Friday, December 8, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

የአገራችን የተወሳሰበ ችግር  አንድን መሪ በሌላ በመተካት ብቻ የሚፈታ አይደለም!

ክፍል ሁለት           

ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

17ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የሊበራል አስተሳሰብ ሲስፋፋ ዋና ዓላማውም ኋላቀር አስተሳሰቦችን በማስወገድና በመደምሰስ የሪብሊካንን አስተሳሰብና አገዛዝ መትከል ነበር፡፡ አንድ ወጥ የሆነውን የፈላጭ ቆራጭ (Despotic) አመለካከት በመጋፈጥ ለሲቪል እንቅስቃሴ በሩን በመክፈት ሳይንስና ጥበብ ዋናው መመያ ይሆናሉ፡፡ ኢንላይተንሜንት (አብርሆት) እየተባለ የሚታወቀው ምሁራዊ እንቅስቃሴም ዋናው ትርጉሙና ዓላማው በጭንቅላት ውስጥ ብርሃን ተፈናጥቆ የሰው ልጅ ታሪክን እንዲራ ማድረግ ነው፡፡ ስለሆነም ኢንላይተንሜንት የሚባለው እንቅስቃሴ የአሪስቶክራሲውንና የፊዳሉን አገዛዝና አስተሳሰብ በመደምሰስ የሲቪል ነፃነት ወይም ሊበሪቲን ማወጅ ነበር፡፡ ዋናው ዓላማው ይህ ቢሆንም የሊበራል እንቅስቃሴ መረታዊውን የፕላቶንና የሶክራተስን አስተሳሰብ ማለትም ዕውቀት ከጭንቅላት ውስጥ ነው የሚፈልቀው የሚለውን የሚቃምና ክስተታዊ አመለካከትንና ከዚህም በመነሳት ሁኔታዎችን ማንበብ የዕውቀት መነሻ ዋናው ምክንያት ነው ብሎ የተቀበለና የሚሰብክ ነው፡፡  ይሁንና ከውጭ ወደ ውስጥ የገባው ክስተታዊ አስተሳሰብ በጭንቅላት ውስጥ መብላላትና ወደ ተግባርም መመንዘር እንዳለበት ለኢንላይተንሜንት እንቅስቃሴ ምሁሮች ግልጽ  ነበር።

ይህ ሁሉ የሚያረጋግጠው በታሪክ ውስጥ የጭንቅላት ተሃድሶ ባልተካሄደባቸው አገሮች ውስጥ ታሪክን መራትና ከውስጥ ደግሞ የተረጋጋ ብረተሰብ መገንባት እንዳማይቻል ነው፡፡ በማንኛውም መልክ የሚገለጽ ጭቆና ዋናው ምክንያትም ጭንቅላት በአዲስ ዕውቀት መታደስ አለመቻሉ ነው፡፡ ከአንድ ብረተሰብ ውስጥም ጭቆናን ማስወገድ የሚቻለው አንዱ ይል ተወግዶ በሌላ ስለተተካ ሳይሆን ጭንቅላትን የሚያድስ ምሁራዊ እንቅስቃሴና አስ ዕውቀት ሲዳብርና ሲስፋፋ ብቻ ነው፡፡ በሌሎች አገሮችም ሆነ በአገራችን እንዳየነውና መገንዘብ እንደቻልነው አንድ ጨቋኝማ ፀረ ዕድገት አገዛዝ ስለተወገደ ብቻ የግዴታ ብረተሰብዊ ለውጥ ይመጣል  የፈጠራ ራ ይዳብራል፣ ቴክኖሎጂና ሳይንስ ይስፋፋሉ፣ እንዲያም ሲል ሁለገብ የሆነ ማበረሰባዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ይመጣል ማለት አይደለም፡፡ በአጭሩ የድሮ አገዛዝ ከተባረረና አዲስ ኃይል ልጣን ከያዘ ጭንቅላትን የሚያድስ ሁገብ ዕውቀት እስካልተስፋፋ ድረስ አንድ ዝብ ነፃነቱን በምንም ይነት እንደማይጎናፀፍ የብዙ አገሮችና የአገራችንም ታሪክ ያረጋግጣል፡፡ አንድ አገርም ብራዊ ነፃነቷን በማስከበር ዝቡ ተዝናንቶና ነፃነቱን ተጎናጽፎ ሊኖርባት የሚችል አገር መመረት አይቻልም፡፡ የአንድን ዝብ ነፃነት፣ ታሪክን መራት መቻልና አለመቻል፣ ከዚህ አጠቃላይና ሁለገብ ሁኔታ ተነስቶ መመርመር የሚያስፈልግ ይመስለኛል፡፡ በዛሬው ወቅት በአገራችን ምድር የተከሰተውን አስቸጋሪ ሁኔታና የአገዛዙንም መደናበርና ወደ ሌላ የጭቆና አገዛዝ ማምራት ከላይ ከተነተነው ሁኔታ መመልከቱ አስፈላጊ ይመስለኛል፡፡ የአገራችን የተወሳሰበ ሁኔታና የዝብ መፈናቀልና የንፈኝነት መስፋፋት በመደመርና በፍቅር ያሸንፋል መፈክር ብቻ እንደማይፈታ የአንድ መቱ የአዲሱ አገዛዝ ሁኔታ ያረጋግጣል፡፡  የለውጥ ኃይል እየተባለ የሚወደሰው አገዛዝ በእርግጥም የለውጥ ኃይል እንዳልሆነ እያረጋገጠልን ነው፡፡ ከድሮው የወረሰውን የጭቆና መሪያ በማንቀሳቀስ ለማያልቅ ጦርነትና ለዝቦች የእርስ በርስ መተላለቅ ሁኔታውን የሚያመቻች ይመስላል፡፡           

አስቸጋሪው ጉዳይ የአገራችንን ሁኔታና የአገዛዙን መንፈስና ተልዕኮ መረዳት!

በሁላችንም ዘንድ አንድ የተለመደ አነጋገርና የምንዝናናበት ነገር አለ፡፡ ይኸውም ኢትዮጵያ የጥንት ታሪክ ያላትና የልጣኔ አገርም እንደሆነች ነው፡፡ የሰውም ልጅ ዘርም ከዚያ የፈለቀ መሆኑ ሁላችንንም ያኮራናል፡፡ ይህ ትክክል የሆነውን ያህል እስከዚህም ድረስ የሚያዝናናን አይደለም፡፡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተመራማሪና ከኒውተን በተጨማሪ የካልኩለስ አፍላቂ የሆነው ጀርመናዊው ላይብኒዝ እንደሚያተምረን ማንኛውም አዲስ ትውልድ በድሮ ዝና መደሰትና መዝናናት ያለበት ሳይሆን ዛሬ የሚታየውን ችግር በመረዳት ለመፍታት ታጥቆ መነሳት እንዳለበትና ለሚቀጥለውም ትውልድ የልጣኔ መረት ጥሎ ማለፍ እንዳለበት ያሳስባል፡፡ ተከታታዩ ትውልድ መነሻ የሚሆነው የልጣኔ መረት እስከሌለው ድረስ የግዴታ ብረተሰብዊ ትርምስ መፈጠሩ የማይቀር ግዴታ እንደሆነም ማረጋገጥ ይቻላል፡፡

ስለሆነም እኛም በጥንቱ ታሪካችን ይህንን ያህልም የሚያዝናናን ነገር የለም፡፡  የጥንት አባቶቻችንና እናቶቻችን ብቻ ሳይሆኑ በታሪክ ውስጥ የተለያዩ አገሮች ልጣኔን በመራት ለምዕራብ አውሮፓ ልጣኔና ለካፒታሊዝም ዕድገት መረት ጥለው አልፈዋል፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳም በልጣኔያቸው ሊገፉበት አልቻሉም፡፡ የግብ ልጣኔ፣ የባቢሎን፣ የኢራና የሶልጣኔዎች ከፍተኛ ደረጃ የደረሱበት ሁኔታ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በታሪክም የተረጋገጠ ነው፡፡ ይሁንና ግን ሁኔታው ስላልፈቀደ ወይም የበሰለ ላልነበ በነዚህ አገሮች ውስጥ የካፒታሊዝም ርዓት ብቅ ሊል አልቻለም፡፡ የነዚህ ልጣኔዎች ተጠቃሚ የሆነው ምዕራብ አውሮፓ ነው፡፡ ከላይ ለማሳየት እንደሞከርኩት የተለያዩ አጋጣሚዎች በመገጣጠም በአውሮፓ ምድር ውስጥ በተለያየ ጊዜና ቦታ ካፒታሊዝም ብቅ ልና ሲስፋፋ ዛሬ ደግሞ ዓለምን ሊቆጣጠር ችሏል፡፡ እዚህ ላይ ግን መቋጠር ያለበት ነገር ካፒታሊዝም ተፈልጎና ታቅዶ የመጣ ርዓት ሳይሆን ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ በአናፊነት የወጣ ርዓት ነው፡፡ ካፒታሊዝም በራሱ ችግር ፈቺ ርዓት ሳይሆን በትግል አማካይነት እንደ ሁኔታው የኃይል አላለፍ ሲቀየርና የጭንቅላት ብስለት ሲዳብር ለግለሰብዓዊ ድርጊት በሩን የከፈተ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ርዓቱ በውስጡ ባለው ውስጠ ኃይል የተነሳ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍት ለመስጠት ያስቻለ ነው፡፡ የቴክኖሎጂ ዕድገትና ለብዙ ችግሮች መረታዊ መፍት መሆን ከካፒታሊዝም ውስጠ ኃይል ጋር የሚያያዝ ነው፡፡ ስለዚህም ካፒታሊዝም በአንድ አካባቢ ብቅ ያለ ያደገና የተስፋፋ ሲሆን ሁሉም አገሮች በዚህ ውስጥ ማለፍ አለባቸው ወይም ርዓቱን እንዳለ መቅዳት አለባቸው የሚል በተፈጥሮ የተደነገገ ግ የለም አይቻልምም፡፡ ይሁንና ግን ለፈጠራና ለዕድገት ያመቻሉ አስፈላጊም ናቸው የምንላቸውን ነገሮች መኮረጅና ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማጣመር ችግር ፈቺ እንዲሆን ለማድረግ መሞከር የማይታለፍ ጉዳይ ነው፡፡  ከዚህ ስንነሳና ወደ ኛ አገር ስንመጣ ታሪክን ለመራትና አዲስ ኅብረተሰብን ለመገንባት ያልቻልንበትን ምክንያት በመጠኑም ቢሆን ማየት ያፈልጋል፡፡ እዚህ ላይ ግን በሰፊው አልሄበትም፡፡

ለዛሬው አፍጦ አግጦ ለሚታየው የተወሳሰበ ችግራችን ዋናው ምክንያት የሰሜኑ የፊውዳል አገዛዝና ሃይማኖታዊ ምነት በአዲስና ጭንቅላትን በሚከፍት አዲስ አስተሳሰብ መጋፈጥ ባለመቻላቸው ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ለብዙ መቶ መታት ተንሰራፎት በመቆየቱ ለዕድገትና ለብረተሰብዊ ለውጥ ማነቆ እንደሆነ የማይካድ ሀቅ ነው፡፡ እንደ አውሮፓው ሁኔታ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከፍልስፍና ጋር የመጣመርና የመፈተሽ ዕድል ስላላጋጠመው የበላይነትን በመጎናፍ አንድ ወጥ አመለካከት በስፈን ለአዳዲስ አስተሳሰብ መፍለቅ ንቅፋት ሊሆን ችሏል፡፡ በዚህ ላይ የንግድ እንቅስቃሴና የዕደ ጥበብ ሙያ ያልተስፋፋ ስለነበር የሰው የእርስ በርስ ግንኙነት ከክልል አልፎ የሚሄድ አልነበረም፡፡ ይህ ይነቱ የተገደበ አኗኗርና የአብዛኛው ዝብ ኑሮ ከመሬት ጋር የተያያዘና በእርሻ ላይ የሚመካ ስለነበር አዳዲስ አስተሳሰቦች መፍለቅ አልቻሉም የፈጠራ ራም ሊዳብር አልቻለም፡፡ በብዙ ጥናቶች በምርምር እንደተደረሰበት በንግድ ልውውጥ አማካይነትና በዕደ ጥበብ ሙያ መስፋፋት የተነሳ ጭንቅላት ብቻ ሳይሆን ቋንቋ ራሱ ውስጣዊ ኃይል በማግኘት ጽሑፍ እንዲዳብር አስተዋጽኦ ሲያደርግ፣ የሰው ልጅ  ጭንቅላትም የበለጠ አርቆ አሳቢና ፈጣሪ እንደሚሆን ነው፡፡  ከዚህ ስንነሳ የፊዳሉ ርዓትና ሃይማኖት የሰውን የማሰብ ይል በማፈን የመንፈስ ልዩ ልዩ ባህሪዎች እንዳይዳብሩና ውነተኛ ግለሰብዊ ነፃነት እንዳይጎለምስና ገበሬውም በራሱ ላይ የሚመካ እንዳይሆንና የምርትን እንቅስቃሴ እንዳያሳድግ አስተሳሰቡን ገድቦበታል ማለት ይቻላል፡፡ የምርት መሪያዎችም ውስን ባህስለነበራቸው የገበሬው የማረስ ኃይል መዳበር አለመቻሉ ብቻ ሳይሆን፣ የተለያዩ የሰብል ይነቶችን፣ ፍራፍሬዎችንና አትክልትን በመትከል የተፈጥሮን ምንነት በመረዳት ኑሮውን ሊያሻሽል በፍም አልቻለም፡፡ በዚህ መልክ ከስምንት መቶ መታት በላይ የተንሰራፋው ፊዳላዊ አገዛዝና ምነት ለፈጠራ ራና ብረተሰብዊ እንቅስቃሴ እንቅፋት በመሆን ብረተሰብዊ መተሳሰር እንዳይኖር አገደ፡፡ በዚህም ምክንያት በሰሜኑም ሆነ በዛሬው መልክ በተዋቀረችው የኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ በከተማዎች የሚገለጽ ዕድገትና የከበርቴ መደብና ፈጣሪ የብረተሰብ ክፍል ብቅ ሊልና በሌላ ወገን ደግሞ ከሌላ ጋር በንግድ አማካይነት በመገናኘት ብረተሰብዊ መተሳሰርና በጋብቻ የሚገለጽ ግንኙነት እንዲዳብር ማድረግ አልተቻለም፡፡ ስለሆነም የዝቡ አስተሳሰብ ውስን ከመሆኑ የተነሳ ለረሃብ፣ ለድህነትና ለጦርነት እንዲዳረግ ሆነ፡፡ ብረተሰብዊ ኃይል እንዳይሆንና በአንድነት ተነሳስቶ አገር እንዳይገነባ ታገደ፡፡  በሌላ አነጋገር፣ ለጭቆና መስፋፋትና ለዕድገት ዋናው እንቅፋት የጭንቅላት ተሃድሶ አለመኖርና አዲስ የሪብሊካን አስተሳሰብ ያለው ብረተሰብዊ ኃይል ብቅ ማለት ያለመቻሉ ነው፡፡ ከላይ አንድ ቦታ ላይ ለማሳየት እንደሞከርኩት ሬናሳንስ፣ ሬፎርሜሽንና ኢንላይተሜንት የቱን ያህል ለአውሮፓው ብረተሰብ የአዕምሮና የመንፈስ ዕድገት አስተዋጽእንዳበረከቱ ነው፡፡ ስለሆነም ይህ ይነቱ ምሁራዊ እንቅስቃሴ ለብረተሰብዊ ለውጥና ለካፒታሊዝም ዕድገት በሩን መክፍት ችሏል ማለት ይቻላል፡፡ በዚህም አማካይነት ነው ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሊዳብሩና ብረተሰቡን ሊያስተሳስሩና የዕድገትም መግለጫ ሊሆኑ የበቁት፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ የኢንላይተንሜንት እንቅስቃሴ ባልተደረገባቸው እንደኛ ባሉ አገሮች መረታዊና ነቀል ብረተሰብዊ ለውጥ ለማምጣት ያለመቻል ዋናው ምክንያት ይህ ይነቱ ጭንቅላትን የሚከፍትና ለሁለገብ ዕድገት፣ እንዲሁም ለሳይንስና ለቴክኖሎጂ ምጥቀት የሚያመች የአዕምሮ ወይም የመንፈስ ተሃድሶ መካሄድ አለመቻል ነው።

በእኛ በትዮጵያውያን ዘንድ ያለው ትልቁ ችግር የብረተሰባችንን ውስጣዊ ግና የተወሳሰበ ችግር በቅጡ ያለመረዳት ነው፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ የኢትዮጵያን ብረተሰብ አወቃቀር ደረጃ በደረጃ ለማጥናትና ለመተንተን እስከ ዛሬ ድረስ ሙከራ ያደረገ የለም፡፡ ከታሪክ አንፃር የሚጻፉት ሀተታዎች በሙሉ ገለጻዊ (Discriptive) ባህ ያላቸው እንጂ በዲያሌክቲክ መነር እየታዩ ተተንትነው የቀረቡና የሚቀርቡ ሀተታዎች አይደሉም፡፡ በመሆኑም ተከታታዩ ትውልድ የብረተሰብችንን አወቃቀርና ታሪክ ትችታዊ በሆነ መልክ እንዳይረዳው ተደርጓል ማለት ይቻላል፡፡ በተማው እንቅስቃሴ ጊዜ እስከተወሰነ ደረጃ ድረስ ሙከራ ቢደረግም ይህም መረት ያደረገው ታሪካዊ ማቴሪያሊዝምን (Historical Materialismm) በተለይም በስታሊን በዶግማ መልክ የቀረበውን የብረተሰብ ታሪክ ከአንድ ደረጃ ወደ ሌላ እንዴት እንደሚሸጋገር ያሳየውን፣ ግን ደግሞ እጅግ አሳሳች የሆነውን ትንተና ዘዴ በመውሰድ ነው፡፡ ይህ ይነቱ አቀራረብ ደግሞ የብረተሰብችንን አወቃቀርና ለዕድገት ማነቆ የሆኑትን ምክንያቶች በደንብ እንዳናጠና አግዶናል ማለት ይቻላል፡፡ በተማሪው እንቅስቃሴ ውስጥ በቀጥታ ያልተካፈለው ምሁር ደግሞ የአገራችንን ችግር ሊረዳ የሚችልበት የትንተና መሪያ ሊያዳብር በፍም አልቻለም፡፡ ሌላው ከተማሪው እንቅስቃሴ እየተስፈናጠረ የወጣው ደግሞ የአገራችንን ችግር ከብረሰብ ችግርና ጭቆና መኖር አንፃር ብቻ በመመልክቱ አቀራረቡ ከስሜታዊነት ያላለፈና ለተከታታይ ጥናትና ትንተና የሚያመች አይደለም፡፡ ያም ሆነ ይህ ፊዳሊዝምና ሃይማኖት አንድ ላይ በመጣመር ለዕድገት እንቅፋት ለምን እንደሆኑና ለምንስ ለአዲስ ለተገለጸለት የብረተሰብ ኃይል መነሳት መፈናፈኛ መስጠት እንዳልቻሉ በሚሉት መረታዊ ጥያቄዎች ላይ ሰፋ ያለ ጥናት ብናካሄድ ኖር ከብዙ ንትርክና ውጣ ውረድ በዳን ነበር፡፡ ለምንስ አንድ ርዓት ለለውጥ የሚያመቹ ሁኔታዎችን ማዘጋት እንደተሳነውና ለምንስ የምርት ኃይሎች ማደግ አልቻሉም? በሚለው መረታዊ ሳብ ላይ ጠለቅ ያለ ጥናት ብናካድ ኖሮ ለብረሰብ ችግር ሁሉ መልስ መስጠት በተቻለ ነበር፡፡  የአገራችንን ችግር በመደብ ትግልና በብረሰብ ጭቆና መኖር ብቻ ባልገደብነው ነበር፡፡ በሳይንስና በአንዳች ልት የሚመራም ምሁር ዋና ተግባር በቁንሳብ ላይ በመመርኮዝ እሱን እንደ ቀኖናዊ አስተሳሰብ በመያዝ ለመከራከር መጣር ሳይሆን ከዚያ አልፎ በመሄድ የአንድን ብረተሰብ ችግር በዲያሌክቲክ መነጽር መመርመር ነው፡፡ በዚህ መልክና የሳብን የበላይነት ስናውቅና በጥሞና ለመወያየትና ለመከራከር ዝግጁ ስንሆን ለአገራችን የተወሳሰበ ችግር ተቀራራቢ መፍት ማግኘት እንችላለን፡፡

ከዚህ ስንነሳ የተማሪውን እንቅስቃሴና ዕድገት ውስን ባህና ተልዕኮውን መረዳቱ ከባድ አይሆንም፡፡ የተማሪው እንቅስቃሴ ተራማጅ መፈክር ይዞ ቢነሳም እንደ አውሮፓውያኑ ይነት ምራዊ እንቅስቃሴ በምሁራዊ ውይይትና ደት ውስጥ ያለፈ ስላልነበር ነገሮችን በውስን መልክ ብቻ ነበር ይመለከት የነበረው፡፡ ይህ ይነቱ አመለካከት ደግሞ በአገራችን ብቻ ሳይሆን በ1960ኛው እና በ70ኛው ዓመት የጦር ትግልና ሰላማዊ ልፍ እንቅስቃሴ በሚካሄድባቸው የስተኛው ዓለም አገሮችና ካፒታሊስት አገሮችም የነበረ ችግር ነው፡፡ ስለዚህም የአገራችንን የተማሪ እንስቃሴ ብቻ መወንጀሉ የችግሩን ምንነት ለመረዳት ብዙም አያግዘንም፡፡ መነሳት ያለበት ጥያቄ የተማሪው እንቅስቃሴ በተለይም ከዚህ የወጡት የማርክሲስት ሌኒንስት ድርቶች አብዮቱ ከሸፈ ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ ምን አዲስ ሳብ አፈለቁ? ዛሬስ መመያቸውና ፍልስፍናቸው ምንድነው? አንዳንዶች ንደሚያደርጉት ስም በመለወጥና፣ የመድበ ፓርቲና የግ የበላይነት መኖር አለበት ስለተባለ ብቻ ውስብስቡና ውጥንቅጡ የወጣው የአገራችን ችግር በዚህ መልክ ሊፈታ ይችላል ወ? በአንድ ወቅት ሲምሉበትና ሲገዘቱበት፣ እንደ መጽፍ ቅዱስም ያነቡ የነበረውን ማርክሲዝም ለምንስ እርግፍ አድርገው ጣሉት? ብለን እንድንጠይቃቸው እንገደዳለን፡፡

በመሆኑም፣ አንዳንድ የተማሪውን እንቅስቃሴ መጽቶች ስናገላብጥ የምንረዳው በተለይም በየዘመኑ የተከሰቱትን የብረተሰብችንን አወቃቀር፣ የተለያዩ የብረተሰብ ኃይሎችን የህሊና አወቃቀርና የመንግት መኪናን አገነባብና  መንግት የሚባለው ፍጡር የምርት ኃሎችን ዕድገት አጋዥ ከመሆን ይልቅ ለምንስ እንቅፋት ለመሆን በቃ? በሚሉት መረታዊ ጥያቄዎች ላይ በቂ ጥናት እንዳልተካሄደ መገንብ እንችላለን፡፡ በእኔ ምነት ይህ ባለመሆኑና በተለይም መንግትና የመንግት ቢሮክራሲው ከኢምፔሪያሊስት ኃይሎች ጋር ያላቸውን ትስስርና መቆላለፍ በሚገባ ካለመገንዘብ የተነሳ አብዮቱ መክሸፉ ብቻ ሳይሆን በቀላሉ ተተኪ የማይገኝላቸው የአንድ ትውልድ ምሁራንና አገር ወዳዶች ተሟጥጠው እንዲያልቁ ለማድረግ ተበቃ፡፡ በተጨማሪም ይህም የሚያመለክተው የተማሪው እንቅስቃሴ የከበደ አስተሳሰብና ኢትዮጵያን ታላቅ አገር ለማድረግ ያለው ራዕይ እጅግ የጠበበና ትግሉን ከራሱ ባሻገር ለማየት ያልቻለ መሆኑን ነው። ትግሉ የኢትዮጵያ ዝብ እንደ መሆኑ መጠን ለመከፋፈል እንዳያመችና ትግልን በማስተባበር ወደፊት በመራመድ አንድ ታላቅ አገር ለመገንባት ስፊ ጥናትን ዕግት እንደሚጠይቅና፣  ብረተሰብዊና ብራዊ ፕሮጀክትን ተግባራዊ ለማድረግ የግዴታ መቻቻልንና አንዳንድ የጎለመሰ አስተሳሰብ ያላቸውን ግለሰቦችም ሆነ ድርጅቶችን ሚና የግዴታ መቀበልና ማክበር እንደሚያስፈልግ የተገነዘበ አልነበረም፡፡ መናናቅና አንዱ በሌላው ላይ ማሾፍ ወይም ስም ማጥፋት አንደኛው የተማሪውም መዮ እንደነበርና ይህም ለአብዮቱ መክሸፍና ለአንድ ትውልድ መተላለቅ ምክንያት መሆኑ የማይካድ ሀቅ ነው፡፡

ያም ሆነ ይህ ራሱን ከፊዳላዊ ግትር አስተሳሰብ ማላቀቅ ያልቻለውና ጭንቅላቱ ያልበሰለና ያልዳ የተወሰነው የተማሪው እንቅስቃሴ አመራር ራሱ ባነሳው ጥያቄ ላይ በእልክነት ጦር ሰበቀ፡፡ ከመቻቻልና ከመደማመጥ ይልቅ ‹‹ጩኸቴን ቀሙብኝ›› በማለት አጠቃላይ ጦርነት ከፈተ፡፡ በጋራ ለመራት የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ከመጠቀምና የታወጁትን የጥገና ለውጦችን ተግባራዊ ለማድረግ ከመሞከር ይልቅ ሁሉም በየፊናው በአገራችን ላይ  ጦርነት አወጀ፡፡ሞክራሲያዊ ለውጥ እታገለሁ ብሎ የተነሳውና ከጭቆናም እላቀቃለሁ ብሎ እዚህና እዚያ ይሯራጥ የነበረው ሁኔታውን በጥሞና ከማንበብና ከመተንተን ይልቅ እልክ ውስጥ በመግባት ችግሩን ውስብስና ድርብርብ በማድረግ ዛሬ የምንገኝበት ደረጃ ላይ እንድንወድቅ የበኩሉን አስተዋጽኦ አደረገ፡፡ የአብዮቱን የብራዊ ባህና ለውጥ አምጭነት ያተረዳው ቢሮክራሲያዊ ኃይል ደግሞ ውስጥ ለውስጥ ተንኮል በመራትና ከውጭው ኃይል ጋር በማበር ለወጣቱ ማለቅ የበኩሉን አስተዋጽኦ አደረገ፡፡ ከዚህ ስንነሳ መገንዘብ የምንችለው ነገር በተለይም ጣሊያን ከአገራችን ከተባረና ነፃነታችንን ከተቀዳጀን በኋላ የተከሰተው አዲስ ብረተዊ ኃይል የበሰለ አስተሳሰብ ማዳበር ያልቻለና መንፈሱን ለለውጥ ያላዘጋጀ መሆኑን ነው፡፡ በትንሽ ነገር ተደስቶ እንደሚኖርና ታላቅ አገርና ብራዊ ኩራት በሳይንስና በቴክኖሎጂ ምጥቀና በከተማዎችና በመንደሮች ዕድገት የሚገለጽና ለዚህም በታታሪነት መራት እንደሚያስፈልግ መንፈሱን ያላዘጋጀና የነገሮችንም ደት በደንብ የተገነዘበ ብረተሰብዊ ኃይል እንዳልነበር በሳይኮሎጂና በሶሎጂ ዕውቀት ማረጋገጥ ይችላል፡፡ መናናቅና ሌላውን ዝቅ አድርጎ ማየት፣ እንዲያም ሲል ወደ ዘረኝነት ማድላትና ለኢምፔሪያሊዝም ማጎብደድ በተለይም ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት  በኋላ ሰተት ብሎ ከገባው የፍጆታ አጠቃቀም፣ ብዙም ሳይሩ ሀብታም ከመሆን ጋር በጥብቅ የተያያዘ ነው።

ነገሩን ለማሳጠር ዛሬም በመከላችን ያለው ትልቁ ችግር ራሳችንን ማግኘትና ማወቅ አለመቻላችን ነው፡፡ የመንፈስን የበላይነት በመረዳት የመንፈስ ተሃድሶ ለማድረግ ዝግጁ አለመሆናያነታርን ይኖራል፡፡ በመሆኑም ሁሉም በየፊናው ሀቀኛ ታጋይና ለኢትዮጵያ አሳቢ ካለሱ ብቻ ያለ አይመስለውም፡፡ እንዲያውም አንዳንድ ድርጅቶች የሚያስቡት የኢትዮጵያ ጉዳይ የጋራ ጉዳያችንና ሁላችንንም የሚያገባን ሳይሆን ለጥቂቶች ብቻ በሞኖፖሊ የተሰጠ በማስመስል በቁም ነገር ላይ እንዳንወያይና መፍትም እንዳንፈልግ በሩን ሁሉ ዘግተዋል፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ጉዳዩን ወደ ተራ ሴሌብሪቲ እየለወጡት ይገኛሉ፡፡ ጠቅላላው ለአገራችን የሚደረገው ትግል በተገለጸለት ምሁራዊ እንቅስቃሴ፣ በሳይንስና በፍልስፍና ላይ ከመመርኮዝ ከመታገል ይልቅ የግለሰቦችን ሚና አጉልቶ በማሳየትና (ፐርሰናሊቲ ልት) እንዲዳብር በማድረግ ትግሉን ፊዳላዊ ለማድረግ በቅተዋል፡፡ ይህ ይነቱ ትግል ደግሞ ሳንወድ በግድ የዛሬውን ‹‹አዲስ አገዛዝ›› እያጠናከረውና የአገራችንን ችግር እየተወሳሰበ እንዲሄድ መንገዱን ሁሉ ያመቻችለታል፡፡ ከምሁራዊ ውይይትና ክርክር በማምለጥ በራችን በመዝናናት በድሮ ዓለም የምንኖር እንዲሁም ደግሞ ሰፋ ያለ ምሁራዊ ውይይትን የምንንቅና ሌላውን የምናጥላላና የምንንቅ ብዙዎች ነን፡፡ ስብሰባ በሚዘጋጅባቸው ቦታዎች ሁሉ የሚደረገውን ሽር ጉድ ስመለከት የቱን ያህል ወደ ኋላ የምንጓዝ መሆናችንን ነው፡፡ ለውጥን መፈልግና  የኋሊት ጉዞ አንድ ላይ ሊሄዱ የሚችሉ ነገሮች አይደሉም፡፡

ያም ተባ ይህ በአገራችን ምድር መረታዊና ሁለንታዊ ለውጥ መምጣት አለበት ብለን የምናምን ከሆነ ከመንፈስ ተሃድሶ ውጭ ልናመልጥ አንችልም፡፡ ለመንፈስ ተሃድሶ ደግሞ ራስን መጠየቅ ዋናው መረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ ከዚህ በፊት ያደረግነውን አዎንታዊና አሉታዊ ድርጊቶችን ማውጣትና ማውረድ አለብን፡፡ ስህተት ወይም ደግሞ ብረተሰብዊ ወንጀል ርተን እንደሆን ወደ ውጭ አውጥተን መናገር መቻል አለብን፡፡ ስህተታችንን ስናውቅና ከስህተታችን ለመታረም ስንሞክር ብቻ ነው ለመረታዊና ለሁለንታዊ ለውጥ አስተዋጽኦ ማበርከት የምንችለው፡፡ ለዚህ ደግሞ የግዴታ የምንመራበት ትክክለኛ ፍልስፍናና ሳይንሳዊ የአራር ዘዴ መኖር አለበት፡፡ በአንድ ትክክል ነው ብለን በምናመነው ሳይንስና ፍልስፍና እየተመራን የምንጽፍና የምናስተምር ከሆነ የየበኩላችንን አስተዋጽኦ ለማበርከት እንችላለን፡፡ በሌላ ወገን ግን ስመለከተውና በጥብቅም ስመረምር አብዛኛዎቻችን ይህንንም ያህል ራሳችንን ለመጠየቅና የመንፈስ ተሃድሶ ለማድረግ ዝግጁ አይደለንም፡፡ ስህተት መሆኑ እየታወቀ ድሮ የራነው ራ ትክክል ነው ብለን ድርቅ ብለን የምንከራከር አለን። እኛ ሳንሆን ሌላው ነው ጥፋተኛ እያልን አሁንም እንምላለን ንገዘታለን፡፡ አንዳንዶቻችን ደግሞ ከተንኮል ጋር የተወለድን ይመስል ግለሰቦችን እናሳድዳልን፡፡ በዚህም ለኢትዮጵያ ዝብ ነፃነት የሚደረገውን ትግል እናጨናግፋለን፡፡ ሌሎቻችን ደግሞ የድርጅትና የግለሰብ ፍቅር እያንገበገበን ውነተኛ ውይይትና ክርክር እንዳይደረግ መንገዱን ሁሉ ለመዝጋት እንሞክራለን፡፡ በዚህም አንዳንድ ድርጅቶችና እንቅስቃሴዎች የሚያካሂዱትን ትግል ትክክል መሆኑንና አለመሆኑን ሳንመረምርና ሳንጠይቅ ወደ ኩርፊያ እናመራለን፡፡  በእርግጥ ከተንኮል ጋር የተወለደን ማዳን አይቻ፡፡  በቀና መንፈስ እንታገላለን ብለው እዚህና እዚያ የሚሉትን ግን ወደ አንድ ውሳኔ ላይ ከመድረሳቸው በፊት ሰፊ ጥናትና ምርምር ማድረግና እንዲሁም በቂ ግንዛቤ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ልናሳስባቸው እንወዳለን፡፡ እንደምናየው የዓለም ሁኔታ እየተወሳሰበና አስቸጋሪ እየሆነ የመጣ ነው፡፡ ስለሆነም ትክክለኛ ወይም ሳይንሳዊ አመለካከትን ለማዳበርና አገራችንን ካለችበት ችግር ለማላቀቅ የምንፈልግ ከሆነ ካለንበት ሁኔታ ባሻገር መመልከት ይኖርብናል፡፡ አስተሳሰባችንን ለመለወጥ ዝግጁ መሆን ይኖርብናል፡፡ አንድን ሳብ ከመቀበላችንና እንደ ምነት ከመውሰዳችን በፊት ትክክል መሆኑንና አለመሆኑን መመርመር መቻል አለብን፡፡ የተለያዩ ሳቦችንና ቲዎሪዎችን ማወዳደር አለብን፡፡ ችግር ፈጣሪዎች ሳንሆን ችግርን ፈቺ ለመሆን ከፈለግን የሚያዋጣው መንገድ ሳይንሳዊ መንገድ ብቻ ነው፡፡ ይህንን ካልኩኝ በኋላ የወያኔንም ሆነ ዛሬ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የሚመራውን አገዛዝ የሳብ ችግርና ግትርነትን ምንጭ ወይም ምክንያት መረዳቱ አስፈላጊ ይመስለኛል፡፡

በአገራችን ታሪክ ውስጥ ከየብረሰቡ የተውጣጡ ምሁራን ነን ባዮች የየብረሰቦቻቸውን የአስተሳሰብ ችግርና የማቴሪያል ዕድገት ኋላ ቀርነት በማንሳት ሰፊ ጥናት ለማድረግ አልሞከሩም፡፡ ሁሉም ነገር ከብረሰብ ጭቆና አንፃር በመታየቱ ከብረተሰብ የባህል ታሪክ ዕድገትና (Socio Cultural Studies) ከማወዳደር አንፃር (Comparative Studies) ጥናት ስላተደረገ የበሽታችንን ዋና ምክንያት ወይም መነሾ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ ስለሆነም አንዳንድ ሙከራ በሚደረግበት ጊዜ ፈላስፋ ነኝ፣ ማንም የሚወዳደረኝ የለም የሚለው የፕሮፌሰርነት ማዕረግ የያዘው ሁሉ መሳደብና መደንፋት ይጀምራል፡፡ የአገዛዙንና የመሪዎችን የአስተሳሰብ ችግር ሲነግሩት ብረሰቡን እንዳለ ለመስደብ ወይም ለማንቋሸሽ የሚደረግ አካሄድ ይመስለዋል፡፡ በዚህ መልክ ሳይንሳዊ ጥናትና ውይይት ከማድረግ ይልቅ ችግሩ በይደር እንዲታለፍና በላዩ ላይ ሌላ ችግር እንዲደረብበት ይደረጋል፡፡ ለነነት በሚደረገው ትግል ውስጥ ከማንኛውም ወገናዊነት መላቀቅ የመጀመያው ተግባር መሆኑ ብዙዎቻችን የተረዳን አይመስለኝም፡፡ በተጨማሪም አብዛኛዎቻችን  የአንድን ብረሰብ ችግርና የህሊና አወቃቀር ለመረዳት የምናደርገው ጥረት ይህንን ያህልም አይደለም፡፡ ለመረታዊ ለውጥ እንታገላለን የምንል ከሆነ  ካለንበት ሁኔታ ባሻገር ማየት መቻል አለብን፡፡ መለኪያችን የብረሰብና የሃይማኖት ጭቆና ሳይሆኑ ሳይንስና ፍልስፍና ብቻ መሆን አለባቸው፡፡ ማንኛውም ብረተሰብ ችግሩን የሚፈታውና የለጠነ ብረተሰብ ለመመሥረት የሚችለው በሳይንስ አማካይነት እንጂ የብረሰብና የሃይማኖች ጭቆናን አጉልቶ በማሳየቱ አይደለም፡፡ኛውም ብረሰብም ሆነ ይኸኛው ወይም ያኛው የሃይማኖት ተከታይ የሆነ በመጀመያ ደረጃ መረታዊ ፍላጎቱ መሟላት አለበት፡፡ መብላትና መጠጣት እንዲሁም ተጠልሎ መኖር አለበት፡፡ ክምና ና ትምህርትም ማግኘት መቻል አለበት፡፡ የአንድን ዝብ መረታዊ ችግርና ጥያቄዎች በብረሰብና በሃይማኖት መፍታት አይቻልም፡፡ የብረሰብና የሃይማኖት ጥያቄዎችን አጉልቶ ማሳየትና በእነዚህ ዙሪያ አስተሳሰባችን እንዲሽከረከር ማድረግ ያለብንን ኋላ ቀርነት ያጠናክረዋል፡፡ ችግራችንን ያባብሰዋል፡፡ እንደ ኅበረሰብ እንዳንኖር ያግደናል፡፡ የብረሰብ ጥያቄን በሳይንስ አማካይነት ብቻ መፍታት የሚቻል ሲሆን፣ የሃይማኖት ጥያቄ ግን ግላዊ ነው፡፡ ሃይማኖትን የብረተሰብ ጥያቄ አድርጎ ማንሳትና የተወሰነው የብረተሰብ ክፍልም ጭንቅላቱ በዚህ እንዲጠመድ ማድረግ መሞከር ልንወጣው የማንችለው ችግር ውስጥ ይከተናል፡፡ ሃይማኖት ምነት ነው፡፡ በሳይንስ የሚረጋገጥ አይደለም፡፡ በሌላ ወገን ግን ማንኛውም ሃይማኖት መከበር ያለበት ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ ሰው መሆናችንና አንደኛው ከሌላው እንደማይበልጥ የምንረዳው ሳይንስንና ፍልስፍናን እንዲሁም ዲያሌክቲክን መረት አድርገን ከታገልን ብቻ ነው፡፡ ይህንን ካልኩኝ በኋላ ወደ ዋናው ፍሬ ነገር ላይ ላምራ፡፡

የቀድሞው የወያኔም ሆነ የዛሬው አገዛዝ የሳብ ግትርነት ዋና ምክንያት ምንድነው? ለምድነው አገዛዞቹ እንደዚህ አምረው በጥፋታቸው እንዲቀጥሉ የተገደዱት? በአዕምሮ ጉድለትና በሳብ አለመዳበር የተነሳ? ወይስ አንዳች ከውጭ ሆኖ የሚቆጣጠቸውና የሚገፋፋቸው ኃይል ስላለ ነው ወይ እንደዚህ አምረው የሚገፉ? ብለን መጠየቅና ተቀራራቢ መልስ ለመስጠት መሞከር አለብን፡፡ የኢትዮጵያን ብረተሰብ ታሪክ በደንብ ለተከታተለ የፊዳሊዝም ጥንስስ የተጣለው ትግራይ ውስጥ ወይም አክሱም ግዛት ነው፡፡ ይህ ግዛት በዘመኑ ታላቅ ልጣኔዎች ከሚባሉት ውስጥ ቢጠቃለልም ወደ ውስጥ ሲታይ ግን ብረተሰቡ በ ክፍፍል የዳበረና ሳብ የሚንሸራሸርበት አልነበረም፡፡ የአገዛዙም ገቢ ከውጭ ንግድ በሚገኝ ገቢና በግብር (Tributary) ላይ የተመረተ ስለነበር ወደ ውስጥ ቢያንስ እንደ ቻይና ልጣኔ የ ክፍፍልን በማዳበርና ቢሮክራሲያዊ አራርን በማጎልመስ የሚታማ አልነበረም፡፡ በዚህም የተነሳ የሰው ኑሮና የአራር ዘዴ ተደጋጋሚና አሰልቺ ስለነበር ለመንፈስ ተሃድሶው የሚያግዘው አንዳችም ነገር አልነበረም፡፡ራ ክፍፍሉም ውስን ስለነበረና በግብና ላይም የተመካ ስለነበር በተፈጥሮ ላይ ከፍተኛ ዘመቻ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ትግራይ ውስጥ በተደጋጋሚ ይከሰት ለነበረው ድርቅና ረሃብ ዋናው ምክንያት ከብዙ መቶ መታት ጀምሮ ሲራበት የነበረው የአስተራረስ ዘዴ ነው፡፡ ተከታታይነት (Sustainable) ያለውና የተፈጥሮን ምንነት በመረዳት እንክብካቤ የሚደረግለት የአስተራረስ ዘዴና የአኗኗር ልት ስላነበ ለም የነበረው  የትግራይ መሬት ቀስ በቀስ ወደ በረሃነት እንዲለወጥ ተገደደ፡፡ በዚህም ምክንያትና ከሌላው ብረተሰብ ጋር በንግድና በሥራ ክፍፍል አማካይነት መገናኘት ያልቻለው ዝብ በአስተሳሰሰቡ ውስንና ተጠራጣሪ ሆነ፡፡ በራሱ ብቻ ተገልሎ እንዲኖር የተገደደው ዝብ በአጠቃላይ ሲታይ አገሪቱ ካሳየችው በጣም ደካማ ዕድገት ጋር ተያይዞ ወደ ፊት መራመድና የሳብ ለውጥ ማድረግ አልቻለም፡፡ ይህ ጉዳይና የሳብ ውስንነትና የፈጠራ ችሎታ አለመዳበር በአብዛኛዎቹ የአገራችን የሰሜኑ ክፍልም በጉልህ ይታያል፡፡

ከዚህ ይነቱ ብረተሰብ የፈለቀውና የፔሪፈሪ ካፒታሊዝም ዕውቀት ጭንቅላቱን የገረፈው የትግራይ ኤሊት የትግራይን ክፍለ ገር ወደ ኋላ መቅረት የተረጎመው ከአጠቃላዩ ከአገሪቱ ሁኔታና ከአገዛዙ ባህ ጋር ከማያያዝ ይልቅ፣  የአማራው ኤሊት የትግራይን ዕድገትና የዝቡን የኑሮ መሻሻል እንደማይፈልግ አድርጎ ነው፡፡ ይህ አመለካከቱና አተረጓሙ ደግሞ በሳይንስ የሚደገፍ አይደለም፡፡  ምክንያቱም ከ1940ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ በአገሪቱ ውስጥ በአዲስ አበባና በአካባቢው የተተከሉት ኢንዱስትሪዎች የማደግና የማባዛት እንዲሁም የፈጠራን ችሎታ የማዳበር ባህ አልነበራቸውም፡፡ አዲስ አበባ ላይ በአማራ የሚታማ አገዛዝ ስለተቀመጠ የአማራው ክፍለ አገሮች ተጠቃሚ አልነበ፡፡ ከደቡቡ የኢትዮጵያ ክፍለ ግዛት በስተቀር ጠቅላላው የአማራው ግዛትና ትግራይም ጭምር በአገዛዙ አኩሮ ያልተሰጣቸውና ዘመናዊ ተቋማትነበራቸው ነበሩ፡፡ ስለሆነም በአዲሱ የኢንዱስትሪ ተከላ ፖሊሲ አማካይነት ጠቅላላው የኢትዮጵያ ዝብ ሳይሆን ተጠቃሚው አምስት በመቶ የማይበልጥብረተብ ኃይል ብቻ ነበር፡፡ ስለሆነም ሌላው የኢትዮጵያ ግዛት ሲያድግ ትግራይ ብቻ ወደ ኋላ ቀረ የሚለው ኢሳይንሳዊ፣ በብረተሰብ ሳይንስና በኢኮኖሚ ቲዎሪ ያልተደገፈ አባባል የትም ሊያደርሰን አይችልም፡፡ ይሁንና ግን ከአማራው ኤሊት ጋር ልክ የተጋባውና የአማራን ኤሊት የበላይነት መስበር አለብኝ ብሎ የተነሳው የተወሰነው የትግራይ ኤሊት በጠባብ አስተሳሰብ በመደገፍ በዚያው በማምራት ጦርነት አወጀ፡፡ ይህንን ህልሙን ተግባራዊ ለማድረግ ሲል ውስጥ ለውስጥ ከውጭ ኃይሎች ጋር በመራት ሁኔታዎችን አመቻቸ፡፡ የቀድሞው የወያኔ አገዛዝ በጦርነት ዘመኑ ቀና አመለካከትና ብራዊ ባህያላቸውን እየመነጠረ ለድል የበቃ ኃይል ነበር፡፡ የሚያሳዝነውና የሚያስገርመው ግን ይህ ተገንጣይና ከፋፋይ ኃይል በማርክሲዝም ስም መማሉና ለሶሻሊዝም ራዕይ እታገላለሁ ብሎ መነሳቱና ብዙውን የትግራይ ወጣት ማሳሳቱ ነው፡፡  ለወያኔ ማደግና ወደ ድል ማብቃት ሻቢያ የማይናቅ አስተዋጽኦ ማድረግ ችሏል ማለት ይቻላል፡፡ ሁለቱም ኃይሎች በመተባበር አገራችንን እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ከተዋት እንደነበር ይታወቃል፡፡  ሻቢያም በበኩሉ ከ400 በላይ የሚበልጡ በኢትዮጵያዊነታቸው የሚያምኑና ተራማጅ አስተሳሰብ የነበራቸውን ኤርትራውያን እንደጨፈጨፈ ይታወቃል፡፡ ይህም ማለት ሁለቱም ይሎች በወንድሞቻቸው ደም የታጠቡ ናቸው፡፡ ርህራሄ የሌላቸው፣ የሰው ነፍስ የቅንጣትም ያህል የማያሳሳቸው ፍጡሮች ናቸው፡፡ ስለሆነም ወያኔ በወንድሞቹ ሞት የሚደሰትና ይህንንም እንደ ድል የሚቆጥርና ጭንቅላቱ የደነደነ ነበር፡፡ ጦርነት ማካሄድና ሰውን መግደል እንደ ሙያና ባህል የወሰደና ከደሙ ጋር ያዋሃደ ነበር፡፡ የሌላው ሰው መሞት ምንም ስሜት የማይሰጠው ከአውሬ በታች ያለ ጡር ነው ማለት ይቻላል፡፡ አዋቂዎች እንደሚሉት መንፈሱ የተሰለበና ራሱም ሰው መሆኑን የተረዳ አልነበረም፡፡ የሰው ልጅ ባህሪዎችና ስሜቶች ሁሉ ተሟጠው ያለቁበትና ሰውነቱ ብቻ የሚንቀሳቀስ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ሰውን ከማሰቃየት በስተቀር ለምን እንደሚኖር የተገነዘበ አይደለም፡፡ ፍቅር፣ ስሜት፣ ፀፀት፣ ርህራ፣ መቧቧት፣ ለፃናት ማዘንንና እንክብካቤ ማድረግ፣ ሽማግሌዎችን ማክበርና ተፈጥሮን መንከባከብ የሚሉት በሙሉ በጭንቅላቱ ውስጥ የሌሉ ናቸው፡፡ በአፈጣጠሩ የሰው ልጅና የተፈጥሮ ጠላት ይመስል የሚወስዳቸው ርምጃች ሁሉ የሚያስገርሙም የሚያሳዝኑም ናቸው፡፡ ሎጂስቲክንና የኅብረተሰብን ግ ያተከተሉ፣ አገራችንን ለከፍተኛ አደጋ የጣሉ ድርጊቶች ነበሩ፡፡ ባለፉት 28 መታት ተግባራዊ የሆኑት ፕሮጀክቶች የአገዛዙን የመንፈስ መቀጨጭ የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡ በአገሪቱ ውስጥ የተከናወኑትንና የሚካሄዱትን ፕሮጀክቶች ስንመለከት የዚህ ይነቱ በ ሥርዓት ያተገራና ጥበብና ሳይንስን ውስጣዊ ኃይሉ ያላደረገ የጭንቅላት ውጤቶች መሆናቸውን እንገነዘባለን፡፡ በእልና በአወቅኹኝ ባይነት የሚሩ ብዙ ሀብትና የሰው ጉልበት የፈሰሰባቸው ናቸው፡፡ ኅብረተዊ ሀብትን መፍጠር የማይችሉና ለፈጠራ ራ የማያመቹ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡ በአጭሩ ቀደም ብሎም ሆነ ዛሬ በአገራችን የሚታየው የተዘበራረቀና ቆሻሻ ሁኔታ የወያኔና ግብረ አበሮቹ ጭንቅላት መበላሸት ውጤቶች ናቸው፡፡ ከላይ በተጠቀሰው ደት ውስጥ የመጣ ኃይል ደግሞ ከጥፋት ሌላ  ታሪካዊና የተቀደሰ እንዲሁም አንድን ዝብ እንደ ኃይል የሚያሰነሳ ፕሮጀክት ከቶም ሊኖረው አይችልም፡፡ ስለሆነም ይህ ይነቱ ኃይል ራሱን ልጣን ላይ ለማቆየት ሲል ከውጭ ኢምፔሪያሊስት ኃይሎች ጋር በመተባበርና ትዕዛዝ ተቀባይ በመሆን አገራችን በችግር ተጠምዳ ዘለዓለሟን ፍዳዋን እያየች እንድትኖር የማያደርገው ጥረት አልነበረም፡፡ በዶ/ር ዓብይ አህመድ የሚመራው አገዛዝም ከወያኔው የአገዛዝ ልት የተላቀቀ የሚመስል አይደለም፡፡ የአገራችን ተጨባጩ ሁኔታ እንደሚያረጋግጠው አገዛዙ አገራችንን ወት አቅጣጫ እንደሚወስዳት ግልጽ የሆነለት አይመስልም፡፡ በሌላ አነጋገር ዝባችን እየተፈራራ የሚኖርባትና እንዲያም ሲል ወደ መተላለቅ በማምራት የውጭ ኃይሎች አገሪቱን እንዲወሩ ሁኔታውን እያመቻቸ እንደሆነ በፍም የተገነዘበ አይደለም፡፡

በአጭሩ ፊዳላዊ ባህሪ ከውስን ካፒታሊዝም ደት ጋር በመዋሃድ የቀድሞውንም ሆነ የዛሬውን አገዛዝ ጭንቅላት ሊያደነድንና ጥያቄ እንዳይጠይቅና ለተለየ ሳብ ጭንቅላቱን ክፍት እንዳያደርግ አግዶታል ማለት ይቻላል፡፡ ልጣን መያዝና በሀብት መደለብ ደግሞ የወያኔን አገዛዝ የባሰ ሳቡን እንዳለመበት ግልጽ ነበር፡፡ ሰብዊ ባህሪውን እንዳለ ገፎታል፡፡ ሰውን በጅምላ መግደል  የሚታየውንና የሚዳሰሰውን ነገር መካድ፣ ዕድገት ሳይኖር ዕድገት አለ ብሎ ድርቅ ማለት፣ ከፋፍሎ መግዛት፣ የሃይማኖት መሪዎችን በጥቅም በመግዛት መከፋፈልና ግጭት እንዲፈጠር ማድረግ፣ አንድን ብረሰብ ለሁለትና ለስት በመከፋፈል በመከላቸው ግጭት እንዲፈጠር ማድረግ፣ እኔ ብቻ ነኝ ሁሉንም ነገር መራት አለብኝ በማለት ለግል መዋዕለ ዋይ መንገዱን መዝጋት፣ ማንኛውም ነገር ከሱ ቁጥጥር ውጭ እንዳይሆን ማድረግና በአጠቃላይ ሲታይ አገራችን ዘለዓለሟን በትርምስ ዓለም ውስጥ እንድትኖር የማይሸርበው ተንኮል አልነበረም፡፡ እንዚህ ይነቱ ባህሪናሳብ መቀጨጭ በማንኛውም የብረተሰብ ታሪክ ውስጥ ያልታየና ያልተለመደ ነው፡፡ ሒትለርና ተከታዮቹ እንኳ እንደዚህ ይነት የሳብ መቀጨጭ አልታየባቸውም፡፡ የተከተለው ርዕዮተ ዓለምና በይሁዲዎች ላይ ያደረሰው ድርጊትና ያወጀው ጦርነት የሚኮነን ቢሆንም፣ የትለር አገዛዝ ጀርመንን ለማጥፋትና የዝቡን ቅስም ለመስበር የተነሳ አልነበረም፡፡ ከዚህ ስንነሳ የአገዛዙን ርዕዮተ ዓለምና የሚመራበትን ፖሊሲ በቀላሉ መተንተንና መረዳት ያስቸግራል፡፡ በአንድ በኩል በዝቅተኛ ስሜት የተወጠረ፣ በሌላ ወገን ደግሞ እኔው ብቻ ነኝ የለጠንኩትና የማውቀው ብሎ በመዝናናት የበላይነቱን ለማሳየት የሚጥር አገዛዝ ነበር፡፡ ስለሆነም ለትግል የሚያስቸግር ነው፡፡ በጊዜው በምን ይነት የትግል ዘዴ መጣልና ሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት እንደሚቻል ግራ ያጋባ አገዛዝ ነበር፡፡ ሌላው አስቸጋሪው ነገር ደግሞ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ከውጭ ኃይሎች ጋር የገባውና የተዋዋለው ስምምነት የአገራችንን ሁኔታ ውስብስብ ማድረጉ ነው፡፡

በዶ/ር ዓብይ አህመድ የሚመራው አዲሱ አገዛዝም ወያኔ ይከተል ከነበረው ኢሳይንሳዊና ኢብረተሰብዊ ፖለቲካ ትምህርት የቀሰመ አይመስልም፡፡ ወያኔ 28 መት ኢትዮጵያን ረግጦ ሲገዛ ያደረሰውን ባህላዊና ማበራዊ ውድቀት፣ እንዲሁም ብራዊ ውርደት የተገነዘበ አይመስልም፡፡ በተለይም ጊዜው የኛ ነውይህንን ዕድል ካልተጠቀምንበት መቼ ነው የምንጠቀመው እያሉ የሚያወሩ አንዳንድ የኦሮሞ ኢሊቶችና መሪዎች ከፍተኛ የታሪክ ወንጀል እየሩ ለመሆናቸው የተገለጸላቸው አይመስልም፡፡ ዝም ብለው በስሜት እየተገፉ የሚወስዷቸው ፖሊሲዎችና ዝብን ‹‹መጤ›› እያሉ ማፈናቀል የተቀረውን ዝብ ብቻ ሳይሆን እንወክለዋለን የሚሉትን ብረሰባቸውንም ወደ ኋላ እንዲጓዝ እያደረጉት ለመሆናቸው በፍም የተገነዘቡ አይመስልም፡፡ ካላቸው አስተሳሰብና ከሚያካሄዱትም ፖለቲካ የምንረዳው ነገር አዲሶቹ መሪዎች ስለኢኮኖሚና ስለብረተሰብ ዕድገት ይህን ያህልም ግንዛቤ ያላቸው አይመስልም፡፡ የፖለቲካ ሥልታቸው በሙሉ የፈጠራ ራንና አጠቃላይ የሆነን የ ክፍፍልን የሚረር ነው፡፡ ዝባችን ለዝንዓለሙ በድህነት ዓለም ውስጥ እየማቀቀ እንዲኖር የሚያደርግ ነው፡፡ በአጠቃላይ ሲታይ የፍልስፍናን፣ የሳይንስን፣ የባህልን፣ አርክቴክቸርንና ለአንድ ማበረሰብ ዕድገት የሚያስፈልጉ ዕውቀቶችን በሙሉ የሚቀናቀን ነው፡፡ ተግባራቸው በሙሉ ለውጭ ኃይሎች የሚሩ ነው የሚያስመስላቸው፡፡ ስለሆነም ከዚህ ይነቱ እጅግ አደገኛ ከሆነ አመለካከትና አገርን በታኝ ፖለቲካ መላቀቅ አለባቸው፡፡ ዛሬ እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ከሚገኙት እነ ኢራሪያና ሊቢያ ከመሳሰሉት አገሮች ውድቀት ትምህርት መቅሰም አለባቸው፡፡ ሌሎችም እንደ ክልል መታወቅ አለብን የሚሉ አንዳንድ ብረሰቦች የጎዝላቪያን ጣ ማየትና ከዚያ ትምህርት መቅሰም አለባቸው፡፡ በመበታተንና አትድረሱብኝ በማት ሳይሆን አንድ ክልልም ሆነ አገር ሁለገብ በሆነ መልክ ሊገነቡ የሚችሉት በመተባበርና ሳብ ለሳብ በመለዋወጥና በመመካከር ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም ለመው ትውልድ ጥሩና ቋሚ ነገር ጥለንለት ለማለፍ የምንፈልግ ከሆነ የሳብ ተሃድሶ ማድረግ አለብን፡፡ ከግትርነት፣ ከእልከኝነት፣ ከአወቅኹኝ ባይነትና ከጠባብ አስተሳሰብ መላቀቅ አለብን፡፡ መልካም ንባብ!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_imgspot_img
- Advertisment -

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

Related Articles