Friday, December 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

የአገራችን የተወሳሰበ ችግር አንድን መሪ በሌላ በመተካት ብቻ የሚፈታ አይደለም!

ክፍል አንድ

 ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

መግቢያ

በየጊዜው የተለያዩ ጸፊዎች አዳዲስ ጽፎችን በመጻፍ ለሰፊው ዝብ ለንባብ ያቀርባሉ፡፡ እንደምገምተው ከሆነ በዚህ መልክ የታሪክን አደራ ለመወጣት በማሰብና አገራቸውም እንዳትበታተን ለማሳሰብ ነው፡፡ ይሁንና ግን አንደኛ የአብዛኛዎች የአጻጻፍ ልት ግልጽ አይደለም፡፡ ሁለተኛ አብዛኛዎች ጽፎች በተወሰነ ሳብ ላይ ያተኮሩና በዚያው ላይ የሚሽከረከሩ አይደሉም፡፡ በሌላ አነጋገር እንድንወያይበትና እንድንከራከርበት በር የሚከፍቱ አይደሉም፡፡ ሁሉም እንደፈለገውና እንደመሰለው የሚጽፍ እን ከተጨባጭ ሁኔታዎችና ከህሊና ሁኔታ በመነሳት ችግራችንን የሚተነትን አይደለም፡፡ስተኛ ደረጃ በአንዳንድ ድረ ገጾች ላይ የሚወጡት ጽፎች በአንድ ግለሰብ ሳብና ዕይ ላይ ያተኮሩ ሳይሆኑ የግለሰብን ስም የሚያድፉ ወይም ሞራሉ እንዲወድቅ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ አሁንም በሌላ አነጋገር ሳይንሳዊ ትንተና መሆናቸው ቀርቶ ተራ እንካ ስላንቲ ወይም ስድብ ናቸው፡፡ ስለሆነም የሚያሰተላልፉት መልዕክት ይህንን ያህልም የሚጨበጥና እንድናስፋፋው ወይም ትችታዊ በሆነ መልክ እንድንገመግመው የሚጋብዘን አይደለም፡፡

እንደሚታወቀው አንድን ብረተሰብ የሚመለከት ተጽፎ በሚቀርብበት ጊዜ የራስን ስሜት ለመግለጽ ተብሎ አይደለም፡፡ እንደሚገባኝ ከሆነ ብረተሰቤ ያገባኛል የሚል ስለዚህም የራሴን አስተዋጽኦ ማበርከት አለብኝ ብሎ ብዕሩን የሚሰነዝር ስለሚጽፈው ነገር አለበት፣ ለምን እንደሚጽፍ መረዳት አለበት፡፡ በሌላ አነጋገር ምን መልዕክትና ትምህርት ለማስተላለፍ እንደሚፈልግ ማውጣትና ማውረድ አለበት፡፡ ምን ይነት የአራር ልት እንደሚጠቀም መገንዘብ አለበት፡፡ ዝም ብሎ በጥሩ አማርኛም ሆነ ንግሊ አቀነባብሮ ለመጻፍ ብቻ ወይስ ሳይንሳዊ የአራር ልትን በመጠቀም በተለይም ታዳጊውን ትውልድ ለማስተማር እችላለሁ ብሎ የበኩሉን አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ከመጀመያውኑ መረዳት አለበት፡፡ ይህም ማለት አንድን ብረተሰብም ሆነ አንድን ሁኔታ የሚመለከት ነገር ለመጻፍ ስንነሳ የተወሰነ ስልትንና ሳይንሳዊ የአተናተን ዘዴን መከተል አለብን፡፡ አንድን የአራር ዘዴና ሳይንሳዊ አተናተንን ያልተከተለ አጻጻፍ የሰውን ጭንቅላት ለማደስና ለማስተማር አይችልም፡፡ ውነተኛውንም የነፃነት መንገድ ይዘን እንድንጓዝ መመያ ሊሆነን አይችልም፡፡ ከተጨባጭ ሁኔታዎችና ከአገዛዝ አወቃቀር፣ እንዲሁም ከአጠቃላዩ ዝብ አስተሳሰብ ተነስቶ የማይጻፍና የችግሮችንም አመጣጥ በተቻለ መጠን ተቀራራቢ በሆነ መንገድ ለማመልክት የማይችል የሰውን አስተሳሰብ በታኝ ብቻ ሳይሆን፣ የአንድን ብረተሰብም ችግር እንዳይፈታ ንቅፋት ይሆናል፡፡  በየጊዜው በኢትዮጵያውያን ድረ ገጾች ላይ በእንግሊኛም ሆነ በአማርኛ የሚወጡትንና ለንባብ የሚቀርቡትን ፎች ስመለከትና ሳገላብጥ ግራ የሚያጋቡኝ ነገሮች አሉ፡፡ ለኢትዮጵያ ዝብና ለአገራችን ተቆርቋሪ ነን ብለውና አጥብቀው የሚሟገቱትን ሰዎች ጽፍ ሳነብ ለምን እንደሚጽፉ፣ ምን ይነት ልትና ሳይንሳዊ ዘዴን እንዲሁም የትኛውን ፍልስፍና መረት በማድረግ እንደሚጽፉ ለማወቅ ግራ ከተጋባሁ ዘመናት አልፈዋል፡፡ የአገራችንም የተወሳሰበ ችግር እንዴት እንደሚፈታና እንደ ብረ ር ወይም እንደ አገር በጠንካራ መረት ላይ በየአቅጣጫው እንዴት መገንባት እንዳለባት የሚጠቁም አጻጻፍ አይደለም፡፡

ስለሆነም አገራችንና ዝባችንን ነፃ እናወጣለን፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ባለቤት በማድረግ የተከበረችና የተፈራች አገር እንዲገነባ እናደርጋለን፣ ሺ በሺ የሚቆጠሩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ሰዎች፣ ፈላስፋዎችና የጥበብ ዎች ለማፍራት የሚያስችል ሠረ መጣል አለብን የምንል ከሆነ ከሳይንሳዊ ጥናትና ትንተና ማለፍ አንችልም፡፡ የፍልስፍና መረትና ምነትም ያስፈልገናል፡፡ ማንኛውም ነገር ምግብ እንኳ ሳይቀር ከሳይንስ አኳያ እየታየ የሚተከልና ለምግብም የሚቀርብ ካልሆነ በሽታን ነው የሚያስከትለው፡፡ በተጨማሪም ከሳይንስ አንፃር እየታየና እየተመጠነ የማይቀቀል ምግብ የመጨረሻ መጨረሻ ጤንነትን ያቃውሳል፡፡ አንድ ፍም እንዲሁ ከሳይንስ አኳያ የማይጻፍና የተወሰነ የአራር ዘዴን የማይከተል ከሆነ የታዳጊን ትውልድ ጭንቅላት ከማደንዘዝ በስተቀር የሚያበረክተው አዎንታዊ አስተዋጽኦ አይኖርም፡፡ ጭንቅላቱ እንዲሾልና ተጨባጩን ሁኔታ በደንብ እየተመለከተ ትንተና ለመስጠት የማይችል ወጣት ትውልድ በሚፈለፈልበት ብረተሰብ ውስጥ ደግሞ ትግል ከስሜታዊነት ሊዘልቅ በፍም አይችልም፡፡ እንደዚህ ይነቱ ትውልድ ደግሞ በራሱ ላይ እንዳይተማመንና ጥቂት ግለሰቦችን እያመለከ እንዲኖር ይገደዳል፡፡  ይህ ይነቱ ሁኔታ ደግሞ የግዴታ ወደ ርስ በርስ መነታረክና ወደ መጨራረስ እንድናመራ ያስገድደናል፡፡ በየካቲቱ አብዮት ወቅት የደረሰው የወንድማማቾች መተላለቅና እስከ ዛሬም ደርሶ እንዳንግባባ ያደረገን ነገር ከዚህ ከሳይንስና ከፍልስፍና ውጭ የተደረገና የሚደረ ትግል መመያችን በመሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም  ከሳይንስ፣ ከፍልስፍና፣ ከዲያሌክቲክና ከሶስሎጂ ውጭ ትግል ማድረግ በመጀመራችን ስንትና ስንት መቶ ዝብ እንዲያልቅ ማድረጋችን ብቻ ሳይሆን፣ ትግሉ ሁለት ትውልድ አልፎ እስከ ዛሬ ድረስ ሲያፋልመንና ሲያነታር ቆይቷል፡፡ በዚህም ከቀጠለ በቀላሉ መቋጠሪያ የሚገኝለት አይመስለኝም፡፡ ይህ ይህንን ችግር ተረድቶ የአመለካከታችን ሁኔታዎች የማንበብ ጉዳይና ከዚያ በመነሳት እንዴት ትንተና ማድረግ እንዳለብን ከአ ዓመታ በላይ የፈጀ ትግል ቢያደርግም ተደማጭነት ሊያገኝ አልቻለም፡፡  በዚህም የተነሳ ሀቀኛውን የትግል ዘዴ ከአሳሳቹና የሰውን ጭንቅላት ከሚያበላሸው የትግል ዘዴ ለመለያየት የቱን ያህል አስቸጋሪ እንደሆነ ከተገነዘብኩኝ ዘመናት አፈዋል።  ይሁንና ግን ደግሞ እጅን አጣጥፎ መቀመጥ እንደ ተሸናፊነት መቆጠሩ ብቻ ሳይሆን ታሪካዊ ወንጀልም እንደ ራት ይቆጠራል፡፡ የድህነቱ ዘመን እንዲራዘምና ዝባችን ውርደትን ተከናንቦ በውጭ ይሎች ዘለዓለሙን እየተናቀ እንዲኖር አስተዋጽኦ እንደማበርከት ይቆጠራል።

ያም ሆነ ይህ እኔም ሆነ ሌሎችም ጻፉ በአጠቃላይ ሲታይ የአስተሳሰብ ለውጥ (Mindset) ማድረግ እስካልቻልን ድረስ ምንም ይነት ለውጥ ልናመጣ አንችልም፡፡ ዛሬ ሞክራሲያዊ ርዓት ሰፈነባቸው የሚባሉትን የምዕራብ አውሮፓ የካፒታሊስት አገሮችን ሁኔታ ስንመለከትና ስንመረምር በየአገሮች ውስጥ የአስተሳሰብ ለውጥ ሳይደረግ ዝም ብሎ በጭፍን ትግል የተካሄደበት ቦታ የለም፡፡ በሌላ ወገን ግን የአስተሳሰብ ለውጥ አንድ ቦታ ላይ በመጫን የሚመጣ ሳይሆን በየጊዜው ራስን በመጠየቅና የጭንቅላት ጂምናስቲክ በማድረግ የሚመጣ ነው፡፡ የታሪክን ደት መረዳት የሚቻለውና የአንድን ብረተሰብ አስቸጋሪ ሁኔታ መገንዘብ የሚቻለው ከሳይንስ አንፃር ትግል ለማድረግ ሲሞከርና ጥረት ሲደረግ ብቻ ነው፡፡ በየጊዜው ጥያቄን ማቅረብ ሲቻል ብቻ ነው ተቀራራቢ መልስ ማግኘት የሚቻለው፡፡ ከዚህ ስንነሳ የተወሳሰበውን የአገራችንን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህልና የ ልቦና ችግሮችን ለመረዳት የግዴታ የአዕምሮን መረታዊ ወይም ቁልፍ ቦታ መረዳት እጅግ አስፈላጊ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ቆንጆም ሆነ መጥፎን ነገር ማድረግ የምንችለው በአዕምሮአችን እየታገዝን በመሆኑ የአዕምሮን ቁልፍ ሚና መረዳቱ በተለያየ መልክ የሚታየውንና የሚገለጸውን ችግር ለመረዳት ያግዘናል።

ዋናው ችግራችን የአዕምሮን ወይም የመንፈስን ትርጉም ያለመረዳት ነው!

እንደሚታወቀውና ሁላችንም የምንቀበለው ሀቅ ማንኛውም ሰው በግልጽ የምናየውና የምንዳስሰው አካል ብቻ ሳይሆን መንፈስም ሆነ አምሮ እንዳለው ነው። እኛም ራሳችን አለን። እንደ አስተዳደጋችን፣ እንደ ትምህርት አቀሳሰማችንና ንቃተ ህሊናችን የማሰብ ኃይላችን፣ አንድን ነገር መረዳትና መተንተን፣ ወይም ያለመረዳትና ለመተንተን ያለመቻል፣ ማውጣትና ማውረድ፣ ግንዛቤን ማሳደር፣ ወይም ግንዛቤ ማሳደር ያለመቻል፣ አርቆ የማሰብ ኃይላችንም ሆነ ያለማሰብ፣ ቁጠኛ መሆንም ሆነ አለመሆን፣ አመኛ መሆንም ሆነ፣ አንድን ነገር በሰላምና በውይይትም ሆነ በክርክር መፍታት መቻል ወይም ያለመቻል፣ ስለሰው ልጅ የሚኖረን ግንዛቤም ሆነ ግንዛቤ ያለመኖር፣ ስለ ነፃነትም ሆነ ስለ ዕድገት የሚኖረን ግምትና ግምት ያለመኖር፣ በጠቅላላው ከየት እንደመጣን፣ በዚህች ዓለም ላይ ለምን እንደምንኖርና ምን መራት እንዳለብንና ወዴት እንደምንጓዝ ማወቅና መረዳት የምንችለው በመንፈስና በአዕምሮ ኃይላችን አማካይነት ብቻ ነው። በአጭሩ፣ መጥፎ ነገርም ሆነ ጥሩ ነገርን ማድረግ የምንችለው በአዕምሮአችንና በመንፈሳችን እየተመራን ነው፡፡ ለማንኛውም ይነት ድርጊታችን፣ በተለይም ለብረተሰብ ዕድገት በሚደረገው ትግል የመንፈስ አወቃቀራችና የንቃተ ህሊናችን ሁኔታ ከፍተኛውን ቦታ ይይዛሉ ማለት ነው፡፡ ከመንፈስና ከአዕምሮ እንዲሁም ከንቃተ ህሊና ውጭ የምናደርገው ምንም ነገር የለም፡፡ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሚዳሰሰውና በግልጽ የሚታየው አካላችን የመንፈሳችን ተገ ወይም በመንፈሳችን የሚመራ ነው፡፡ በሌላ ወገን ግን መንፈሳችን የአካላችን ተገ በመሆን ድርጊታችንን ወደ ማይሆን አቅጣጫ በመመራት ችግር ፈጣሪዎች እንድንሆንና ብረተሰብንም እንድናመሰቃቅል ያደገናል፡፡ ይሁንና ግን የማሰብ ኃይላችን የዳበረ፣ የተወሳሰቡ ነገሮችን መረዳት የሚችልና የመተንተንም ኃይል ካለው የምናደርገውን እናውቃለን ማለት ነው፡፡ መንፈሳችን የሰውነታችን ወይም የአካላችን ተገ መሆኑ ቀርቶ መንፈሳችን የበላይነትን በመቀዳጀት ታሪካዊ ነገሮችን መራት እንችላለን፡፡  

በብዙ ምርምሮችና ጥናቶች እንደተደረሰበት ለአንድ ሰው የማሰብ ኃይልና ማመዛዘን እንዲሁም በረቀቀ መልክ ማሰብ መቻልና ያለመቻል የተወለደበትና ያደገበት ብረተሰብ ወሳኝ ሚናን እንደሚጫወት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የምርት ኃይሎች ማደግ ወይም አለማደግ፣ የባህል ዕድገት መኖር ወይም አለመኖር፣ የከተማዎች በቆንጆ መልክ መራትና ያለመራት፣ በገጠር ውስጥ ማደግና ያለማደግ፣ ወዘተ. በአሰተሳሰባችን ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ይኖራቸዋል። የቤተሰብ ሁኔታ፣ የማበረብ የአኗኗር ልት እንዲሁም አጠቃላዩ የብረተሰብ ወቃቀር የአንድን ሰው አስተሳሰብ ይቀርታል ድርጊቱንም ይወስናሉ፡፡ ለዚህ ነው መጀመያ የግሪክ ፈላሳፎች ምርምር ሲጀምሩ ለአዕምሮ ከፍተኛ ቦታ የሰጡት፡፡ነሱ ምነትም የማንኛውም የሰው ልጅ ድርጊት በአርቆ የማሰብና ያለማሰብ ኃይሉ የሚወሰን ሲሆን፣ ይህ በአንፃሩ ደግሞ ሊወሰን የሚችለው በቀሰመው ዕውቀት አማካይነት ብቻ ነው፡፡ በተለይም ሶፊስቶችን አጥብቀው ይዋጉ የነበሩት ሶክራተስና ፕላቶ አርቆ የማሰብ ኃይልን ሚና ሲያነሱ ትክክለኛ ዕውቀት ለማሰብ ኃይላችንና ለፈጠራ ራችን የቱን ያህል ወሳኝ ሚና እንዳለው በማስመር ነው፡፡ ለዚህም ነው በሚታዩ ነገሮች ላይ ብቻ ያተኮረውንና በጥቂት ሰዎች ተደንግጎ የሚቀርበውን ግም ሆነ ዕውቀት እንደ መመያ አድርገው ማስተማርና መስበክ የጀመሩት ሶፊስቶችን ወይም የተሙለጨለጨ አስተሳሰብ ያላቸውን ምሁሮች አጥብቀው መዋጋት የጀመሩት፡፡ በሶክራተስና በፕላቶም ምነት ግሪክ በጊዜው የነበራትን የበላይነትና ኃያልነት ልትነጠቅና የመጨረሻ መጨረሻም ልጣኔዋ ሊዳከም የቻለው በጊዜው የነበሩት አገዛዞች በሶፍስቲያዊ ዕውቀት በመልጠናቸውና ከዚህም በመነሳት በልጣንና በሀብት በመመካታቸውና በመባለጋቸው ነበር፡፡ ሌሎች ልጣኔዎችና ኃያላን መንግታትም ሊፈራርሱና ሊወድሙ የቻሉት በጉልበትና በሀብት በመመካት ብቻ በመስፋፋታቸውና የመጨረሻ መጨረሻ ኃይላቸው በመዳከሙ ነው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን፣ የአዕምሮና የመንፈስ አለመዳበር፣ አርቆ አለማሰብና ባሉት ነገሮች ብቻ ጠግቦ ወይም ተደስቶ መኖርና፣ ይህንን እንደ ባህል አድርጎ ማስፋፋትና ማስተማር ለዕድገት ከፍተኛ እንቅፋት እንደሚሆን የታወቀ ጉዳይ ነው። ፈላስፋዎች ትችታዊ አመለካከት ወይም እየመላለሱ መጠየቅ የሚሉት ቁም ነገር አለ። ይህም ማለት አንድ የሚነገርን ነገር ዝም ብሎ መቀበል ሳይሆን መመርመርና ትክክል መሆኑና አለመሆኑን በጥያቄ ውስጥ ማስቀመጥ እንደሚያስፈልግ አጥብቀው ያስተምራሉ፡፡ ስለሆነም በፕላቶ ምነትና መመያ አንድን ነገር ዝም ብሎ ከመቀበል በፊት የግዴታ እየመላለሱ መመርመርና ማገናዘብ እንደሚያስፈልግ ያተምራል፡፡ አንድ ነገር ተቀባይነትን ከማግኘቱ በፊት በዲያሊክቲክና በፍልስፍና መነጽር መመርመርና መታሸት አለበት፡፡ በዚህ አማካይነት ብቻ ሀቀኛውን ከአሳሳቹ፣ ለዕውቀትና ለልጣኔ የሚታገለውን ለልጣንና ለራሱ ዝና ብቻ ከሚታገለው ነጥሎ ማወቅ ይቻላል፡፡ ይህንን ሳያደርግ ዝም ብሎ በጭፍን በትግል ለም ውስጥ የገባ የአንድ ሰው ወይም የአንድ ድርጅት ጭራ በመሆን የራሱን ነፃነት ማጣቱ ብቻ ሳይሆን ለውነተኛ ዝባዊ ነፃነት የሚደረገውን ትግል ያደናቅፋል፡፡ በየጊዜው ጠብ ጫሪ በመሆን ብረተሰብዊ ስምምነት እንዳይኖር በማድረግ የአንድ ዝብ ዕድል በውጭ ኃይሎች እንዲወሰን ያደርጋል፡፡

በአጠቃላይ ሲታይ መንፈስ ወይም አዕምሮ በመረቱ የቆንጆ ነገሮች ማፍለቂያ ነው፡፡ አንድን ነገር በ ሥርዓት እንድንራ ወይም እንድናደራጅ፣ እንድናቅድ፣ እንድናቀናጅና መልክ እንድንሰጠው የሚመራን ነው። መንፈስ ወይም አዕምሮ የሙዚቃ፣ የዕል በአጠቃላይ ሲታይ ደግሞ የዕውቀት ምንጭ ሲሆን፣ በዚህ እየተመራን ቆንጆ ቆንጆ ነገሮችን እንድናስብና ተግባራዊ እንድናደርግ መመያ የሚሰጠን ነው፡፡ ለይወታችን ትርጉም እንድንሰጠው ሰው መሆናችንን የሚያረጋግጥልን ልዩ ነገር ነው፡፡ እንደሚባለው መንፈሱ ቆንጆ የሆነና የማሰብ ኃይሉ የዳበረ ሰው ተዓምር ይራል፡፡ በረሃውን ወደ ገነት መለወጥ ይችላል፡፡ ልዩ ይነት ቅርና ውበት በመስጠት የሰው ልጅ ኑሮ ዝርክርክ እንዳይሆን ያደርጋል። ስለሆነም ቆንጆ መንፈስ የፍቅር፣ የሰላም፣ የርዓት፣ የጥበብና የፈጠራ ምንጭ ነው፡፡ በአንፃሩ ደግሞ መንፈሱ የተረበሸ ወይም በልጅነቱ በደንብ ያልተኮተኮተ የተቃራኒውን የሚያደርግ ነው፡፡ ከበጎ ነገር ይልቅ ክፉ ነገርን የሚሻ መንፈሱ ለተንኮል ብቻ የተፈጠረ ይመስል ተንኮልን የሚያውጠነጥን፣ ከፍቅር ይልቅ ጦርነትን የሚናፍቅ፣ የሌላውን ሰው ደስታ የማይሻ፣ በሰው ስቃይ የሚደሰት፣ ስለሆነም ሰውን በመጉዳት ወይም ተንኮል በመራት የተሻለ ነገር የሚያገኝ የሚመስለው፣  በአጠቃላይ ሲታይ የአንድ አካባቢ ዝብ በሰላምና በደስታ ቢኖር ደስ የማይለው ነው፡፡  ከመሰሉ ጋርም በማበር ዘለዓለማዊ ጦርነት እንዲሰፍን የሚያደርግና የአንድ ገር ሀብትና የታሪክ ቅርስ እንዲወድም የሚያደርግ ነው። በመሆኑም በራሱ ስግብግብ ፍላጎት በመመራትና ከውጭ ኃይሎች ጋር በመተባበር አንድ ዝብ ታሪክ እንዳይራ እንቅፋት የሚሆን ነው፡፡ እንደዚህ ይነቱ ሰው የማሰብ ይሉን በሚገባ የማይጠቀም ሰው መሆኑን የዘነጋና ታሪካዊ ኃፊነትም እንዳለበት የሚገነዘብ አይደለም፡፡ አንድ ቦታ ላይ ቆሞ ድርጊቱን የሚያወጣና የሚያወርድ፣ እንዲሁም የሚያመዛዝን አይደለም። በአጭሩ መንፈሱ የተሰለበና የሚራውን የማያውቅ፣ እንዲሁም ለመኖር ብቻ የሚኖር የሚመስለው ነው።

ጭንቅላታችን አርቆ የማሰብ ኃይል ያለውን ያህል ሌሎች የሰው ልጅ ባህርያት ሊገለጹና ተግባራዊ ሊሆኑ የሚችሉት በማሰብ ኃይላችንና በቀሰምነው ዕውቀት አማካይነት ብቻ ነው፡፡ የመንፈስ ጥንካሬና በመርህ (ፕሪንፕል) መመራት በቀላሉ ያለመታለልና ያለመደለል፣ ለምናምነው ዓላማ መቆምና እሱን በጥሞናና በውይይት ለማሳመን መሞክር፣ ለነፃነት መቆምና ለሌላው ላልተማረው ጠበቃ መሆንና ውነተኛውን የነፃነት ፈለግ እንዲከተል መንገዱን ማሳየት፣ የአንድን ብረተሰብ ሁኔታና ችግር ከብዙ አኳያ ማየትና መገምገም፣ ከዚህም በመነሳት ለልጣኔ መቆምና እስከ መጨረሻው መታገል፣ እነዚህና ሌሎች ነገሮች ሁሉ በጭንቅላታችን ውስጥ የሚውጠነጠኑና የሚገነቡ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ለምን በተለያዩ ሰዎች ዘንድ የተለያየ አስተሳሰብ ብቻ ሳይሆን፣ ከላይ የዘረዝርኳቸው ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ ብለን? ጥያቄ በምናስቀምጥበት ጊዜ የምናገኘው መልስ በአጭሩ አስተዳደጋችንና የገበየነው ዕውቀት ወሳኝ ሚናን እንደሚጫወቱ እንደሆነ መገንዘብ እንችላለን። በተለይም የአንድ ብረተሰብ አወቃቀርና የታሪክ ደት እንዲሁም የባህል ሁኔታ ባህሪያችንን ይወስኑታል፡፡ ስለዚህም ነው ማንኛውም ግለሰብም ሆነ ድርት ከሞላ ጎደል የብረተሰቡ ግልባጭ ወይም ኮፒ ነው የሚባለው፡፡  ከዚህ ስንነሳ አንደኛው ቀጣፊና ውሸታም፣ አድሪና ወላዋይ፣ አጎብዳና ነገር አቀባይ፣ ራሱን ለሌላው ለመሸጥ የሚዘጋጅ፣ ሰላይና በራሱ ላይ ምነት የሌለው፣ እንደየሁኔታው ሳቡን የሚቀያየር፣ አለሁ አለሁ ባይነት የሚያጠቃው፣ ስግብግብነትና አገር ለመሸጥ መዘጋጀት፣ ለገር ነፃነት ጥብቅና ከመቆም ይልቅ የሌላውን አገር ጥቅም በማስቀደም አገር ማፈራረስ፣ ታሪክን በተጣመመ ሁኔታ ማቅረብና ሌላውን አሳስቶ አንድ ዝብ ተስማምቶ እንዳይኖር ማድረግ፣ ጠባብ አስተሳሰብ እንዲስፋፋ በማድረግ ግለሰቦችም ሆነ የተለያዩ ምነት ተከታዮችም ሆነ ከዚህም ሆነ ከዚያ ብረሰብ የተወለዱ በጥላቻ መንፈስ በመጠመድ በመፈራራትና የጎሪጥ እየተያዩ እንዲኖሩ ማድረግ፣ ቀጥሎም ወደ ጦርነት እንዲያመሩ ማድረግ፣ ለውንብድና በመዘጋጀት አንድን አገር የጦር አውድማ በማድረግ ታሪክ እንዳይራ ማድረግ፣ እነዚህ ሁሉ በማሰብ ኃይል ድክመትና በተሳተ ዕውቀት ምክንያት የሚፈጠሩ ድርጊቶች ናቸው፡፡ በተጨማሪም በተንኮል ተጠምዶ ሌላውን ከሱ የላቀን ሰው ለማጥፋት የሆነ ያልሆነ ምክንያት መፈለግና ስም ማጥፋት የጭንቅላት አርቆ ለማሰብ ችግር ነው፡፡ በተሳሳተ ዕውቀት በመመራትና በዚህም ምክንያት ጭንቅላት በትክክል ለመገራት ያለመቻሉ የሚገለጽ ችግር ነው፡፡ በተጨማሪም ሌላው ደግሞ የአንድን ተንኮለኛ አነጋገር ሰምቶና አምኖ የሚያስተጋባና ለትግል እንቅፋት የሚሆን እንደዚሁ ጭንቅላቱ በደንብ ያልተገራ ወይም ደግሞ የቀጨጨ አስተሳሰብ ስላለው ነው።

ይህም ማለት ምን ማለት ነ? ለአንድ ዝብ በሰላም መኖር፣ ራሱን መለወጥና ማደግ እንዲሁም ታሪክ መራት መንፈስ፣ ጭንቅላትና አዕምሮ ከፍተኛ ሚናን የሚጫወቱ ብቻ ሳይሆኑ ወሳኞችም ናቸው፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ አንድ ሰው የፈለገውን ያህል የተማርኩ ነኝ ቢልም ና አር ጊዜ ካለ እኔ በስተቀር ታጋይ የለም እያለ ቢምልና ቢገዘትም ጭንቅላቱ ውስጥ የተቀበረውን ወደ መጥፎ ነገርና ተንኮል እንዲያመራ የሚያደርገውን የተወላገደ ባህ ማስወገድ እስካልቻለ ድረስ በምንም ይነት ለብረተሰብ ዕድገትና ለነፃነት አስተዋጽኦ ሊያበረክት አይችልም፡፡ በአገራችንም ሆነ በልዩ ልዩ አገሮች የደረሱትን ዕልቂቶች፣ የታሪክና የሀብት ውድመቶች፣ የዝብ መበታተንና በሌላ አገር ባክኖ እንዲኖር ማድረግ፣ በአጠቃላይ ሲታይ ለዕድገት እንቅፋት መሆን ዋናው ምክንያት በትንሽ ዕውቀት እየታገዘ ልጣን ለመውጣት እታገላለሁ በሚል አጉል ግብዘኛ ምክንያት የተነሳ ነው፡፡ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ባልተማሩ ስዎች ወይም በደ ገበሬና ወዝ አደር ጦርነት የተቀሰቀሰበትና አገር የወደመበት ሁኔታ በፍም አልታየም አልተመዘገበምም። እስከ ዛሬ ድረስ ብዙ አገሮች የወደሙትና በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ዝብ እንዲያልቅ የተገደደው ተማርኩ ባሉ ጥቂት ኤሊቶች አማካይነት ነው፡፡ የሰውን ልጅ ለመግደልና ለማሰቃየት ተብለው የሚሩት የተወሳሰቡ መሪያዎች በተማሩ ሰዎች አማካይነት ነው፡፡ ትዕዛዝ የሚሰጡትም እንዲሁ በዝብ ተመርጠናል ውክልናን አግኝተናል ብለው በሚዘባነኑ ፖለቲከኞች አማካይነት ነው፡፡ ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ውዝግብ፣ በሃይማኖት አሳቦ ዕልቂት ማስከተል፣ የብዙ ሺ መታትን ታሪክና ባህል ማውደምና የብዙ ሺ ዎችን ይወት መቅሰፍ ስንመለከት የምንደርስበት መደምደሚያ ይህ ሁሉ አሰቃቂ ግፍ የሚፈጸመው በሀብት በናጠጡና በልጣን ጥም በሰከሩ ኤሊት ነን በሚሉት አማካይነት ነው፡፡ ወይም ደግሞ አንድን መመያና ዕውቀት የሚሉትን ራሳቸው በፈለጉት መልክ ስለሚተረጉሙት ብቻ ነው፡፡  የዩሁዲው ማርክሲስትና ምሁር አዶርኖ እንደሚለው ለዚህ ዋናው ምክንያት ገለብ ገለብ ያለ ዕውቀት ነው፡፡ምነት የታሪክን ደትና አመጣጥ የአንድን ብረተሰብ አወቃቀር ውጣ ውረድነት ያለው መሆኑን ያልተገነዘበ ኤሊት በስሜት ብቻ እየተነዳ የሚያካሂደው ፖለቲካ የሚሉት ፈሊጥ የግዴታ ለታሪክ መበላሸት፣ ለዝቦች ዕልቂትና ለአገር መፈራረስ ዋናው ምክንያት ይሆናል፡፡ ትለር በስድስት ሚሊዮን ዝቦች ላይ ያደረገው ዕልቂትና የሌሎችንም አገሮች በመውረር ወደ ሃምሳ ሚሊዮን የሚጠጋ ዝብ እንዲሞትና አገሮችም እንዲፈራርሱ የተደረገው ይሁዲዎች ለጀርመን ልጣኔ ያደረጉትን አስተዋጽኦ ለመገንዘብ ባለመቻሉና ወደ ኋላ መለስ ብሎ የታሪክን ደት ለማጥናት ባለመቻሉ ብቻ ነው፡፡ በዘረኝነት ቲዎሪ በመመራቱና የጀርመንም ዝብ ከሁሉም ዘር በላይ ይበልጣል ብሎ በማመኑ ነው፡፡ ይህም የሚያረጋግጠው የተቆራረሰ ዕውቀት ጭንቅላትን እንደሚጋርድና ሌላውን በመናቅና በማንቋሸሽ ለብዙ ሚሊዮን ዝቦች መሞትና ለባህልና ለታሪክ መፈራረስ ምክንያት እንደሚሆን ነው፡፡ የአገራችንንም የአብዮት ታሪክና የደረሰውን ዕልቂት ስንመረምር ለችግሩ መንስ የሆኑ ሰዎች ተማርን የሚሉ ሲሆኑ  የታሪክን ውጣ ውረነት ያልተገነዘቡ፣ በየታሪክ ደረጃዎች ላይ የነበረውን ንቃተ ህሊና ያላገናዘቡ፣  አንድ ብረተሰብም ሆነ አገር ለመረጋጋትና ታሪክን ለመራትና እንዲራበትም ለማድረግ አንድ ዝብና አገዛዝ ብረተሰብዊ መመሰቃቀሎችንና ውህደቶችን ማለና ራሳቸውን ለመገንዘብ በብዙ መቶ መታት የሚቆጠር ዕድሜ እንደሚያስፈልግ ባለመረዳታቸው ነው፡፡ ፍሪድሪሽ ሽለር የተባለው ታላቅ የድራማ፣ የፍልስፍናና የሳይንስ ምሁር እንደሚያስተምረን የሰው ልጅ ራሱን በራሱ እስኪያገኝ ድረስ ብዙ ውጣ ውረዶችን ማለፍ እንዳለበት ነው፡፡ እሱ ምነት የሰው ልጅ አርቆ የማሰብ ኃይሉን ማዳበር ከፈለገ የግዴታ መንፈሱ ከልጅነቱ ጀምሮ በጥሩ ዕውቀትና ጥበብ መኮትኮት አለበት፡፡ ጥበባዊ ጭንቅላትን የመኮትኮቻ ትምህርት (The Aesthetic Education of the Human Mind) በሚለው መጽፉ ውስጥ የሚያመለክተውና የሚያረጋግጠው ይህንን ነው፡፡ የሰው ልጅ ጭንቅላት ከልጅነቱ ጀምሮ በጥሩ ውቀት እስካልተኮተኮተ ድረስ ሰብዊ ባህ ሊኖረው አይችልም፡፡ ቆንጆና የተረጋጋ ማበረሰብም ሊገነባ አይችልም፡፡ ሜንደልሰን የሚባለውና የጀርመኑ ሶክራተስ እየተባለ የሚጠራው ይሁዳዊው ምሁርም የሚያረጋግጠውም ይህንን ነው፡፡ ጭንቅላቱ በሚገባ ያልተኮተኮተና ያልዳበረ እንደ አውሬ እንደሚሆንና ለሌላው እሱን ለሚመስለው ሰው ምንም ይነት ርህራ እንደማይኖረው ነው፡፡ ኢማኑኤል ካንትም በተለይም በሰው አዕምሮ ላይ ከፍተኛ ትኩሮ በመስጠት የሰው ልጅ በአጠቃላይ ሲታይ ወደ ውስጥ ራሱን መመልከት እንዳለበትና ድርጊቱን ሁሉ መቆጣጠር እንዳለበት ያስተምራል። አዌርነስ (Awarness) በሚለው ሀተታው የሰው ልጅ የግዴታ ለድርጊቱ ሁሉ ተገቢውን ግንዛቤ ማድረግ እንዳለበት ያስተምራል፡፡ በመሆኑም የሰውን ልጅ የጭካኔ ባህ የተረዱት የ18ኛው እና የ19ኛው ክፍለ ዘመን የጀርመን ምሁራን ምርምር ያደርጉ የነበረውና አጥብቀውም ያነሱ የነበረው የሰውን ባህ በመኮትኮት ጤናማ አስተሳሰብ እንዲኖረው ማድረግ ነበር፡፡ ጠቅላላው የጀርመን ፈላስፋዎች ምርምርም በዚህ ዙሪያ ያተኮረ ሲሆን፣ አንድ ዝብ ታሪክን ሊራ የሚችለው በየጊዜው ራሱን መጠየቅና ጭንቅላቱን መኮትኮት የቻለ እንደሆን ብቻ ነው፡፡ የሚያስገርውና የሚያሳዝነውም በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ፈላሳፋዎችና ምሁራን ብቅ ባሉበትና ሳይታክቱ ባስተማሩበት፣ እንዲሁም ትምህርታቸውን ተግባራዊ ባደረጉበት አገር ትለርና ፋሺዝም መነሳታቸውና ለብዙ ሚሊዮን ዝብ መሞት ምክንያት መሆናቸው ነው፡፡

ወደ አገራችን ስንመጣም ያለው ችግር ለመንፈስና ለአዕምሮ መዳበር አትኩሮ ያለመስጠትና የመንፈስ መበላሸትም ሆነ በጥሩ ዕውቀት መኮትኮት ያለውን አሉታዊና አዎንታዊ ሚና ያለመገንዘቡ ነው፡፡ ለአንድ አገር ዕድገት፣ አንድ ዝብ ኋላ ቀር ከሆኑ አመለካከቶች ተላቆ በመተባበር አገር እንዲገነባ ከተፈለገ ትክክለኛ ዕውቀት አስፈላጊና በዚህ ላይ መረባረቡ የሁሉም ነገር ቁልፍ መሆን ግዛቤ ያለመደረጉ ነው፡፡ በመሆኑም በተለይም ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት በኋላ የገባው ይህንንም ያህል ለጭንቅላት መዳበር፣ ለአርቆ አሳቢነትና ለፈጠራ ራ የማያመቸው ትምህርት ብረተሰብዊ መዘበራረቅን እንዳስከተለና አቅጣጫ እንዳሳጣን ምርምር ያለመደረጉ በጣም የሚያሳዝንም የሚያስገርምም ነው፡፡ ይህ ይነቱ ቸልተኝነትና ንቀት ደግሞ የግዴታ በየኤፖኩ (በየዐረፍተ ዘመኑ) የተነሱትን ሁኔታዎች እንደፈለግን ልንተረጉማቸው ተገደናል፡፡ ለምሳሌ አብዛኛው ተንታኝ በአብዮቱ ወቅት የተፈጠረውን ትርምስና እጅግ ለጭንቅላት የሚዘገንን ድርጊት ለማያያዝ የሞከረው ዝም ብሎ በደፈናው ከማርክሲዝም ጋር ነው፡፡ ፊውዳሊዝምና እጅግ ተበጣጥሶ የገባው የካፒታሊዝም የፍጆታ አጠቃቀምና አመራረት በህሊና አወቃቀራችንና በመፈሳችን መበላሸት ላይ ያለውን አሉታዊ ተፅዕኖ የተገነዘበ ያለ አይመስለኝም፡፡ ስለዚህም አብዛኛው ሰው ወይም ምሁር ነኝ ባይ በአብዮቱ ጊዜ የደረሰውን ዕልቂትና መተራረድ የተገነዘበው ከውጭ ከመጣው የማርክሲስት ሌኒንስት ዕዮተ ዓለም ጋር በማያያዝ ነው፡፡ ለምሳሌ የኢትዮጵያ የጦር ኃይል እንዳለ የለጠነው በአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝም የጦር ሳይንስ በሚሉት ነው፡፡ ሪያዎቹም የመጡት ከዚያ ነው፡፡ ፖሊሱ ደግሞ በጀርመን ፖሊሶች የሠለጠነ ሲሆን፣ የማሰቃያ መሪያዎችም በሙሉ ከዚያ የመጡ ነበሩ፡፡ በሌላ አነጋገር የኢትዮጵያ የጦር ኃይልና ፖሊስ በኢምፔሪያሊዝም የጭቆናና የማሰቃያ እንዲሁም ሰውን የመግደያ ልት ነው የለጠነው፡፡ ስለሆነም በአብዮት ጊዜ የተካሄው መተላለቅ ከማርክሲዝምና ከሶሻሊዝም ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡ ማርክሲዝምና ሶሻሊዝም የብዙ መቶ መታትን የደነደነ አስተሳሰብና መንፈስ በተወሰነ ጊዜ ውስጥ የመቀየር ኃይል የላቸውም፡፡ የሰው ልጅ የማሰብ ይል በክንውንና በደት ውስጥ የሚቀረ ነው፡፡ በተለይም ፍሪድሪሽ ሄግል ይህንን ነው የሚያስተምረን፡፡

ከዚህ ስንነሳ በአጠቃላይ ሲታይ የብዙ የስተኛውን ዓለም አገሮች የተዘበራረቀ ሁኔታና የየመንግታቱን የመጨቆሪያና አለመደላደልን ስንመለክት ከአገራችን ሁኔታ ጋር ተመሳሳይነት አላቸው፡፡ የሚለዩት ግን አብዛኛዎቹ አገሮች እንደኛው በፊዳል ርዓት ውስጥ አለማለቸው ብቻ ነው። ያም ሆነ ይህ የአንድን ብረተሰብ ዕድገት ሁለንተናዊ ከሆነ ሁኔታ ያላጤኑ መንግታትና ሁለገብ ዕርምጃ ለመውሰድ ያልሞከሩ አገሮች አንዳች ነገር በሚፈጠርበት ጊዜ ወደ መረጋጋት ከመምጣት ይልቅ ወደ ውዝግብና መተረማመስ ያመራሉ፡፡ በአገራችን በአብዮቱ ዘመን የታየው የመንፈስ መረበሽና ለጭንቅላት የዘገነነ ድርጊት ዋናው መነሾው ጭንቅላትን ለማደስና መንፈስን ለማረጋጋት የሚያስችል ዕውቀት ባለመስፋፋቱ ብቻ ነው፡፡ ዛሬም ያለው ችግርና የዝብ መፈናቀልና የመንግትም ቸልተኝነት ዋናው ምክንያት ሰው መሆናንን የሚያረጋግጥልንና ታሪክ ሪ መሆናችንን የሚያስጨብጠን ዕውቀት ከጭንቅላታችን ጋር እንዲዋሃድ ባለመደረጉ ነው፡፡ ስለሆነም አብዮቱ ከመተባበር ይልቅ ቡድናዊ ስሜትን አጠናከረ፡፡ ወደ ጤናማ ፉክክር ሳይሆን ወደ ጦርነት የሚያመራና ደም መፋሰስን ወደ ሚያስከትል አጉል እልከኝነት ውስጥ ከተተን፡፡ ሁሉም በየፊናው በመራወጥ አሸናፊ ሆኖ ለመውጣት ዝግጅት ማድረግ ጀመረ፡፡ ሁሉም በየፊናው በቀላሉ ድልን የሚቀዳጅና ልጣን የሚጨብጥ መስሎ ታየው፡፡ረሰቤን ነፃ አውጣለሁ ብሎ የሚታገለው ደግሞ አገሪቱን ወደ ጦር ውድማነት ለወጣት፡፡ አብዛኛው ታጋይ ነኝ ባይና ቢሮክራሲው ሁሉ ሳይቀሩ የኢትዮጵያ ላቶች ሆኑ፡፡ልጣኔና የዕድገት ጠንቅ በመሆን ውስብስብ ሁኔታዎችን ፈጠሩ፡፡ በመረቱ እነዚህ ሁሉ ኃይሎች ትንሽም ቢሆን ፊደል የቆጠሩና የተማሩም ነበሩ፡፡ የተማሩት ትምህርት ግን የማሰብ ኃይላቸውን እንዲጠቀሙ አላገዛቸውም፡፡ የመንፈስን የበላይነት በማስቀደም የወንድማማች ደም እንዳይፈስ ጥረት እንዲያደርጉ አላስቻላቸውም፡፡ በተንኮልና አገርን በማፈራረስ፣ እንዲሁም ሳይቀድመኝ ልቅደመው በሚል ፈሊጥ በብዙ መቶ ሺ የሚቆጠሩ ለጋ ወጣቶች ይወታቸውን እንዲያጡ ሁኔታውን አመቻቹ፡፡

ያም ሆነ ይህ በአጠቃላይ ሲታይ የሰው ልጅ ጭንቅላትም ሆነ መንፈስ አንድ ይነት ቅር ነው ያላቸው፡፡ ይህም ማለት በየትኛውም አገር የተወለደና ያደገ ሰው ሁሉ ሁሉም የው ልጅ ባህሪዎች ይኖሩታል፡፡ ከላይ እንዳልኩት የየግለሰቡ ባህና ድርጊት ሊቀረና ሊወሰን የሚችለው በአስተዳደጉ፣ በአካባቢው ሁኔታና በአጠቃላይ ሲታይ ደግሞ በጠቅላላው የኢኮኖሚ፣ የማበራዊና የባህል ዕድገት ሁኔታ ነው፡፡  ይሁንና ግን አንዳንድ ሰው ሲወለድ ከመጀመያውኑ ተቀድሶ የሚወለድና ጭንቅላቱ ወደ ተንኮልና ወደ መጥፎ ነገር የማያመራ አለ፡፡ ይህ ባይሆን ኖሮ እንደ ሶክራተስና ፕላቶንን፣ እንዲሁም ታላላቅ የሳይንስና የፍልስፍና ዎች የመሳሰሉት ብቅ ባላሉ ነበር፡፡ እንደዚህ ይነት ሰዎች ደግሞ ወደ እግዚአብሔርም የሚጠጉ ናቸው፡፡ ለጥሩ ነገር እንጂ ለመጥፎ ነገር ያልተፈጠሩ ጠቅላላው አስተሳሰባቸው የሰውን ልጅ ታሪክ ሪነት ማስታወስና ማስተማር ተልዕኳቸው የሆነ ልዩ ይነት ፍጡሮች ናቸው። በመሆኑም እንደነዚህ ይነት ስዎች ባይፈጠሩ ኖር የሳይንስና የቴክኖሎጂ ባለቤት መሆን ባልቻልን ነበር፡፡ ኑሮአችን ሁሉ የጨለመና እየተንከራተትን እንደ እንስሳ የምንኖር ነበርን፡፡  ተግባራችን ሁሉ ጦርነትና መተላለቅ ብቻ በሆነ ነበር፡፡  የዓለምና የሰው ልጅ አስደናቂውና በቅራዎች መወጠር የሚያስገርመው ነገር እዚህ ላይ ነው፡፡ በአንድ በኩል ለቅዱስ ራ የተፈጠሩና የተካኑ፣ በሌላ ወገን ደግሞ ለተንኮልና ለጥፋት እዚያው በዚያው መኖራቸው የሰው ልጅና የተፈጥሮ ግዴታ ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ ጨለማና ብርሃን፣ የሚያቃጥልና ቀዝቃዛ ነገሮች እንዳሉ ሁሉ የሰው ልጅ ባህም በአጥፊዎችና በተንኮለኞች በአንድ በኩል፣ በሌላ ወገን ደግሞ በፈጣሪዎችና ለተቀደሰ ዓላማ በቆሙ ሰዎች የሚገለጽ ነው፡፡

ከዚህ ስንነሳ የጭንቅላትን ሚና ታሪክ ሪነትና አጥፊነትን መረዳቱ የሚታለፍ ነገር አይደለም፡፡ እንደገና የፕላቶንን ቁም አባባል ለማስታወስ፣ የሰው ልጅ ችግር አርቆ አለማሰብና በትክክለኛ ዕውቀት አለመኮትኮት ነው፡፡ ለመጥፎ ድርጊትና ለችግር መፈጠር እንዲሁም ለጥሩ ራ ዋናው ተጠያቂው የሰው ልጅ ራሱ እንጂ ከላይ ሆኖ የሚቆጣጠር ኃይል ወይም ደግሞ አንዳች ይነት ርዕዮተ ዓለም በመከተሉ አይደለም፡፡ እንደየአስተዳደጋችን እኛው ራሳችን የአስተሳሰባችንና የድርጊታችን ተጠያቂዎች ነን፡፡ ሌላ ሰው የሚያሳስተን ከሆንና የሱን አስተሳሰብ ተከትለን ወደ መጥፎ ነገር የምናመራ ከሆነ ጭንቅላታችን በጥሩ ዕውቀት አልተኮተኮተም ማለት ነው፡፡ የማመዛዘንና ጥያቄን የመጠየቅ ልምድ አላካበትንም ከጭንቅላታችንም ጋር አልተዋሃደም ማለት ነው፡፡ ዝም ብለን የምንመራ፣ ሌላው ሲጮህ የእሱን የምናስተጋባ ከሆነ ጭንቅላታችን ውነተኛ ነፃነትን አልትጎናፈም ማለት ነው፡፡ ውነተኛ ግለሰባዊነትና በራስ ላይ መተማመንን አላዳበርንም ማለት ነው፡፡ በጭፍን የምንመራ እንጂ በራሳቸን የማሰብ ኃይል የምንመራ አይደለንም ማለት ነው፡፡ እንደዚህ ይነት ሰዎች ደግሞ ማንኛውንም መጥፎ ነገር ከመራት አይቆጠቡም፡፡

ሁለገብ የመንፈስ ተሃድሶ ዘዴ የሰላምና የዕድገት ዋናው ቁልፍ ነው!

በታሪክ ውስጥ ልጣኔና ዕድገት የተካሄደባቸውንና የሰውም ልጅም ውነተኛ ግለሰባዊ ነፃነትን የተቀዳጀበትን ሁኔታና ታሪክን ስንመለከት የመንፈስ ተድሶ መሠረታዊ የሆነና ከፍተኛውን ሚናም እንደሚጫወት እንገነዘባለን፡፡ በታሪክ ውስጥ የመጀመያው ሁለገብ የመንፈስ ተሃድሶ ተግባራዊ የሆነው ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ክፍለ ዘመን ሲሆን፣ ይህንንም ተግባራዊ ያደረገው ሶሎን የሚባለው ታላቅ ፈላስፋና የአገር መሪ ነበር፡፡ ለሶሎን መነሳትና የተቀደሰ ድርጊት ደግሞ ቀደም ብለው የተካዱት በተፈጥሮ ፈላስፋዎች የተደረጉት ምርምሮችና የሆሜር ድርሰት ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል ማለት ይቻላል፡፡ በጊዜው የነበረውን የእርስ በርስ ጦርነትና የገመደቦችን ቅጥ ያጣ ብዝበዛና ግፍ የተመለከተው ከመሳፍንት ዘር የተወለደው ሶሎን በጊዜው የነበረውን አስቀያሚ ሁኔታ ያያዘው ከመንፈስ ወይም ከአዕምሮ መበላሸት ወይም በጥሩ ዕውቀት ካለመታነ ጋር ነው፡፡ ስለሆነም ልጣን ሲጨብጥ በአካባቢው ያሉትን በማሳመን ሁለገብ ጥገናዊ ለውጥ በማካሄድ በታሪክ ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ልዩ ይነት በሳይንስ፣ በሒሳብ፣ በፍልስፍና፣ በድራማና በአርክቴክቸር የሚገለጽ የዕውቀት መረት ይጥላል፡፡  ለሶክራተስ፣ ለፕላቶን፣ ለአርቺሜዲስና ለአርስቲቶለስና እንዲሁም መጠናቸው ለማይታውቅ ፈላስፋዎና የሳይንስ ሰዎች መነሳት ዋናው ምክንያት ይሆናል፡፡ ታላቁ አሌክሳንደር ሲነሳ ይህንን መረት በማድረግ ልጣኔውን ማስፋፋት ይጀምራል፡፡ሱ ስም በሚጠራውም የግብ ከተማ የመጀመያውን መጽፍ ቤት ይከፍታል፡፡ አስተሳሰቡ ከዚያ በመነሳት በአካባቢውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ሳይንስና ጥበብን ማስፋፋት ነበር፡፡ ይህ ህልሙ ግን በሮማውያን ወራሪዎች ድምጥማጡ ይጠፋል፡፡ ከሰባት መቶ ሺ በላይ የሚጠጉ መጻም ይቃጠላሉ፡፡ የግሪና የግብ ልጣኔ መውደም በአውሮፓ ውስጥ የጨለማው ዘመን እየተባለ ለሚጠራው መነ ሲሆን፣ ይህ በራሱ በምዕራብ አውሮፓ ምድር ከይማኖት ጋር የተጣመረ ፊውዳላዊ የጨለማ አገዛዝ እንዲስፋፋ ያደርጋል፡፡ የአውሮፓ ዝብ ዕጣ በሽታ፣ ረሃብና ጦርነት ይሆናል፡፡ የሰፊውን ዝብ አስተሳሰብ በጭፍን ምነት እንዲጋረድ ያደረጉት የካቶሊክ ሃይማኖት መሪዎች የአውሮፓ ዝብ ታሪክ እንዳይራና ውነተኛ ነፃነቱን እንዳይቀዳጅ ያደርጉታል፡፡ ይህ ሁኔታ ግን ቀስ በቀስ የሚለወጥበት ሁኔታ ይፈጠራል፡፡ ዳንቴ የደረሰው የአምላኮች ኮሜዲ ለጭንቅላት ተሃድሶ በሩን ይከፍታል፡፡ የሰው ልጅ ከጨለማው ዓለም በመላቀቅ እንዴት አድርጎ ብርሃንን እንደሚጎናፍ ዳንቴ በግሩም ድርስቱ ውስጥ ያመለክታል፡፡ የዳንቴ ድርሰት ለሬናሳንስ መነሳት መረቱን ይጥላል፡፡ የእሱን ድርሰት ያነበቡት መልዕክቱን በመረዳት ለአዲስና ለታሪካዊ ራ ይነሳሳሉ።

ረቦችና በይሁዲዎች አማካይነት ወደ ምዕራብ አውሮፓ የገባው የግሪኩ ዕውቀት ወደ ላቲን በመተርጎምና የነበረውን ጨለማዊ አገዛዝ በመጋፈጥ በአውሮፓ ምድር ውስጥ በተለይም በጣሊያን ናሳንስ የሚባለው ዕውቀትን መልሶ የማግኘት ዘዴ ይስፋፋል፡፡ ዛሬ ኢስታንቡል ተብላ ከምትታወቀው በድሮ ስሟ ኮኒስታንቲኖፕል ተብላ ከምትጠራው ከተማ ፈልሰው የመጡ ቀሳውስት የፕላቶንን ሳብ በማስፋፋት አዲስ የልጣኔ ፈለግ ይቀዳሉ፡፡  የንግና የዕጥበብ መስፋፋት አዳዲስ ኃይሎችን ሲያፈልቅ፣ የድሮው ጨለማዊ አገዛዝ በድሮ መልኩ የማይቀጥልበት ሁኔታ ይፈጠራል፡፡ እነ ኬፕለርና ጋሊሊዮ እንዲሁም ብሩኖ ጋርዲያኖ የመሳሰሉት ጠለቅ ያለ ዕውቀት ያላቸው ምሁራን ያፈለትና ያዳበሩት አዲስ ዕውቀት የካቶሊክ ሃማኖት መሪዎችን ጭፍን ትምህርት በመቀናቀን መፈናፈኛ ያሳጣዋል፡፡ የእነ ዳቪንቺና ሚካኤል አንጀሎ ልዩ ዕላዊና የአርክቴክቸር ራዎች ለአሮፓው ልጣኔ መነሻ ይሆናሉ፡፡ ይሁንና ግን ፊዳላዊው ርዓትና የሃይማኖት ምነት ሙሉ በሙሉ ተዳክ ዝቡ ግለሰባዊ ነፃነት እስኪቀዳጅ ድረስ ረም መንገድ መጓዝ ነበረበት፡፡ ለብዙ መቶ መታት የተንራፋውን አስተሳሰብና የኃይል አላለፍ ለማሸነፍ ቀላል አልነበረም፡፡ ስለሆነም ሪፎርሜሽን ተብሎ የሚጠራው የካቶሊክን ሃይማኖት የሚቀናቀን ሃይማኖት በማርቲን ሉተርና በተከታዮቹ አማካይነት በመዳበርና በመስፋፋት የካቶሊክን ጭፍን አመለካከት ይጋፈጣል፡፡ ይህ እንቅስቃሴ ግለሰብ ምግባርን በማዳበር ለካፒታሊዝም ዕድገት ልዩ ምርታን ይሰጣል፡፡ ይህ አዲሱ ሃይማኖት በተስፋፋባቸው ቦታዎች ሳይንስ፣ ጥበብና ንግድ በመዳበር ለከበርቴው መደብ መነሳት ምክንያት ይሆናል።

ይቀጥላል፡፡

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_imgspot_img
- Advertisment -

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

Related Articles