ኢሰማጉ አስታውቋል፡፡

‹‹በተለይም የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)፣ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) እና የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት በመባል የሚታወቀው ስብስብ አባላትና ደጋፊዎች ናቸው በተባሉ ግለሰቦች ላይ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተፈጸሙ እስራቶች፣ ከፖለቲካ ተሳትፏቸውና ከሚያራምዱት አስተሳሰብ ጋር ተጣምሮ ሲታዩ እያስከተሉ ያለው ተፅዕኖ በፖለቲካ ፓርቲዎቹና በአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤቱ ላይ ብቻ ሳይሆን፣ አገራችን በጀመረችው አጠቃላይ የለውጥ ሒደት ላይ መሆኑ በእጅጉ አሳሳቢ ያደርገዋል፤›› በማለት ሥጋቱን አብራርቷል፡፡

- Advertisement -

የሲዳማ የክልልነት ጥያቄን በተመለከተ ደግሞ፣ ‹‹መንግሥት፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ እንዲሁም ጥያቄውን የሚያስተባብሩ አካላትና ምሁራን በፍጥነት የጋራ መፍትሔ በመፈለግ የደኅንነት ሥጋቱን እንዲያቃልሉ ወይም ዳግመኛ እንዲህ ዓይነቱ የደኅንነት ሥጋት እንዳይፈጠር፣ እንዲሁም ጥያቄው በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ ብቻ እንዲፈታ፤›› ሲል ጥያቄውን አቅርቧል፡፡

በቅርቡ ከወጡት የገዥው ፓርቲ አባል ፓርቲዎች መግለጫ ጋር በተያያዘም፣ ‹‹ሕወሓትና አዴፓ በቅርቡ በየበኩላቸው የሰጧቸው መግለጫዎች በፓርቲዎቹ መካከል ያሉትን ልዩነቶች ወደ ቃላት ጦርነት ከፍ ማለቱን የሚያሳዩ ከመሆኑም በላይ፣ በክልሎቹ መስተዳድሮች መካከል ባለፈው አንድ ዓመት የታየውን የመገዳደር ሥርዓት ወደ ግጭት እንዳያመራ ያሠጋል፤›› በማለት ሁኔታውን ገልጾታል፡፡

‹‹ሁለቱ ድርጅቶች በሰላማዊና በሠለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ችግሮቻቸውን እንዲፈቱ፣ በከረሩ መግለጫዎቻቸው የሁለቱን እህትማማች ሕዝቦች ወደ ግጭት እንዳይገፉ፣ መንግሥት ፓርቲዎቹ ችግሮቻቸውን በሰላማዊ መንገድ የሚፈቱበትን መንገድ እንዲያመቻችና የክልሎቹንም ሆነ የመላው የአገሪቱን ነዋሪዎች ደኅንነት የማስጠበቅ ሥራውን ይወጣ፤›› በማለት ጥሪ አቅርቧል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች የኢትዮጵያ ሕዝብ ወደ ቀዬአችን እንድንመለስ ድምፅ ይሁነን ሲሉ ጠየቁ

ከሰኞ ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለሦስት ቀናት የተቃውሞ ሠልፍ በመቀሌ ከተማ እያካሄዱ ያሉት የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፅ እንዲሆናቸው ጠየቁ፡፡ በፕሪቶሪያ...

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በታጣቂዎችና ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተክል ዞን ቡለን ከተማ፣ በሸኔ ታጣቂዎችና በክልሉ ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰው ሕይወት መጥፋቱ ተሰማ፡፡ የክልሉ ነዋሪዎች ‹‹የሸኔ ኃይሎች›› በማለት ወደ የጠሯቸው...

መንግሥትና ታጣቂዎች በየትኛውም ቦታና ሰዓት ለመነጋገር ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን አሜሪካ አስታወቀች

የሲቪክ ምኅዳሩ ሊጠበቅና ሚዲያዎች በነፃነት ሊሠሩ ይገባል ተብሏል ‹‹በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች መንግሥትና ታጣቂዎች ገንቢ በሆነ መንገድ በየትኛውም ቦታና ጊዜ ሰላማዊ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ...

መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ገንብቻለሁ አለ

የንብረት ታክስ አዋጅ እምብዛም ማስተካከያ ሳይደረግበት መፅደቁ ቅሬታ ፈጥሯል መንግሥት ኢሕአዴግ መንግሥት ሆኖ አገሪቷን ሲያስተዳድር ለ14 ዓመታት (ከ1996 እስከ 2010 ዓ.ም.) በአገሪቱ ከገነባቸው ኮንዶሚኒየም የጋራ...

በነዳጅ ማደያዎች የቴሌብር ወኪሎች እንዲነሱ ትዕዛዝ ተላለፈ

በዮናታን ዮሴፍ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በሁሉም የነዳጅ ማደያዎች ሲሠሩ የነበሩ የቴሌብርም ሆነ የማደያ ወኪሎች እንዲነሱ ሲል የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ለሁሉም የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች፣ ለኢትዮ ቴሌኮምና...

አዳዲስ ጽሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው ሥራ አስፈጻሚ። ምን ገጥሟችሁ ነው የተሰበሰባችሁት? ለመረጠን ሕዝብ ቃል የገባናቸውን ተግባራት አፈጻጸም የምንገመግምበት የተለመደ ስብሰባ ነው። የገባችሁት ቃል...

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

ባንኮች እየፈጸሙት ያለው አቅርቦትንና ፍላጎትን ያላገናዘበ የውጭ ምንዛሪ ግዥ

የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ ዋጋ እንዲገበይ የወጣው ሕግ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ከሰባት ወራት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ሕጉ ተግባራዊ በተደረገበት የመጀመርያው ቀን የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ...

አሳረኛው ኑሮ!

የዛሬው ጉዞ ከቦሌ ወደ ፒያሳ ይሆን ዘንድ ግድ ሆኗል፡፡ ለምን? በኑሮ  ምክንያት፡፡ የታክሲ መሠለፊያው ወሬ የነዳጅ ጭማሪውን ተከትሎ ስለሚመጣው ተጨማሪ ታሪፍ ነው፡፡ ‹‹የእኛ ኑሮ...

የግለሰቦች ለመብታቸው ኃላፊነት አለመውሰድ ለአገር ያለው አደጋ

በያሬድ ኃይለመስቀል አንድ የማከብረው ኢኮኖሚስት አንድ መጽሐፍ እንዳነብ መራኝና ማንበብ ጀመርኩኝ። ይህንን መጽሐፍ ሳነበው ከዋናው ሐሳብ ወጣ ብሎ ስለ “የነፃ ተጓዦች ሀተታ” (The Free Rider...

‹‹የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበራትን ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ማጠናከር ያስፈልጋል›› አቶ ፍፁም አብርሃ፣ የአሚጎስ ብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ

አሚጎስ የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር ከተመሠረተ አሥራ ሁለት ዓመታት ሆኖታል፡፡ በእነዚህ ዓመታት 8,500 አባላትን ማፍራት ችሏል፡፡ አሚጎስ ስለተመሠረተበት ዓላማ፣ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ተግባራት፣ የብድርና...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን