Saturday, December 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊከ300 ሺሕ በላይ ተማሪዎች የሚካተቱበት የምገባ መርሐ ግብር ከዚህ ሳምንት ጀምሮ ይተገበራል

ከ300 ሺሕ በላይ ተማሪዎች የሚካተቱበት የምገባ መርሐ ግብር ከዚህ ሳምንት ጀምሮ ይተገበራል

ቀን:

በአዲስ አበባ ከመዋዕለ ሕፃናት እስከ ስምንተኛ ክፍል የሚማሩ 300 ሺሕ ያህል ተማሪዎችን ለመመገብ የተዘጋጀው መርሐ ግብር በዚህ ሳምንት ሙሉ ለሙሉ እንደሚጀመር የአዲስ አበባ አስተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ጽሕፈት ቤቱ በሳምንቱ የተሠሩ ሥራዎችን በገመገመበት ወቅት እንዳስታወቀው፣ ከየዘንድሮው የተማሪዎች ምገባ መርሐ ግብር በአንዳንድ ምህርት ቤቶች የተጀመረ ሲሆን፣ ከጥቅምት 3 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ደግሞ ሙሉ በሙሉ ይተገበራል።

የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራሙ ከዚሁ ቀደም በአዲስ አበባ በሚገኙ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች በተለያየ መልኩና በተለያዩ አካላት ሲተገበር የቆየ ሲሆን፣ 2011 በጀት ዓመትም የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ 51 ሺሕ ያህል ተማሪዎችን እየመገበ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ከተለያየ የኑሮ ደረጃ የሚመጡ ተማሪዎችን በተመሳሳይ መልኩ ለማስተናገድ ሲባል ሁሉም ተማሪዎች በተማሪዎች ምገባ እንዲስተናገዱና ተመሳሳይ የደንብ ልብስ እንዲለብሱ የከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ ሥራዎችን ሲሠራ ቆይቷል፡፡

በተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም፣ አሥር ሺሕ በላይ እናቶች ምግብ በማዘጋጀትና በማቅረብ የሥራ ዕድል የሚያገኙ ሲሆን፣ የምገባ ፕሮግራም ተጠቃሚ ተማሪዎች እናቶችን በማሳተፍ የምግብ አቅርቦቱ ደኅንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን ትምህርት ቤቶች በሚገኙባቸው ወረዳዎች ላይ የሚገኙ እናቶችም በማኅበር ተደራጅተው የሚሳተፉበት አካሄድ ተመቻችቷል፡፡

ለተማሪዎች ምግብ በማቅረብ ሥራ የሚሳተፉ እናቶች በሚመሠርቱት ወይም በመሠረቱት ማኅበር አማካይነት ከሸማቾች ኅብረት ሥራ ማኅበራት ጋር እንዲተሳሰሩ፣ በሚሠሩባቸው ትምህርት ቤቶችም ማብሰያ ቦታ እንዲያገኙ፣ መብራትና ውኃ በነፃ እንዲጠቀሙ እንደሚደረግምግብ አቅራቢ ማኅበራትም በሚሰጣቸው የምግብ ዓይነትና ዝርዝር መሠረት ቁርስና ምሳ እንደሚያቀርቡ ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወቃል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...