Tuesday, May 30, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ለክቡር ሚኒስትሩ የቀድሞ ሚኒስትር ስልክ ደወሉላቸው

[ክቡር ሚኒስትሩ ከደላላ ወዳጃቸው ጋር ቢሯቸው እያወሩ ነው]

  • ይገርማል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምኑ ነው የሚገርመው?
  • በቃ ተተኮስን፡፡
  • ማን ነው የተተኮሰው?
  • በአንድ ጀንበር እኮ ነው የተተኮስነው፡፡
  • ምንድነው የምታወራው?
  • ተቸበቸበ እኮ፡፡
  • ምኑ?
  • ችግኙ ነዋ፡፡
  • ምን ጥያቄ አለው?
  • እኔ እንደዚህ ይሆናል ብዬ አልጠበኩም፡፡
  • እንዴት?
  • ያው ሕዝቡ አልተደመረም ብዬ ነዋ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ሕዝቡ እኮ በልቡ ተደምሯል፡፡
  • እሱንማ አሁን በሚገባ አረጋግጫለሁ፡፡
  • እንዴት?
  • ይኼን ያህል ሕዝብ በችግኝ ተከላው ይሳተፋል ብዬ አልጠበኩማ፡፡
  • ሕዝቡ እኮ ለውጥ የተራበ ነው፡፡
  • አዎን ግን አሁን አሁን እኮ ለውጡን እየተጠራጠረው ነበር፡፡
  • እንዴት ሆኖ?
  • በቃ አብዛኛው ሰው ለውጡ አቅጣጫውን ስቷል እያለ ነበራ፡፡
  • እንዴት አድርጎ ነው ለውጡ አቅጣጫውን የሳተው?
  • ክቡር ሚኒስትር አገሪቱ እኮ ከነበረችበት ችግር የባሰ እየገጠማት ነው የሄደችው፡፡
  • ይህ የፀረ ለውጡ አራማጆች ሐሳብ ነው፡፡
  • በመሬት ላይ ያለውም ሀቅ ግን እንደዚያው ነው፡፡
  • እንዴት?
  • ማለቴ ኢኮኖሚው አይሉ ፖለቲካው ሁሉም ነገር ተቃውሶ ነበር፡፡
  • ያው ሊነጋጋ ሲል ይጨልማል አይደል የሚባለው?
  • ቢሆንም ክቡር ሚኒስትር አገሪቱ እኮ የመፍረስ ጫፍ ላይ ናት፡፡
  • እ…
  • ይኸው በየጊዜው የሚፈናቀለው ሕዝብ ብዛት ከዓለም ራሱ አንደኛ አድርጎናል እኮ፡፡
  • ምን ይደረግ ታዲያ?
  • በዚህ ሁሉ ቀውስ ውስጥ ታዲያ እንዲህ ዓይነት የሕዝብ ንቅናቄ በጣም ያስገርማል፡፡
  • ሕዝቡማ ለአገሩ ያለውን ፍቅር በሚገባ አስመስክሯል፡፡
  • ለማንኛውም ክቡር ሚኒስትር እኛ በግርግሩ አምልጠናል፡፡
  • ጥሩ ተሸቀለ?
  • ምን ጥያቄ አለው፡፡
  • ለነገሩ በችግኝ ተከላው እኮ የራሳችንንም ሪከርድ ሰብረነዋል፡፡
  • ሰሞኑን ምን ያልተሰበረ ሪከርድ አለ?
  • ደግሞ ሌላ የምን ሪከርድ ተሰበረ?
  • እርስዎም ሪከርድ ሰብረዋል፡፡
  • የምን ሪከርድ?
  • የኮሚሽን!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ የፖለቲካ ተመራማሪ ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው]

  • በጣም ደስ ይላል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምኑ?
  • የሰሞኑ የችግኝ ተከላ እንቅስቃሴ ነዋ፡፡
  • እኛ እኮ የተግባር ሰዎች ነን፡፡
  • እርሱን እንኳን ተውት፡፡
  • ምነው?
  • አሁን የፖለቲካ ዲስኩርዎትን እንዲያሰሙኝ አልፈልግማ፡፡
  • ይኼ እኮ ዲስኩር ሳይሆን ሀቅ ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እናንተ እኮ የምትተቹት እንዲያውም በዚህ ነው፡፡
  • በምን?
  • የተግባር ሰዎች አይደሉም ተብላችሁ ነዋ፡፡
  • ይኸው አረጋገጥን አይደል እንዴ?
  • በእርግጥ በችግኝ ተከላው ጥሩ ሥራ ነው የተሠራው፡፡
  • ገና ሌላ ብዙ እንሠራለን፡፡
  • ለጊዜው ጉራውን ተውትና ሕዝቡን ማመስገን አለባችሁ፡፡
  • እሱማ ግዴታ ነው፡፡
  • ሕዝቡ የፖለቲካ ልዩነቱን ወደጎን ትቶ እንዲህ በነቂስ ወጥቶ በችግኝ ተከላው በመሳተፉ ሊመሰገን ይገባዋል፡፡
  • እውነት ብለሃል፡፡
  • ግን ክቡር ሚኒስትር ሕዝቡ ምን ያህል አገሩን እንደሚወድ አላያችሁም፡፡
  • በደንብ ነው እንጂ ያየነው፡፡
  • ታዲያ ለምን ታባሉታላችሁ?
  • እ…
  • አሁን ይኼን ታሪክ የሠራ ሕዝብ በብሔር ከፋፍላችሁ ማባላቱ ጠቃሚ ነው ትላላችሁ?
  • ኧረ እኛ መቼ አባላነው?
  • ተው እንጂ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምነው?
  • ሰው መቼ ከቦታ ቦታ እንደፈለገው ተንቀሳቅሶ ይኖራል፡፡
  • ይኼ እኮ የአንዳንድ ጠባቦች ሴራ ነው፡፡
  • ይኸው በቅርቡ እንኳን በክልልነት ጥያቄ ቀውስ ስንቶች አይደል እንዴ የተጎዱት?
  • ልክ ነህ፡፡
  • አሁን ደግሞ ሕዝቡ አገራዊ ጥሪ ሲቀርብለት መቼ አሳፈራችሁ?
  • እኛም ከጠበቅነው በላይ ነው የሆነብን፡፡
  • ታዲያ እናንተ ለፖለቲካ ቁማራችሁ እያላችሁ ሕዝቡን ማለያየቱ አይቀርባችሁም?
  • ምን እያልክ ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር አገሪቱ ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እያመራት ያለችው በእናንተ ፖለቲከኞች ስግብግብነትና ራስ ወዳድነት እንጂ ሕዝቡ መቼም ቢሆን ለአገሩ ቅድሚያ እንደሰጠ ነው፡፡
  • እሱንማ አሁን በሚገባ ተረድተናል፡፡
  • ለማንኛውም ሕዝቡን በብሔር እየከፋፈሉ ማባላት ለማንም አይጠቅምም፡፡
  • እ…
  • ስለዚህ ልዩነታችንን ለጊዜው ወደጎን ትተን መተባበሩ ይጠቅመናል፡፡
  • እውነት ነው፡፡
  • አገሪቱ ላለችበት ችግርም መፍትሔው ተገኝቷል፡፡
  • ምንድነው?
  • አንድነት!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ የፖለቲካ ፓርቲ መሪ ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው]

  • ለመሆኑ ተሳተፍክ?
  • በምኑ?
  • በችግኝ ተከላው ነዋ፡፡
  • ምን ዓይነት ጥያቄ ነው?
  • ምኑ ነው ያልገባህ?
  • ጥያቄው ነዋ፡፡
  • እንዴት?
  • ችግኝ መትከል እኮ አገራችንን ነው የሚጠቅመው፡፡
  • እኔም እኮ ለዚያ ነው የጠየቅኩህ?
  • ተክያለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ያው የፖለቲካ ልዩነት ስላለን ምናልባት ላትተክል ትችላለህ ብዬ ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ችግኝ እኮ ፓርቲ የለውም፡፡
  • ቀልደኛ ነህ መቼም?
  • መቼ ነው ግን የሚለወጠው ክቡር ሚኒስትር?
  • ምኑ?
  • የፖለቲካ ሥርዓታችን ነዋ፡፡
  • እንዴት?
  • አገራዊ አጀንዳ ላይ እኮ አንድ ላይ እንተባበራለን ብለን ማሰብ ካልቻልን ያሳዝናል፡፡
  • ያው የፖለቲካ ሥርዓታችን እኮ ሴራ ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ነው፡፡
  • ለነገሩ በብቃትና በአቅም ላይ ቢመሠረት ኖሮ አገራችን አሁን ያለችበት ችግር ውስጥ ባልተዘፈቀች ነበር፡፡
  • የምን ችግር ነው?
  • ምን ችግር ውስጥ ያልተዘፈቀ ነገር አለ፡፡
  • እ…
  • ፖለቲካው ቢሉ ኢኮኖሚው፣ ሁሉ ነገር መላ ቅጡ ጠፍቶታል አይደል እንዴ?
  • ያው ለውጥ ላይ ስለሆንን ነዋ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ለሁሉም ችግር እኮ ለውጡ ሰበብ መሆን አይችልም፡፡
  • ምን?
  • የሆነ ችግር ሲመጣ ለውጥ ላይ ስለሆንን እየተባለ መድበስበስ የለበትም፡፡
  • ለውጡን አትደግፈውም ማለት ነው?
  • ለውጡን ሳይሆን በአገሪቱ ያለውን ቀውስ ነው የማልደግፈው፡፡
  • እ…
  • እናንተ አሁን አሁን ለውጡን እንደ ማርያም መቀነት እያደረጋችሁት ነው፡፡
  • ምን?
  • ለሁሉም ችግር ለውጡ ላይ ነው የምታላክኩት፡፡
  • የለውጡ ተቃዋሚ መሆንህን በሚገባ ተረድቻለሁ፡፡
  • እንዳይመስልዎት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ስለዚህ በቅርቡ ተደራጅታችሁ መንቀላችሁ አይቀርም፡፡
  • ምንድነው የምንነቅለው?
  • የተተከሉትን ችግኞች ነዋ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር በአገሪቱ ከችግኝ ነቀላ በላይ የሚያሳስብ ነገር አለ፡፡
  • ምን?
  • የሕዝብ ነቀላ!

[ለክቡር ሚኒስትሩ የቀድሞ ሚኒስትር ስልክ ደወሉላቸው]

  • እንኳን ደስ አለዎት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለምኑ?
  • ለሪከርዱ፡፡
  • እኛ እኮ ሪከርድ መስበር የለመደብን ነን፡፡
  • ለነገሩ 100 ፐርሰንት ምርጫ በማሸነፍ ሪከርድ የያዝን ፓርቲ ስለሆንን ይኼኛው ብዙም ላያስደንቅ ይችላል፡፡
  • ምን?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • አሁን የእኛን ስም ለማጠልሸት ነው ከማይነፃፀር ነገር ጋር ይኼን የችግኝ ተከላ የምታነፃፅረው?
  • ምን ችግር አለው ክቡር ሚኒስትር?
  • እንዴት ችግር የለውም?
  • 100 ፐርሰንት ፓርላማ ማሸነፋችንን ያፍሩበታል ማለት ነው?
  • እ…
  • እናንተ ቀጣዩ ምርጫ በተያዘለት ፕሮግራም ላይካሄድ ይችላል እያላችሁ አይደል እንዴ?
  • ማን አለ?
  • እሱን እንኳን ተውት፡፡
  • ምን?
  • ለማንኛውም  እንኳን ደስ አለዎት፡፡
  • ለመሆኑ አንተ ችግኝ ተክለሃል?
  • እኔማ ከትጥቅ ትግል ጀምሮ ነበር የምተክለው፡፡
  • የምቆርጠው ማለትህ ነው?
  • ምን እያሉ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • እናንተ አይደላችሁም እንዴ አገሪቱን ባዶ ያስቀራችኋት፡፡
  • ምን?
  • የአገሪቱን ደን እየጨፈጨፋችሁ ስትሸጡ ነበር እኮ፡፡
  • ማን ነው ያለው?
  • እናንተ መቁረጥ እንጂ መትከል አትችሉም፡፡
  • እ…
  • ባይሆን በመትከል የታወቃችሁበት ነገር አለ፡፡
  • ምን በመትከል ነው የታወቅነው?
  • ችግር!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ያደረገው አዋጅ የፍትሐዊነት ጥያቄ አስነሳ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ተቋማዊና...

የሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ሁሴን አህመድ (1930-2015)

ኢትዮጵያ የሁለተኛውን የፋሺስት ጣሊያን ወረራ (1928-1933) በድል ከተወጣች በኋላ...

ከወለድ ነፃ ባንክ የተሰበሰበውን በመቶ ቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለምን ሥራ ላይ ማዋል አልተቻለም?

  ባንኮች ከወለድ ነፃ የሚሰበስቡት ተቀማጭ ገንዘብ መጠን ዕድገት እያሳየ...

መንግሥት ባለፈው ዓመት ለማዳበሪያ የደጎመው 15 ቢሊዮን ብር ለአርሶ አደሮች አለመድረሱ ጥያቄ አስነሳ

መንግሥት ለ2014/15 በጀት ዓመት እርሻ በአፈር ማዳበሪያ ላይ ያለውን...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የመስቀል አደባባይ የመግቢያ ክፍያ ለምን?

ወጣቶች፣ ሕፃናትና አረጋውያን ሳይቀሩ መንፈሳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሐሳባቸውን በነፃነት...

በሕገ መንግሥቱ የተዋቀረው ‹‹የብሔር ፖለቲካ›› እና ‹‹ሥርዓቱ›› ያስከተለው መዘዝና መፍትሔው

(ክፍል አራት) በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ) ባለፈው ጽሑፌ (በክፍል ሦስት) አሁን ያለው...

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብና የመንግሥት መሪ ምሥል

በበቀለ ሹሜ በ2015 ዓ.ም. መጋቢት ወር ውስጥ ይመስለኛል በ‹ሸገር ካፌ›...

ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ያደረገው አዋጅ የፍትሐዊነት ጥያቄ አስነሳ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ተቋማዊና...

ለመጪው ዓመት የሚያስፈልገው 4.3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ 4.4 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይጠይቃል

ለመጪው 2016 ዓ.ም. ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ለታቀደው 4.3...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል ክፍያ መንገድ ብቻ እንዲፈጸም የተላለፈውን ውሳኔ አተገባበር ላይ ስለተነሱ ቅሬታዎች ከባልደረባቸው ጋር እየተወያዩ ነው]

ክቡር ሚኒስትር አተገባበሩ ጥሩ ቢሆንም፣ ከፍተኛ ወቀሳ እየደረሰብን ነው። ዲጂታል የግብይት ሥርዓቱን ለማስፋፋት በመጣራችን መመስገን ሲገባን እንዴት እንወቀሳለን? የሚገርመው በዲጂታል ክፍያ ላይ የተሰማሩ ኩባንያዎች ናቸው በዋነኛነት...