Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅበታላቁ ቤተ መንግሥት ውስጥ የተገነባው ፓርክ

በታላቁ ቤተ መንግሥት ውስጥ የተገነባው ፓርክ

ቀን:

የተለያዩ የምሥራቅ አፍሪካ መሪዎች በተገኙበት ሐሙስ መስከረም 29 ቀን 2012 ዓ.ም. የተመረቀው አንድነት ፓርክ፣ በመደመር እሳቤ ትናንትን መሰብሰብ፣ ዛሬን ማከማቸትና ነገን ማካበት ላይ ተመሥርቶ የተገነባ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ አንድነት የሚል ስያሜ የተሰጠው ፓርኩ ስድስት መስህቦች ሲኖሩት፣ ከአንዱ በስተቀር አምስቱ ከዓርብ መስከረም 30 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ለጉብኝት ክፍት ሆኗል፡፡ እነዚህ መስህቦችም የባለ ጥቁር ጎፈር አንበሳ ዋሻ፣ የተለያዩ እንስሳት ማቆያ ቅጥር፣ የዘጠኙ ክልሎች ወኪል እልፍኞች፣ የአገር በቀል ዕፀዋት ማሳያ ሥፍራና የታደሱት የነገሥታት ታሪካዊ ሕንፃዎች ሲሆኑ፣ የእንስሳት ማቆያው ቅጥር ግን እስከ ጥቅምት አጋማሽ ድረስ ተጠናቅቆ ለጉብኝት ክፍት እንደሚሆን ተነግሯል፡፡ በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ፣ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት መሐመድ አብዱላሀ መሐመድ (ፎርማጆ) እና የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዳት ተገኝተዋል፡፡ ጎብኚዎች ፓርኩን ለመጎብኘት ለመደበኛ 200 ብር፣ ለልዩ ጉብኝት (ቪአይፒ) ደግሞ 1,000 ብር መክፈል የሚጠበቅባቸው ሲሆን፣ ሁሉም ዓይነት ክፍያዎች የሚከናወኑት ከወረቀት ገንዘብ ውጪ በኤሌክትሪክ የክፍያ ዘዴዎች ናቸው፡፡

በታላቁ ቤተ መንግሥት ውስጥ የተገነባው ፓርክ

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...