Wednesday, December 6, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ልናገርየኢኮኖሚ ፖሊሲውን ካስተካከልን እኛው እንችላለን!

የኢኮኖሚ ፖሊሲውን ካስተካከልን እኛው እንችላለን!

ቀን:

በኪሩቤል ፍሬሰንበት

በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ድሜው ለራ የደረሰና ኮኖሚውን የሚያንቀሳቅስ ወይም የማንቀሳቀስ ድርሻውን መወጣት የሚችለውን ይል እንየ የኮኖሚ አቅሙ በስት መክፈል ይቻላል፡፡ የመጀመያው በአንራዊነት በከፍተኛ የገንዘብ አቅም የሚንቀሳቀስ ባለብት፣ ሁለተኛው በመካከለኛ የገንዘብ አቅም በግል የራ ፈጠራ ተማርቶ ወይም በራሱ ጥረት ከዝቅተኛው የማበረሰቡ ክፍል በተሻለ ብቃት ላይ የሚገኝ መጠነኛ ገቢ ያለውን ሲሆን ስተኛውና የመጨረሻው ክፍል ደግሞ በዝቅተኛ የገንዘብ አቅም የሚራ ወይም በራ አጥነት የሚገኝ ያህል ነው፡፡

ኢትዮጵያ ከንጉርዓት ወደ ወታደራዊ ርዓት ስትሸጋገር በወቅቱ የነበረው መንግት ከላይ የሚገኘውንና በአንራዊነት በከፍተኛ የገንዘብ አቅም የሚንቀሳቀሰውን ይል በኢፔሪያሊስት፣ በበዝባዥነትና በፊውዳልነት በመፈረጅ የመደምሰስ መንገድ መከተሉ አጠቃላይ ከነበረው የማያባራ ጦርነት ጋር ተደማምሮ ኢኮኖሚውን ወደ ማንቀላፋት አሸጋግሮት  ነበር፡፡ ይህ በራሱ ጥረት ብት ያፈራውንና የሚያፈራውን ሁሉ በጅምላ (Categorically) በበዝባዥነት የመፈረጅ አስተሳሰብ አሁንም ተፅዕኖው በልጣን ላይ ባለው ትውልድ ይታያል፡፡ ከወደራዊው መንግት መውደቅ በኋላ የተተካው ርዓት ወደመጀመያው የልጣን ዘመን አካባቢ፣ ከሶሻሊስነት በፈጣን አክሮባት ወደ ካፒታሊስትነት ተገልብጦ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ያለው ኢንቨስተር ከውጭ የመሳብ ፍላጎት ላይ ተጠምዶ የቆየ ቢሆንምልጣን ዘመኑ እየገፋ ሲሄድ በተለይም ከምርጫ 97 በኋላ ለልጣኑ ፈተና ሲሆንበት ራ አጡንና ዝቅተኛውን የማበረሰብ ክፍል ላይ ለማተኮር ሞክሯል፡ አሁንም ሲሞክር ይታያል፡፡ ከሶሻሊስትነት ወደ ካፒታሊስትነት ያደረገው ለውጥም ለውጭ ኢንስተሮችና ለፖለቲካው ታማኝ ለሆኑ የራሱ የፖለቲካ ደጋፊ መደብ እንጂ ለሌላው ሲተርፍ አልታየም፡፡ ይህ በውጭ ባለሀብቶችና በፖለቲካ ታማኞች ላይ የተንጠለጠለ የኢኮኖሚ ፖሊሲ አሁን ላለንበት ውስብስብ ችግር ዳርጎናል፡፡

ባልተጠናከረ የመል መደብ ኢኮኖሚ ያለበት ገር ላይ በጥቂት ከፍተኛ የውጭ ኢንቨስተሮችና የፖለቲካ ታማኞች ብቻ የገርን ኮኖሚ ለማንቀሳቀስ ማሰብ ተኩላን ዶሮ ጠባቂ ለማድረግ እንደ መሞከር ያለ የቂል ተግባር ነበር፡፡ በተግባርም ኢትዮጵያ ውስጥ የሆነው ይ ነው፡፡ “ኢንቨስተሮቹ” እና የፖለቲካ “ታማኞቹ” ያለ ርህራ ለነገ እንኳን ሳይሉ ያገኙትን የዘረፉት የተኩላነት ባህሪ ስላላቸው ነው፡፤

በዚህ ወቅት ካለው የፖለቲካ ትኩሳት አንር የጽላማ ለተንኮል ፖለቲካ እንዳይውል የፖለቲካ “ታማኞቹን” ለጊዜው እንተውና ለዚህ የተኩላነት ባህሪህ  እንደ ማሳያ ሊሆን የሚችሉት የካሬቱሪ ኩባንያ ይነት ኢንቨስተሮች ናቸው፡፡ አብዛኛዎቹ የውጭ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያውያን የማይሰጥ ድልና እንክብካቤ ተደርጎላቸው የፕሮጀክት ዋጋን እንሻቸው በተጋነነ ዋጋ በማስገመትና 30 በመቶ የኢንቨስትመንት ድርሻ ከውጭ ይዘው የመጡ በማስመሰል (ለዚህ የማጭበርበር ድርጊት በተዘዋዋሪ መንገድ የመጡበት ሮች ኤክዚም ባንኮች ድጋፍ ያደርጋሉ)  ፕሮጀክቱን ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ  የ”ሰባ በመቶ”  ፋይናንስ ብድር ተብሎ በሚወጣ ገንዘብ ፕሮጅክቱን መቶ ከመቶ ከመራት አልፎ ፕሮጀክቱ ራ ሳይጀምር ይዘው መጡ የተባለውን የ30 በመቶ ድርሻ በካፒታል ቃዎች ግ በው ምንዛ ወደ ገራቸው ስደው ፕሮጀክቱ ሳይጀመር በትክክል ካወጡት ገንዘብ 233 በመቶ ወይም የተጣራ 133 በመቶ የሚደርስ ትርፍ ከባንኩ ካዝና ከመመዝበርይህ ምዝበራ ተመልካችና ጠያቂ እንዳይኖረው ከኢትዮጵያ ባንክ የወጣ ገንዘብ ተመልሶ ለኢትዮጵያ ባለልጣናትን ኪስ መሙላቱ የአደባባይ ሚስጥር ነው (የ133 በመቶ ቅድሚያ ትርፍ ቸር ሆነው ፕሮጀክቱን በእጥፍ ብቻ በተጋነነ ዋጋ ካስገመቱት ነው፡፡ አራት አምስት እጥፍ ካስገመቱ ፕሮጅከቱ ሳይጀመር ያላቸው ትርፍ 700 እስከ 800 በመቶ ሊደስ ይችላል)፡፡ ካሩቱ የኢትዮጵያን ደን በኢትዮጵያውያን አስመንጥሮ ከል አክስሎ ለኢትዮጵያውያን ከሸጠ በኋላ፣ የገርን መሬት ለራሱ ለባለ ገሩ ባንኮች አስይዞ ተበድሮ መጥፋቱ  የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡ እዚህ ላይ ከል አከልክ ደን መነጠርክ  ተብሎ የታሰረውንና የተቀጣውን ኢትዮጵያዊ ማሰብ ነገሩን የበለጠ አሳዛኝ ያደገዋል፡፡

በዚህ መንገድ የሚመጣ ኢንቨስተር ከራሱ ኪስ ያወጣው መዋጮ ባለመኖሩና ራው ሳይጀመር ከበቂ በላይ ትርፍ ስለሚያገኝ ነው “ኢንቨስተሩ“ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ጨርቄን ማቄን ሳይል ያለ ማቅማማት ገር ለቀው ውልቅ የሚለው፡፡ ባለቤቱ ‹‹የውጭ ኢንቨስተር ነበር የተበደረውን ዳ ሳይከፍል ከአገር ኮበለለ፤›› የሚባለውም ዜናም የሚበዛው ለዚህም ነው፡፡ ከልማት ባንክ ራጅ እንደሚወጣበት እየተነገረ ተጨማሪ ኢንቨስት አደርጋለው የሚል ኢንቨስተርም የምንሰማው ለዚህ ነው፡፡ በአጠቃላይ የውጭ ኢንቨስተሮች ራ የለበሰውን ሸሚዝ አስወልቆ መልሶ ለባለ ሸሚዙ መልሶ የመሸጥና በባለ ዙ እንደ ባለውለታ የመቆጠር ይነት ከፍተኛ የማጭበርበር ራ ነው፡፡ በተለይም በእርሻ ኢንቨስትመንት የተማሩ የውጭ ባለብቶች የኢትዮጵያን መሬት አስይዘው ከኢትዮጵያ ባንኮች በተበደሩት ገንዘብ የኢትዮጵያን መሬት በኢትዮጵያውያን በማሳረስ መልሰያመረቱትን ሰብል  ለኢትዮጵያውያን በመሸጥገር ውስጥ የተገኘን ትርፍ በውጭ ምንዛሪ በጥቁር ገበያ ከማሸሽ የተለይ ራ ሲሩ አልታዩም፡፡ በአርባ ምንጭ አካባቢ የሙዝ እርሻ እንዳላቸው በራ አጋጣሚ ያጫወተኝ የህንድ ኢንቨስተር ወኪል ወደ ውጭ ገር የተመረተውን ሙዝ  ኤክስፖርት ማድረግ አለማድረጉን ስጠይቀው ውጭ ገር አንድ ኪሎ ሙዝ ብዙ የጥራት መፈርት እንዲያሟላ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶበት  በ20 ብር ሲሸጥ በኢትዮጵያ ውስጥ አስ ገሰሱን ጭምር ያለ ብዙ ድካም በኪሎ 22 ብር ስለምንሸጥ ለምን ኤክስፖርት እንዳደርጋለን ብሎ የመለሰልኝ ሳስበው እንደ ገር ምንኛ በከፍተንቀላፋት ውስጥ እንደምንገኝ ያስታውሰኛል፡፡

ቀድሞ ኢትዮጵያን ሊወር የመጣው ጣያን በፋሽስትነትና የቀለም የበላይነት እሳቤ መደብደቡንና ማሩ በራሱ ለመራት ስለሞከረ ወራሪ ብለን አባረርነው፡፡ አሁን ግን ዘመናዊው ኢንቨስተር የመብደቡን ራ ለራሳችን ለኢትዮጵያውያን ሰጥቶ፣ ከካዝናችን ብር ውስዶ፣ በራሳችን ጉልበት አምርቶ፣ መልሶ ለራሳችን ሸጦ ኢንቨስተር እየተባለ በመሪዎቻችን ደጃፍ ላይ ቅድሚያ እያገኝ ተብሮ ይኖራል፡፡ ከላይ ለመጥቀስ በሞከርኳቸው መንገዶችና በተለያዩ መንገዶች ከራሳችን ኪስ የተገኘውን ብትም በውጭ ሮች ጥሪት ለመቋጠር ከሚንከራተቱ ኢትዮጵያውያን የውጭ ምንዛሪ ከብራዊ ባንክ የምንዛሪ ተመን ላይ ዋጋ እየጨመረ በመግዛት ወደ ገሩ ያሸሻል፡፡

አንድ የአሜሪካ ዶላር 13 ብር በነበረበት ጊዜ የጥቁር ገበያው 16 ብርጋዊ ምንዛሪ ዶላር 16 ብር ሲገባ ጥቁር ገበያ 18 ብር ቆይቶ ቆይቶም ብራዊ ባንክ የምንዛሪ ዋጋውን 28 ብር ሲያደስ የጥቁር ገበያው 30 ብር እያለ የሚጓዘው በዋነኝነት በዚሁ ምክንት ነው፡፡ እንደ ሰሞኛው ደግሞ የገር ውስጥ የፖለቲካ መረጋጋት ሲጠፋ ልዩነቱን እስከ አር ብር በማድረስ ብትን ለማሸ ስለሚሞከርንዲይነት የውጭ ኢንቨስተሮች ተመልካች እስካላገኙ ድረስ ብራዊ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር መግዣን አንድ ሺ ብር ቢያደርስም የጥቁር ገበያው ዋጋ በላዩ ላይ ጭማሪ በማድረግ እንደናረ ይቀጥላል እንጂራዊ ባንክ ከጥቁር ገበያ ጋር ተወዳድሮ የውጭ ምንዛሪ ክምችቱን ሊያተካክል አይችልም፡፡ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ገር ውስጥ በብራዊ ባንክ በኩል ብቻ የሚላከውን የገንዘብ መጠን የቱ ቀንደኛ ኤክስፖርት ከሆነው ቡና በላይ የውጭ ምንዛሪ የሚያመነጭ መሆኑንና ብራዊ ባንክ የሚገባው የውጭ ምንዛሪ ከትው ኢትዮጵያውያን ከሚላከው ገንዘብ አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመለቱት አንድ አምስተኛ እንኳን እንደማይሞላ ማስታወስ በእነዚህ የውጭ ኢንቨስተሮች ምክንያት እየደረሰ ያለውን ጉዳት መገንዘብ ያስችላል፡፡

ዚህ ምክንያት ያጋጠመውን የውጭ ምንዛሪ ችግር ለመፍተታት ብራዊ ባንክ ትርፉን በገሩ ላይ የሚያፈሰውን የገር ውስጥ አስመጪ ላይ ብቻ ትኩረቱን በማድረግ የውጭ ምንዛሪ መፍቀድን አቁሞ ኢምፖርት ራን በማዳከም የውጭ ምንዛሪ ክምችቱን ለማሻሻል ቢሞክርም በኢትዮጵያ ውስጥ የኑሮ ውድነት ከመፍጠርና የማበረሰቡን የመግዛት አቅም ከማመንመን ውጪ የተሻለ ውጤት ሊያመጣ ያልቻለውም ለዚህ ነው፡፡ በአጠቃላይ ተኩላን የዶሮ ጠባቂ ማድረግ ማለት ይ ነው፡፡ በዚህ በውጭ ኢንቨስተር የገርን ኢኮኖሚ ለማስተዳደር በሚደረግ ሙከራ በሚመጣ ችግር ምክንያት በዝቅተኛው የኢኮኖሚ ርከን ውስጥ የሚኖሩ የማበረብ ክፍሎች የመኖር ዋስትናቸው ጥያቄ ውስጥ ስለሚገባ የመንግት ራ ምታት ይሆናሉ፡፡  ዝቅተኛው የማበረሰብ ክፍል ወይም ራ አጡ በኢኮኖሚው ውስጥ በበቂ ሁኔታ ስለማይካተት አመ ለማንሳት ወደ ኋላ አይልም፡፡ የዚህ የብረተሰብ ክፍል ጥያቄም በቀላሉ ወደ ፖለቲካ ጥያቄ ማደግ ስለሚችል መንግትንም ሆነ ገርን ለማጥቃት ለሚዘጋጁ ይሎች ጥሩ መሪያ ይሆናል፡፡ ጥያቄው በአንድ ጀበር የሚፈታለት ስለሚመስለውም ይው የማበረሰብ ክፍል አስፈላጊውን መስዋትነት ለመክፈል አያመነታም፡፡

መንግትም ይህን ስለሚያውቅ እነዚህን የማበረሰብ ክፍሎች አነስተኛና ጥቃቅን በመሳሰሉ በበቂ ጥናት ላይ ያልተመረቱ ፕሮግራሞች መርቶ ተጠቃሚ በማድረግ የራሱ የፖለቲካ ደጋፊ እንዲሆኑ ዙ ገንዘብ በጅቶ ላይ እታች ሲል ይታያል፡፡ ድሜው ላልደረሰ ልጅ ከአቅሙ በላይ የሆነ ራ ማራት ሕፃኑን እንደሚገድልና የነበረድልና ተስፋ እንደሚያባክን ሁሉ ያልጠነከረ የማበረሰብ ክፍል ላይ በጀት ማፍሰስም እንዲሁ ትውልድ ገዳይ መሆኑ አይቀም፡፡ ለችግር መውጫ እየተባለ ለራ ፈጣሪነት ከመንግት የሚለቀቀው ገንዘብ  ራ ፈጠራን ሳይሆን ገወጥ ስደትን ስፖንሰር እንዳደረገ የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ከስደትና ከመባከን ውጪ ጥቃቅንና አነስተኛ ተብለው ለተደራጁ ወጣቶች በፈሰሰው ገንዘብ ወጣቶቹ እንዲማሩበት የተደረገው የራ መስክ በአብዛኛው ተጨማሪ የኮኖሚ እንቅስቃሴ ሩ ለከተሜ ኑሮ የሚሆኑ ያለቁ የመገልገያ ቃዎችን ማምረት ስለሆነ በዚህ መንገድ ወደ ገበያው የሚገባው ገንዘብ የኑሮ ውድነትን ሲፈጥር ይታያል እንጂ ኢኮሚውን በዘላቂነት ሲቀየር አይታይም፡፡

መንግ በሌብነት፣ በዘረኝነትና ሌሎች ችግሮች ቢኖሩበትም የጽላማ ኢኮኖሚ ላይ ስለሆነ ለጊዜው እነሱን ትተን ያለ ውቀትና ምክንያታዊ ባልሆነ መንገድ ፖለቲካን ብቻ ታሳቢ አድርጎ በሚመራው ኢኮኖሚ ምክንያት ወጣቱ ላይ ገንዘብ ቢያፈስምዝቡን ችግር ሊፈታ ለማይችል ራ አጡንና ዝቅተኛው የማበረሰብ ክፍል ዘረፉህ ሰፋሪዎች መሬትህን ወሰዱብህ በሚል ተራሪ ያህሎች በእጃቸው ያደርጉታል፡ የሚያጣው ነገር ትንሽ ስለሆነ በአጣኝ ችግሩ የሚፈታለት ስለሚመስለውና  ስለማይፈራም ይህ የማበረሰብ ክፍል አመ ያነሳል፡ራሪም ይህን ይል ተጠቅሞ ልጣን ላይ ከወጣ በኋላ ራሱ የቀሰቀይል ለራሱ ልጣንም ስለሚያ ይህን አካል ለማስተንፈስ ባልተጠናና አዋጭ ባልሆነ መንገድ ገንዘብ ያፈስለታል፡፡ላማው መሳካት ላገዘው ሁሉ ችሎታ ለሌለውም ቢሆን ልጣን ለመስጠት ይገደዳል፡ ይህም ገራዊ ኮኖሚውን ኪሳራ ላይ እንዲወድቅ ያደርግና የሁሉን ነገር ፈተና ወደ ጥያቄ ቁጥር አንድ ይመልሰዋል፡፡ በዚህ ይነት የፖለቲካ ትኩሳትን ለማብረድ እየተባለ በሚራ ምክንያት የመካከለኛው የማበረሰብ ክፍል ለኢፍትዊ የኮኖሚ አስተዳደር ይጋለጣል፡፡ የተሳሳተ የኢኮኖሚ አመራር ገር ለማፍረስ ዳር ሲደርስ ከሁለትና ስት መታት በፊት እንደታየው ለኢትዮጵያዊው ባለብት የለም ወይም በከፍተኛ ዋጋ በጨረታ ውሰድ የሚባለው መሬት ለአመ ለተዘጋጀው ወጣት በነፃ ይከፋፈላል፡፡ በስንት ልፋት መሬት አግኝቶም በባንክ ራ የጀመረውም ቢሆን የፖለቲካ ትኩሳቱ ሲያይል ብትና ንብረቱን አሳ ተብሎ ያለማው የማድን ቦታ ተቀምቶ ለወጣቶች ተሰጥቷል ይባላል፡፡ ለመከለኛው የብረተሰብ ክፍል የተነፈገው የባንክ ብድርም ጥቃቅንና አነስተኛ ለተደራጀ ወጣት ይከፋፈላል፡፡

በዚህ የእሳት ማፋት ራም ኢትዮጵያ ውስጥ ከጓደኞቹ በርትቶ በትምህቱ የገፋው ወጣት የትምህት ዘመኑን በዋዛ ፈዛዛ ሲያሳልፍ ከነበረ ወጣት ያነሰ የኢኮኖሚ አቅም እንዲኖረው ተደርጓል፡፡ በርትቶ የግል ራ ፈጠራ ላይ ያለው ወጣት እየተተወ በሥራ አጥነት ገር ሲያስቸር የነረ ወጣት የመሥሪያ ሼድና የገንዘብ ብድር ይሰጠዋል መንግታዊ ኮንትራት በቀጥታ ያገኛልወዘተ.፡፡ በትምህለም ውስጥ ሲታር የነበረው ወጣት ራ አጥ ሆኖ ሲንከራተት ወይም በአስተኛ ደመወራ ተሻምቶ እንዲያገኝ ሲሆን ለመማር ቃደኝነት ያልነበረው ወጣት በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅ እየተባለ “ሚሊነር” የሚሆንበት፣ በርትቶ ነግዶና ራ ፈጥሮ ራውን ለማሳደግ የሚሞክረው ወጣት እያለ ራ ከመራት ይልቅ አመ የሚያነሳው ወጣት ብቻ ድጋፍ የሚያገኝበት ሁኔታ በአጠቃላይ በጠንካራው የወጣት ክፍል ተስፋ መቁረጥን አስከትሏል፡፡

አሁን በዚህ ወቅት በወጣቱ ላይ እየታየ ያለው ከምትለፋና ከምትጣር ወይ አመ አንሳ ወይም ወደ ውጭ ሮች ተሰደድ የሚለው አስተሳሰብ መበራከትና ባለ ምጡቅ አዕምሮ ኢትዮጵያውያን ለገራቸው ሳይሆንለባገር ውቀታቸው ለመገበር የሚቀዳደሙበት ዋነኛ ምክንያት በገር ውስጥ ያለው ይህ ቅ እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም፡፡ የሚመራውን ማበረሰብ በሚጠበቅበት ደረጃ መምራት የተሳነውና ስንፍና ሆነ ተንኮል የተጠናወተው መሪ ጥያቄ ሲበዛበት ሌብነት ራ ነው ብሎ ያውጅና የራበው ውሻ ጆሮውን ቆርጠው ቢሰጡት ምግብ የሰጡት ይመስለዋል እንደሚባለው ከራሱ ኪስ እየሰረቀ የሚኖር ማበረሰብ ይፈጥራል፡፡ ቀጥሎም የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ ውጥንቅጥ በስግብግብ ነጋዴዎች እያሳበበ በወንበሩ ለመቆየት ይጥራል፡፡ በርትቶ መራት መልካም ነው ሳይሆን ሌብነት ራ ነው የሚል መሪ የሚያይ ማበረሰብ በጤናማ ኢኮኖሚ ራሱን ሊያሳድግ አይችልም፡፡ አብዛኛው ራ ፈጣሪ የሚሆነው ወጣታችን ጊዜውን በአምራች በሆነ መንገድ ሳይሆን ኢመደበኛ የኢኮኖሚ መስኮች ላይ በማፍሰስ እንዲጠመድ ያረገውም ይህ ነው፡ አዲስ አበባ ውስጥ ከጠዋት እስከ ማታ መንገዶች የሚጨናነቁትም በመደበኛ ኢኮኖሚ የሚያመት ሳይሆን በኢመደበኛ ኢኮኖሚ ከላይ ታች ሲዋትት የሚኖር ማበረሰብ ስለበዛ ነው፡ ይህ ውታማ ሊሆን የሚችል መከለኛው የብረተሰብ ክፍል ለአፍታም ቢሆን ከሚኖርበት የባለሀብት እርገጥ ጉዞ ደከም ቢል ወደ ዝቅተኛው ማበረሰ እንደሚወርድ ስለሚያስብ የሆዱን በሆዱ አድጎ ሲፍጨረጨር ያኖራል፡፡ ለመንግት ቀጥተኛ ጋት ስለማይሆነውም መንግትም ዞር ብሎ አያየውም፡፡

በራሱ ጥረት በርትቶ በኢኮኖሚና በውቀት የጎለመሰውን መከለኛው የማበረሰብ ክፍል ወደ ላይ እንዳያድግ በፋይናንስ፣ በመሪያ ቦታና በቢሮክራሲ ማነቅ  ለገር አደጋ የሆነ፣ በሌብነትና በሌብነት ብቻ ማደግ ይቻላል ብሎ የሚያምን፣ በአየር በአየር የአጭር ጊዜ ራ ላይ ብቻ የሚንጠለጠል ኢኮኖሚ ውስጥ የሚሳተፍ የመከለኛ ኢኮኖሚ አንቀቃሽ ይፈጥራል፡ ድለላ አስመጪነት፣ ቤት ርቶ ማከራየት፣ አንድ ሱቅ ላይ ችርቻሮ የመራት የመሳ ራዎችን በመራት  መኪና በሞዴል መቀየር እንጂ ሌላ የማይመኝ ብትን ጥቅም በማይሰጥ ብልጭልጭ ነገር የሚያጠፋና ያገኘውን ገንዘብ ምን እንደሚያደርግበት ግራ ገብቶት ለሱስና ለመጤ ባህል የሚጋለጥ ትንሽ ገንዘብ ሲያገኝ ዱባይና ሌሎች አገሮች ዶ ሆቴል ማደርን እንደ ድገት መለኪያ የሚቆጥር የማበረሰብ ክፍል ይፈጥራል፡፡ አንድ ወጣት እንደ ድሜው እንዲራ እንዲታትር ቢያበረታቱት ያለውን ትኩስ ኃይል እንዲጠቀም ቢደረግ ከፍተኛ ለውጥ እንዲያመጣ ማረግ እንደሚቻል ሁሉ በተቃራኒው እንዳይሮጥና እንዳይታር ታስሮ እንዲቀመጥ ማረግ ሰነፍና ለቤተሰቡ አደጋ የሆነ ወጣትን ይፈጥራል፡፡ ር የሚያየውም ታዳጊም በላብና ወዝ ማደግን እንዳይመኝ ያደጋል፡፡ በየትኛውም ማበረሰብ ውስጥ ድገት የሚገኘው ራ ሲከበር ሁሉም እንደ ጥረቱ ውጤቱን ሲያገኝና ማበረታቻ ሲደረግት ነው፡

በኢትዮጵያ ውስጥ ግን የሚታየው የዚህ ተራኒ ነው፡፡ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሁኔታ አምራችና ጥረት የሚያደርግ የማበረሰብ ክፍልን ያበረታታ አይለም፡ኢትዮጵያዊ የሆነውና ከኢትዮጵያውያን አንር ከፍተኛ ገቢ አለው የሚባለው የማበረሰብ ክፍልም ደግሞ መንግት በተሳሳተ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ምክንያት ለውጭ ባለብቶች ብቻ ትኩረት የሰጠ በመሆኑ የአምራችነት (ባለ ኢንዱስትሪ የመሆን) ሞራሉ ሞቷል፡፡ አምራች እንዲሆን የያደርገው መንገድ በአብዛኛው ለገር ውስጥ ባለብት ሁሉ እንደ ዳገት እንዲከብደው ተደርጓል፡፡ ው ዳገት ከገጠመው የመሬቱን አቀማመጥ እያየ ወደ ቀለለው እንደሚፈስ ሁሉ ይህ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ይልም ወደ ቀለለው ይሄዳል፡፡ ማምረቻ ቦታ ለማግኘት ያለው የቢሮክራሲው ጣ ውረድና የተቀመጠው የሊዝ ዋጋ ልምዱንና የራ ባህሉን ተጠቅሞ ወደ መካከለኛ ኢንዱስትሪያሊስትነት እንዳያድግ ሲያተውና ችግሩን ለመፍታት አንድ ሚኒስትር ለማግት ለወራት ሲንከራተት እንደ አክጉን ግሩ ያሉ የቱርክ “ባለ ብቶች በባዶ እጅ ቤተ መንግት ገብተው በሺዎች የሚቆጠር ክታር ሲቀበሉና ያለ ራ ለመታት አጥረው ሲያስቀምጡ  ይታያል፡ይህ የማበረሰብ ክፍል በጽፉ መግቢያ ላይ በተገለጸው  ምክንያት በውጭ ባለብቶችና በሌሎች ምክንያቶች በሚመጣው የውጭ ምንዛሪ ችግር በእጁ ያለው ገንዘብ የመግዛት አቅም ከማጣቱ በፊትገር ውስጥ ያፈራውን ብት በራ ፈጣሪ ኢንቨስትመንቶች ላይ ከማዋል ይልቅ ለመገንባት የውጭ ገር ግብዓቶችን የሚጠቀም ከተገነባም በኋላ ምንም ይነት ተዘዋዋሪ ዊ ኢኮኖሚ ፋይዳ የሌለው የመኖሪያ ቤትና ርቶ ማከራየት ላይ ብቱን  እንዲያውል ይገደዳል፡፡ ከገር ውስጥ ባንክ ተበድሮ የሚገዛውን የግብርና ምርት በኪሳራ ለውጭ አገሮች በመሸጥ በሚያገኘው የውጭ ምንዛሪ የባዕድ ገር ፋብሪካ ምርት አምጥቶ ለገር ውስጥ በማቅረብ ትርፍ ለማግኘት ይሞከራል፡ ኑግ ልኮ ዘይት ይገዛል፡ ዘይት እዚሁ የመጭመቁ መንገድ ዳገት ተደጎበታ፡፡ ‹‹ድብ ሲያባርርህ የሚጠበቅብህ ከጓደኛህ መቅደም ብቻ ነው›› እንደሚባለውኛው የማበረሰብ ክፍል ከሌላው በተሻለ ስለሚኖር ከተቀረው የብረተስብ ክፍል ትርፍ በመብሰብ ኑሮውን በአንፃራዊ “ምቾት” ነገር ግን ዘላቂነት በሌው መንገድ  ይመራል፡፡

አፈር ይዞ ውስጡ አረንጓዴ ለምን ይሆን የራበው ሆዴ? ለሚለው የዘመናት ጥያቄ መልስም ከላይ የተጠቀሱት ነገሮች ከበዙት ችግሮቻችንና መልሶቻቸው ውስጥ አንዱ ከላይ የተዘረዘረው ይነት የተሳሳተ የኢኮኖሚ አስተዳደር ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ይህ የተሳሳተ የኮኖሚ አስተዳደር የፖለቲካ ቀውስ ለመፍጠር ዳር ዳር ሲለው ሠርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥ በሆነ መንገድ የሚከናወነው ራ ችግር አባባሽ ሲሆን እንጂ መፍት ሲሆን አልታየም፡የተሳሳተ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ድህነትን በመፍጠር ድህነት የፖለቲካ አለመረጋጋትን፣ የፖለቲካ አለመረጋጋት የኢኮኖሚ ድቀትን፣ የኢኮኖሚ ድቀት የኑሮ ውድነትን፣ የኑሮ ውድነት ተመልሶ የፖለቲካ አለመረጋጋት እየወለደ ጨካኝና አውዳሚ የሆነ እሽክርክሪት (ቪሸስ ሰርክል) ውስጥ ገር እንድትሽከረከር ያደጋል፡፡

ይህን ውስብስብ የችግር ቋጠሮ ለመፍታት በችኮላ ያገኙትን ጫፍ ይዞ ከመጎተት እንደ ኢትዮጵያ ያለ ከ100 ሚሊዮን በላይ ዝብ ያቀፈን፣ አብዛኛው ወጣት የሆነ ማበረሰብ ያለውን፣ ለምና ለራ ምቹ የሆነ መሬትና የአየር ባይ ያለው ገር ይዞ የውጭ ሮች ላይ ለድገት ከማተኮር ይልቅ ማበረሰባችን ለምን ማደግ አልቻለም ብሎ ቆም ብሎ ማሰብ ያስልፈልጋል፡

ገር ኢኮኖሚን አሳድጎ በዘላቂነት ለማስቀጠልና ለትውልድ እንዲተርፍ ለማደረግ ከር ወደ ላይ የሆነ ተፈጥሯድገት መስመርን ተከትሎ የራስን አቅም መገንባት ይበጃል፡፡ አንድ ልጅ ተወልዶ በሚያስፈልገው ጊዜ የሚያስፈገውን ምግብ እያገኘና በድሜ መጠኑ ልክ የሆነ ራ እየራ እንዲያድግ ቢደረግ ለራሱም ለማበረሰቡም የሚጠቅም እንደሚሆን ዜጎችም በዚሁ የኢኮኖሚያዊ ዕድገት መሰላል  ውስጥ ተገቢውን ፍራ እየተሰጣቸው እንደ መጠናቸው አስፈላጊ የሆነ ድጋፍ እየተደረገላቸው በኢኮኖሚ ካደጉ ኢትዮጵያውያን ላለው ትውልድ የተመቸች ለቀጣዩም ትውልድ የምትተርፍ ማድረግ ይቻላል፡፡ ከታችኛው ወጣት ጀሮ እስከ ላይኛው የገር ውስጥ ኢንቨስተር ድረስ ያለው ሰንሰለት እንደ አስፈላጊነቱና በጥረቱ እንደ ደረሰበት ደረጃ ማበረታቻና ድጋፍ እያገኘሩ ከሱ ያነሱትን እያቀፈ እንዲሄድ ማድረግ ለዘለቄታዊ የገር ድገትና ህልውና  ወሳኝ ነው፡፡ በራሳችን ስተት ባመጣነው የደን መራቆትን ለመፍታት ከባህር ማዶ ስመጣነው ባህር ዛፍ መሬቱን ሁሉ አድርቆ ገር በቀል ዛፎችን እንዳያድጉ እንዳደረገው ሁሉ ዜጋን ችላ ብሎ ትልቅና ጠንካራ የሆኑ የውጭ ኢንቨስተሮችን ወደ ገር ውስጥ እንዲመጡ ቢደረግ የገር ውስጥ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾችን በመጨፍለቅ ማበረሰቡን እንደ አንድ አንድ የአፍሪካ አገሮች ተቀጣሪ ከማድረግ የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም፡፡

በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ያሉ የተደራጀ መከለኛ ክፍል ማበረሰብ በሌለበት ገር የሚመጡ የውጭ ኢንቨስተሮች በገር ውስጥ የተዘጋጀ ገበያ ስለማይኖራቸው በተቻላቸው መጠን መላው ገሩን እንደ ወርክ ሾፕ ብቻ በመቁጠር የሚቻላቸውን ያህል ገብዘብ ወደ መጡበት ገር ያሻግራሉ እንጂ ተጨማሪ ኢንቨስትመንት በገር ውስጥ ለማፍሰስ ፍላጎት የላቸውም፡፡ እዚህ ላይ እንደ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት (FDI) ማብዛት ያሉ በለም ባንክና በሌሎች ለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ለኢኮኖሚ ድገት አስፈላጊነት የሚቀነቀኑ የኢኮኖሚ ምክሮችን እንደ እውነተኛ ምክር በመቁጠር የውጭ ባለብቶችን መሳብ ትክክለኛ መንገድ ነው ብለው የሚሟገቱ ወገኖች ይኖራሉ፡ ለእነዚህ ወገኖች የለም አቀፍ ተቋማትና ያደጉ ገሮች መንግታት ለኛ ሳትገብሩ ብቻችሁን ደጉ ብለው እንዲመክሩን እየጠበቃችሁ ነው ይ? የገዘፈ ኢኮኖሚ ባለቤት በሆኑ ገሮች የተቋቋሙ የፋንናንስ ተቋማት እንጂ ለድቅ የተቋቋሙ ተቋማት እንዳልሆነ ዘንግታችሁታል ወይ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ይሆናል፡፡

ባራክ ኦባማን ጨምሮ የተለያዩ ገር መሪዎች መከለኛውን የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ መደብ በማንቀሳቀስና በማበረታታት ዜጎቻቸው በኢኮኖሚ እንዲያጉ ማድረግገራቸው ኢኮኖሚ እንደሚበጅ ሲሟገቱና ልቅ ተቋማቶቻቸውን በሚገባ ሲደግፉ ይታያሉ እንጂ የውጭ ኢንቨስተር እንዲመጣላቸው ወይም ራ አጥ ወጣቶቻቸው ተደራጅተው ጥቃቅንና አነስተኛ ንግድ ላይ እንዲማሩ ሞግቱ አይታይም፡፡ ያደጉት አገሮች ከውጭ የመጡ ኢንቨስተሮች የማይፈልጉት በቴክኖሎጂ ከራሳቸው አገሮች ድርጅቶች  ስለማይበልጡ አይደለም፡፡ የውጭ ኢንቨስተር የኢኮኖሚ ጥቅሙ ለመጣበት ገር ስለሆነ እንጂ፡፡

ሁዋ የተባለው ግዙፉ የቻይና የቴሌኮም ኩባንያ በአሜሪካ የገጠመው ችግር ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው፡፡ ሁዋ የደረሰበት 5G ቴክኖሎጂ የአውሮፓና የአሜሪካ ካምፓኒዎች የደረሱበት ቴክኖሎጂ አይደለም፡ በቅርቡም የሚደርሱበት አይመስልም፡፡ ሁዋ በአሜሪካ ኢንቨስት በማረጉና የቴሌኮም መስመር ዝርጋታዎችን በመሳተፉም በሺዎች ለሚቆጠሩ አሜሪካውያን ራ ይፈጥራል፡፡ የሪቱን ኢኮኖሚ እንቅስቃሴም በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድል፡ ሁሉ ጥቅም እያለው ሁዋ አሜሪካና ምዕራባዊያን ኢኮሚ እንዲወጣ ጫና ውስጥ የገባው በአደባባይ እንደሚባለው ለቻይና መንግት መሰለያነት እንደሚውል ስለተጋ ብቻ አይደለም፡፡ የ5G ቴክኖሎጂ በአውሮፓና አሜሪካ በራ ላይ በመዋሉ ለቻይናና ለሁዋ 500 ቢሊዮን ዶላር በላይ ጥቅም የሚያስገኝ ስለሆነና የምዕራባዊያን የቴሌኮም ኩባኛዎችን ከ ውጪ ስለሚያደግ ነው፡ ይህም ዞሮ ዞሮ በአጭር ጊዜ ለምዕራባውያን የሚሰጠውን የኮኖሚ ጥቅም በረጅም ጊዜ ውስጥ አጥፍቶ የኢኮኖሚውንም ሆነ የፖለቲካ ይሉን ወደ ቻይና ስለሚያዞረው ነው፡

ምዕራባውያን የሚፈልጉት የውጭ ኢንቨስትመንት (FDI)  የሌሎች ገር ዜጎች በምዕራባውያኑ ኩባንያዎች አክዮን እንዲገዙ፣ ገንዘባቸውን ከገራቸው አውጥተው በምዕራባውያን ባንኮች እንዲያስቀምጡ፣ የተረጋጋ የፖለቲካ ርዓት ስላላቸው ለመጠባበቂያ ቤት እንዲገዙ በማድረግ ላይ የተመረት እንጂረታዊ የሆነ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾቻቸውን የሚወዳደሩ የውጭ ኢንቨስተሮች እንዲመጡ አይፈቅዱም፡፡ ይህ ቅ ከገር “ኮኖሚስቶች” እና “ምሁራን” ለምን እንደተሰወረ መረዳት ይቸግራል፡፡ በውጭ ሮች የኢኮኖሚ ቱሪስቶች ትምህትን በመሸምደድ ብቻ ኮኖሚስት ስለተባሉ ወይም በግላቸው ለውጭ ባለብቶች ተቀጥረው በመራት የሚያገኙትን ጥቅም ታሳቢ በማድረጋቸውወይም ደግሞ የባዕድ ቋንቋንና ቃላትን ብቻ እንደ ውቀት ወስደው ዋናውን ውቀት ባለመውሰዳቸው ይሁን በሌላ ምክንያት አልታይ ያላቸው መገመት ይከብዳል፡፡

በምዕራብ አገሮችኮኖሚ ቱሪስቶች ሳብ ራ ሰዎች (የኢኮኖሚው አንቀሳቃሾች) ተመዝኖና ተመርጦ ኢኮኖሚው ሲመራገር ግን “ኢኮኖሚስቶች” የመንግት አማካሪ በመሆን ያለ ራቸው ኢኮኖሚው መሪ ስለሚሆኑ ይሆናል የኢኮኖሚ ችግራችን ሊፈታ ያልቻለው የሚል ግምት አለኝ፡፡ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ችግርና የኢትዮጵያ ዜጎች የኮኖሚ ድቀት በውጭ አገር ኢንቨስትሮች ሊፈታ አይችልም፡፡ አንድ ሺ የውጭ ከፍተኛ ኢንቨስተሮች መጥተው በኢንዱስትሪ ፓርኮች እያንዳንዳቸው ለአምስት ሺ ራተኞች (እስካሁን አስት ሺ የፈጠረ ፋብሪካም መኖሩ ያጠራጥራል) ራ ፈጥረው ደመወዝ ቢከፍሉ እንኳን በየመቱ እስከ ስት ሚሊዮን ራ አጥ በሚጨመርበት ገር ውስጥ አምስት ሚሊዮን ራ በመፍጠር የኢትዮጵያ ችግር ሊፈታ አይችልም፡፡ የውጭ ኢንቨስተር ላይ ማተኮር ከችግር ወደ ችግር እንድንኳትን ከማድረግ ውጪ መፍት ሊሆን አይችልም፡፡ የሚያስፈልገን የውጭ ኢንቨስተር ይነት የኛን ምርት ሊገዛ የሚችል ኢንቨስተር  ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ መጥቶ ቤት የሚገዛ፣ እንደ ዱባይ በራሱ ገር ያመረተውን ምርት ለሌላ ገር  ለመሸጥ በገራን ወደብና ደረቅ ወደብ ውስጥ የሚ ኢንቨስተር ነው የሚያስፈልገን፡፡

የትኛውም ገር ከውጭ መጥቶ የገር ውስጥ ባለተስፋ አምራቾችን በሚያቀጭጭ ኢንቨስተር አላደገም፡፡ የውጭ ኢንቨስተር ጥቅም የተወረወረበት ደርሶ ሳያርፍ ወደ ወርዋሪው የሚመለስውን ተሽከርካሪ መጫወቻ ይነት ነው፡፡ ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ውጥንቅጥ ወጥታ እርስ በርሱ በደብ የተሳሰረ፣ ከስደት ይልቅ በገር ውስጥ መኖርን ልሙ ያደረገ፣ በቀላሉ በጠላት የማይፈታ ሆኖ የተሳሰረ ማበረሰብ እንዲኖራት ሁሉም በራው መጠን ልክ የሚከበርበትና የሚበረታታበት ርዓት መገንባት ስፈልጋል፡ ተፈጥሯዋዊ ድገት ተከትለን ነገር ግን ፈጣን በሆነ መንገድ ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ችግር ወጥታ ካደጉት አገሮች ተርታ እንድትለፍ የተጠናቀረ የኢኮኖሚ ርዓት ለመገንባት ትኩረት ሊሰጠውና ከፍተኛ ድጋፍ ሊደረግለት የሚገባው የውጭ ኢንቨስተር ወይም በኪራይ ሰብሳቢነት ኑሮውን ማጣጣም የለመደውን የገር ውስጥ ከፍተኛ ባለብትንና በተቃራኒው አቅጣጫ ያለውን ለራ ዝግጁ ያልሆነን የታችኛው ማረሰብ ሳይሆን ገና ሮጦ ያልጠገበው ለመራት ከፍተኛ አቅምና ለማደግ ከፍተኛ ጉጉት ያለውን የመካከለኛውን የኮኖሚ አንቀሳቃሽ ክፍል ነው፡፡

ይህ የማበረሰብ ክፍል ባለው ምቅ ችሎታና ከፍተኛ የማደግ ፍላጎት አንድም ያንቀላፋውን የላይኛውን ማበረሰብ በኢንቨስተርነት በመሳብ ያለውን ፋይናንስ የሚጠቀምበት መንገድ በመፍጠር ለኢኮኖሚው ግብዓት ያደገዋል፡፡ ካልሆነም በተደረሰብኝ ስሜት እንዲሮጥ ያስገድደዋል፡፡ በሌላም መንገድ ለታችኛውም ማበረሰብ ሰፊ የድል ይፈጥራል፡፡ በየመቱ ከከፍተኛ የትምህት ተቋማት ለሚመረቁ ተማሪዎች አሁን በውጭ ባለብቶች እንደሚታየው የመታት የራ ልምድ ሳይጠይቅ የድል ይፈጥራል፡፡ መንግትም ከመንግታዊ ራው ወጥቶ የነጋዴና ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ራ ውስጥ ገብቶ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የገር ብት ከሚባክን የመራት አቅም ላላቸው የገር ውስጥ ዜጎች የጥቅምም የኪሳራም ባለቤት በማድረግ ጀምሮ ኪሳራ ያቋረጣቸውን ፕሮጀክቶቹን ቢያስተዳድር፣  የኢንዱስትሪ ፓርኮችን መንግት በመራት ለማከራየት ከሚሯሯጥ ለግል ባለብቱ እንደ አቅሙና በአክዮን እየተደራጀ በመራት እንዲያከራዩ የረጅም ጊዜ የፋይናንስ ድጋፊ ቢያደረግ፣ ፋብሪካዎችን በባቤትነት እንዲያስተዳድሩ የአክሲዮን ማበራትን ቢያጠናክር የተሻለ ይሆናል፡፡ ገር በቀል በቅ የሚሩ መከለኛ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ባንኮችን ከዜሮ ተነስተው በመመረት በታጠረና በማይመች ፖሊሲ ውስጥ የት እንዳደረሱ መመልከት በራስ መለወጥ የሚችል ይል እንዳለን በቂ ማሳያ ነው፡፡

በመንግት ውስጥ ያሉ ስታሊኒስትና ያልገባቸውን ሶሻሊዝም እንደ ሃይማኖት የያዙ ባለልጣናትም የራስ ገር ዜጋ አሥር ብር ያለአግባብ ከሚጠቀም ቻይና ትውልድን ባለ ዳ ብታደግ ይሻላል ከሚል አመለካከት ቢወጡ ይሻላል፡ ቢያንስ በራስ ገር ያግባብ የተገኘ ገንዘብ ተመልሶ የሚገላበጠው ገር ውስጥ ነው፡፡ በረጅም ጊዜም በጋዊ መንገድ ለማስመለስም ድልም አለው፡ የራስ ዜጋ ላይ ጦር ሰብቆ ቆሞ ለቻይናና ህንድ ዜጎች ራና እንጀራ የሚፈጥር  ከራስ ስው ጋር የመጠማመድ  አስተሳሰብ ሊወገድ ይገባዋል፡፡ በአጠቃላይ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚና የፖለቲካ ችግሮችን ለመፍታት መፍትው የራስን ችግር መመልከትና የተንሰራፋውን ኢፍትዊ የኢኮኖሚ ሞዴል ማስተካከል ነው፡ ሁሉም እንደ የአቅሙ እንደ ራ ድርሻው እንዲወጣ ከማድረግ ውጪ አሁን እንደሚታየው ራ መፍጠር ያልቻለ ራ አጥ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ እንዲሆን የሚጣርበት፣ መንግት ነጋዴ ለመሆን ሞክሮ በአሳፋሪ ሁኔታ የሚወድቅበት ነገር ግን ተጠያቂ የማይሆንበት፣ አቅም ያለውና ለራ የሚታትር ሰው እንደ በዝባዥ የሚታይበት የተሳከረ አስተሳሰብ ማስተካከልና ከሁሉም በላይ በራስ አቅም ማመን ለዘላቂ ልማት ሳኝ ነው፡፡ ራስ ማለት ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንጂ ሜቴክና የፖለቲካ ደጋፊ ማለቴ አለመሆኑን ይያዝልኝ፡፡ አዎ ያለ ውጭ ኢንቨስተር የኢኮኖሚ ፖሊሲያችንን ብቻ በማስተካከል ገራችንን የበለገች ማድረግ እኛው እንችላለን፡፡

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...