Sunday, March 26, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ ከሾፌራቸው ጋር እያወሩ ወደ ቤት እየሄዱ ነው

[ክቡር ሚኒስትሩ ከደላላ ወዳጃቸው ጋር ቢሮ ተገናኝተው እያወሩ ነው]

  • እንዴት ነዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • ምን አዲስ ነገር አለ?
  • አዲስ ነገር ከጠፋ ሰነባበተ እኮ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እንዴት?
  • በቃ ሁሉም ነገር ቀዝቅዟላ፡፡
  • ምን ክረምቱስ ቀዝቃዛ አይደል እንዴ?
  • ክረምቱን እኮ በበርካታ ነገሮች ማሞቅ ይቻላል ኑሮን ማሞቁ ነው የከበደን፡፡
  • እ. . . .
  • ክቡር ሚኒስትር ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም ሆነ እኮ ነገሩ፡፡
  • አልገባኝም?
  • በቃ መንግሥትም ዝም አለ፡፡
  • ስለምኑ?
  • ስለኢኮኖሚው ነዋ፡፡
  • መንግሥትማ ፖለቲካው ላይ ተወጥሯል፡፡
  • እንዳይሳሳቱ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እንዴት?
  • ኢኮኖሚው ከተያዘ ፖለቲካው ቁልቁለት ነው፡፡
  • እሱስ ልክ ነህ፡፡
  • ይኸው አሁን እኮ ዳገት የሆነባችሁ ለዚያ ነው፡፡
  • ምኑ ነው ዳገት የሆነብን?
  • ፖለቲካው ነዋ፡፡
  • ምን ይደረግ ብለህ ነው?
  • ለኢኮኖሚው መልስ መስጠት ነዋ፡፡
  • እኮ እንዴት?
  • የራሳችሁን ሀብታሞች ፍጠሩ፡፡
  • ምን እያልከኝ ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር የቀድሞዎቹን ገዥዎች ስትራቴጂ ረሱት እንዴ?
  • ምን ነበር?
  • ፖለቲካውን የተቆጣጠሩት ኢኮኖሚውን በመቆጣጠራቸው ነው፡፡
  • እሱማ ልክ ነው፡፡
  • እናንተም ተመሳሳይ ስትራቴጂ ካልተከተላችሁ አትዘልቁትም፡፡
  • ይቻላል ብለህ ነው?
  • ለምን አይቻልም?
  • አሁን ሁሉ ነገር ተለውጧል፡፡
  • ምን ተለወጠ?
  • ለውጥ የለም እያልከኝ ነው?
  • በወሬማ ለውጥ አለ ነው የሚባለው፡፡
  • በተግባር የለም እያልከኝ ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር ወሬውን ከተቆጣጠራችሁት ተግባሩ ችግር የለውም፡፡
  • እንዲያውም ተግባር ከሌለ ወሬ ብቻ ማን ይቀበለናል?
  • ክቡር ሚኒስትር መንግሥት እኮ ኃይል አለው፡፡
  • ቢኖረውስ?
  • ኃይል ያለው አሸናፊ ነዋ፡፡
  • የመንግሥት ኃይል ሕዝብ መሆኑን ረሳኸው?
  • እኔም እኮ የምልዎት እሱን ነው፡፡
  • ምንድነው የምትለኝ?
  • የራሳችሁን ሕዝብ ፍጠሩ፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • የራሳችሁን ሀብታሞች መፍጠር ነዋ፡፡
  • እ. . .
  • በቃ የእናንተን ሐሳብና ፖሊሲ የሚደግፉ ሰዎችን መፍጠር አለባችሁ፡፡
  • እ. . .
  • ስለዚህ መንግሥትን ከኋላ የሚደግፉ ባለሀብቶችን መፍጠር ነው፡፡
  • አሁን እንደምትለው ቀላል ነው ብለህ ነው?
  • ምን ችግር አለው?
  • እንቅስቃሴው ሁሉ ተዳክሟል እያልከኝ እንዴት ይቻላል?
  • በአሁን ጊዜ በሥራ ባለሀብት መፍጠር አይቻልም፡፡
  • ታዲያ በምንድነው የምንፈጥረው?
  • በዝርፊያ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ የወጣቶች መሪ ጋር ስብሰባ ላይ ተገናኙ]

  • እንዴት ነዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • ሰላም ነህ?
  • ምን ሰላም አለ?
  • ምን ሆንክ? ሰላም አይደለህም?
  • አገር ታማ ሰላም አለ ብለው ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • እ. . .
  • አገር ታማ እኮ ማንም ሰላም ሊሆን አይችልም፡፡
  • አገር ሕመም ላይ ሳትሆን ለውጥ ላይ ናት፡፡
  • ምን አሉኝ ክቡር ሚኒስትር?
  • ለውጥ ላይ ነን ነው ያልኩህ፡፡
  • መቼ ነው ግን የምታምኑት?
  • ምኑን?
  • ችግራችሁን ነዋ፡፡
  • የምን ችግር?
  • አገሪቱ ከዚህ በላይ ምን ትሁን?
  • አልገባኝም?
  • ሕዝብ እንደዚህ ተጨንቆ እየኖረ እናንተ ለውጥ ላይ ነን ምናምን ትላላችሁ፡፡
  • ታዲያ ለውጥ ላይ አይደለንም እያልከኝ ነው?
  • መጀመርያማ መስሎን ነበር፡፡
  • ማለት?
  • ለውጥ አለ ብለን ሁሉን ነገር ለመስዋዕት አቅርበን ታገልን፡፡
  • ትክክል ናችኋ፡፡
  • አልመሰለኝም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለምን?
  • ለውጥ ላይ ሳንሆን. . .
  • እ. . .
  • ነውጥ ላይ ነን፡፡
  • በቃ ወጣቶች ደግሞ ትቸኩላላችሁ፡፡
  • ምን እያሉ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ሁሉ ነገር በአንድ ጀንበር እንዲለወጥ ነው የምትፈልጉት፡፡
  • እ. . .
  • የእናንተ ትውልድ እኮ ፋስት ፉድ የሚወደው ለዚህ ነው፡፡
  • አልገባኝም?
  • ሁሉን ነገር በአንዴ ይወለድ ነዋ የምትሉት፡፡
  • ብለው ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • እኔ ወጣት እያለሁ እንደ እናንተው ነበርኩ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር የእኔ ግንዛቤ ግን ከዚህ የተለየ ነው፡፡
  • እንዴት ማለት?
  • ጭራሽ መንግሥት ወጣቱን የረሳው ነው የሚመስለው፡፡
  • እንዴት ይረሳዋል?
  • ከፖሊሲ ጀምሮ በሁሉ ነገር የወጣት ዘርፉ የተረሳ ነው የሚመስለው፡፡
  • እ. . .
  • መንግሥት ወጣቱን የሚፈልገው ለአብዮት ብቻ ነው፡፡
  • ምን አልከኝ?
  • ክቡር ሚኒስትር ወጣቱ ለምትሉት ለውጥ ዋነኛ ሞተር ነበር፡፡
  • እሱ መቼ ይካዳል?
  • አሁን ደግሞ ወጣቱ ከመንግሥት የሚጠብቀው ነገር አለ፡፡
  • ምንድነው?
  • ዳቦ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ ዳያስፖራ ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው]

  • እንዴት ነዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • የት ነው የማውቅህ?
  • ከዚህ በፊት አውሮፓ ተገናኝተን ነበር፡፡
  • ዳያስፖራ ነህ?
  • አዎን ክቡር ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እንደ አንተ ዓይነት ሰው በጣም ነው የሚያስደስተኝ፡፡
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • በቃ የመደመር ሐሳቡ ገብቶሃላ፡፡
  • ምን አሉኝ?
  • ባይገባህ ኖሮ እንዴት ወደ አገርህ ትመለስ ነበር?
  • መቼ ተመለስኩ አልኩዎት?
  • ለመዝናናት መጥተህ ነው እንዴ?
  • እሱማ አገሬን ለማገልገል ነበር የመጣሁት፡፡
  • ታዲያ ምን ችግር ገጠመህ?
  • ሁሉ ነገር ያስፈራል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • ነገሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሱ እንጂ እየተሻሻሉ አይደለም፡፡
  • ለውጥ ላይ መሆናችንን አትርሳ፡፡
  • ወይ ለውጥ?
  • በለውጥ ላይ ደግሞ ሁሉ ነገር አልጋ በአልጋ አይሆንም፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እኔም ለውጥ አለ ብዬ ነበር የመጣሁት፡፡
  • አሁን የለም እንዳትለኝ?
  • እንደሚወራለት አይደለም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • መቼም ዳያስፖራዎች ስትባሉ አቃቂር ማውጣት ትችሉበታላችሁ፡፡
  • እኔ አቃቂር እያወጣሁ አይደለም፡፡
  • ታዲያ ምን እያደረክ ነው?
  • እውነቱን እየነገርኩዎት፡፡
  • ምንድነው እውነቱ?
  • በቃ ክቡር ሚኒስትር ሲስተም የሚባል ነገር እኮ የለም፡፡
  • የምን ሲስተም?
  • በቃ ሁሉም ሰው በአቋራጭ መክበር ነው የሚፈልገው፡፡
  • እ. . .
  • ሲስተሙ ራሱ በሙስና ላይ ነው የተመሠረተው፡፡
  • እሱን ነዋ ማስተካከል ያለብን፡፡
  • ከሙስናው ባለፈ ደግሞ የዘር ፖለቲካው ሲጨመርበት አደገኛ ነው፡፡
  • ምን አልከኝ?
  • ብቻ ሁሉም ነገር ተስፋ አስቆራጭ ነው፡፡
  • ተው እንጂ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር በአንድ ጀምበር ሚሊየነሮች እየተፈጠሩ ነው፡፡
  • እ. . .
  • በሥራ ሳይሆን በዝርፊያ ማለት ነው፡፡
  • ወይ ጣጣ፡፡
  • የኢኮኖሚ ዕድገት ምናምን የሚባለውም ተራ ወሬ ነው፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • ሁሉም ነገር የተሳሳተ መሠረት ላይ ነው ያለው፡፡
  • እ. . .
  • ሰሞኑን ለመኪኖች ፍጥነት መገደቢያ ማሽን ይገጠምላቸው ሲባል ሰምቻለሁ፡፡
  • እኔም ሰምቻለሁ፡፡
  • በየቀኑ ለሚፈጠሩት ባለሀብቶችም ሌላ ማሽን ሊገጠምላቸው ይገባል፡፡
  • ምን ዓይነት ማሽን?
  • የሀብት መገደቢያ ማሽን!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሾፌራቸው ጋር እያወሩ ወደ ቤት እየሄዱ ነው]

  • ምን ሆነህ ነው የምታዛጋው?
  • እርቦኝ ነዋ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምሣ አልበላህም እንዴ?
  • ምን ነበር እሱ ነገር ክቡር ሚኒስትር?
  • ተጨዋች ነህ እኮ አንተ፡፡
  • የኑሮ ውድነቱ ነው ተጨዋች ያደረገኝ፡፡
  • ፖለቲካህን ጀመርክ ማለት ነው?
  • አሁን አሁን ሳስበው ፖለቲካው ሳያዋጣ አይቀርም፡፡
  • እንዴት?
  • ይኸው እኛማ ከዕለት ዕለት ኑሮ እያላተመን እንሰቃያለን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ባለሀብቶች እንደ አሸን እየፈሉ ነው፡፡
  • ምን ታደርገዋለህ?
  • ነገርኩዎት እኮ ፖለቲከኛ መሆን ነው የሚያዋጣው፡፡
  • ነው ብለህ ነው?
  • ስነግርዎት በአንድ ጀንበር ባለሀብቶች እየተፈጠሩ ነው፡፡
  • ፖለቲከኞች ናቸው እንዴ?
  • እዚያው ካምፕ ውስጥ ያሉ ናቸው ሲለወጡ ያየነው፡፡
  • አንተ መቼም የማታመጣው ነገር የለም፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር በሹፍርና ጠብ ያለልኝ ነገር ስለሌለ በቅርቡ ሥራ እለቃለሁ፡፡
  • ለምን?
  • አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ ለማቋቋም፡፡
  • ምን የሚባል ፓርቲ?
  • ኢችፓ፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • የኢትዮጵያ ችጋራሞች ፓርቲ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

በወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የተሰበሰበው ከፍተኛ ሀብት ጥቅም ላይ እየዋለ አይደለም ተባለ

በኢትዮጵያ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የተሰበሰበው የተቀማጭ ገንዘብ መጠን...

ጥቁር የመልበስ ውዝግብና የእምነት ነፃነት በኢትዮጵያ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ኅዳር ወር ላይ በፓርላማ...

መንበሩ ካለመወረሱ በስተቀር መፈንቅለ ሲኖዶስ መደረጉን ቤተ ክህነት አስታወቀ

ቅዱስ ሲኖዶስ ከነገ ጀምሮ ውይይት እንደሚጀምር ተነገረ ‹‹እኛ ወታደርም ሆነ...

ወ/ሮ መሰንበት ሸንቁጤ የአዲስ አበባን ንግድና ዘርፍ ምክር ቤትን በፕሬዚደንትነት ለመምራት በተደረገው ምርጫ አሸነፉ

የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤትን በፕሬዚደንትነት ለመምራት፣...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...

ብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይፋ ሊያደርግ ነው

የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት የሚረዳ ሪፎርም ማጠናቀቁን የገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...