Thursday, September 21, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየቀድሞ የኢትዮጵያና የኤርትራ እግር ኳስ ፕሬዚዳንት አቶ ተስፋዬ ገብረ ኢየሱስ  (1932-2011)

የቀድሞ የኢትዮጵያና የኤርትራ እግር ኳስ ፕሬዚዳንት አቶ ተስፋዬ ገብረ ኢየሱስ  (1932-2011)

ቀን:

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ በተለይ በዳኝነት ከአገር ውስጥ እስከ ዓለም አቀፍ መድረክ ከበቁት ጥቂቶች አንዱ ነበሩ። አቶ ተስፋዬ ገብረ ኢየሱስ ከሌሎቹ ለየት የሚያደርጋቸው ብሔራዊ ፌዴሬሽኑን በፕሬዚዳንትነት መምራታቸው ነው፡፡ አልፎም የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ አገሮች (ሴካፋ) ፕሬዚዳንትም ነበሩ፡፡ 
አቶ ተስፋዬ በአፍሪካ እግር ኳስ የላቀ ስም ያሰጣቸው ሰባት የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታዎችን፣ የዓለም ዋንጫንና የዓለም ወጣቶች ዋንጫ፣ እንዲሁም በሎስ አንጀለስ ኦሊምፒክ በዳኝነት መሥራታቸው ነው። አቶ ተስፋዬ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ተገንጥላ ራሷን የቻለች አገር ከሆነች በኋላ ብሔራዊ እግር ኳስ ፌዴሬሽኗን በፕሬዚዳንትነት መርተዋል፡፡

ከዳኝነት በኋላ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) እና የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) ኢንስትራክተር በመሆን በርካታ ሙያተኞችን በማፍራት የሚታወቁት አቶ ተስፋዬ የተወለዱት 1932 .. ሲሆን፣ ባደረባቸው ሕመም ምክንያት 79 ዓመታቸው ነሐሴ 18 ቀን 2011 .. አርፈው በማግስቱ ሥርዓተ ቀብራቸው በአስመራ መፈጸሙ ታውቋል፡፡ ዜና ዕረፍታቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ሴካፋና ካፍ ሐዘናቸውን ገልጸዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...