Monday, December 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የረሃብ አድማውን ሰርዘው ደም ሊለግሱ ነው

ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የረሃብ አድማውን ሰርዘው ደም ሊለግሱ ነው

ቀን:

በሰኔ ወር መጨረሻ 2011 ዓ.ም. የፀደቀውን የፖለቲካ ፓርቲዎችና የምርጫ አዋጅ የተቃወሙ የ71 ፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች፣ ለሁለት ቀናት ሊያደርጉ ያሰቡትን የረሃብ አድማ ለጊዜው በመተው በሰሞኑ ጥቃት ለተጎዱ ወገኖች ደም እንደሚለግሱ አስታወቁ፡፡

በፓርላማ በአብላጫ ድምፅ የፀደቀውን የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የሥነ ምግባር አዋጅ በመቃወም ለ48 ሰዓታት የሚቆይ የረሃብ አድማ በአራት ኪሎ ሚያዝያ 27 አደባባይ ለማድረግ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕቅድ ይዘው ነበር፡፡

ሰኞ ጥቅምት 25 ቀን 2012 ዓ.ም. የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ተወካዮች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ ለከተማ አስተዳደሩ የፈቃድና የጥበቃ ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ አላገኙም፡፡ የአስተዳደሩ የሚመለከተው አካል በቃል ቦታ እንዲቀይሩ ጠይቋቸው እንደነበርና እነሱ ደግሞ ቦታ እንደማይቀይሩ በመግለጽ እንዲፈቀድላቸው ቢጠይቁም፣ ኃላፊው ቢሯቸው ባለመገኘታቸው በጸሐፊያቸው ስለተነገራቸው ዕቅዳቸውን ማዘግየታቸውን አስታውቀዋል፡፡

ከከተማ አስተዳደሩ ምላሽ እስኪያገኙ ድረስ የረሃብ አድማውን በማዘግየት፣ በሰሞኑ ጥቃት ለተጎዱ ወገኖች ረቡዕ ጥቅምት 26 ቀን 2012 ዓ.ም. ደም ለመለገስ መወሰናቸውን አስታውቀዋል፡፡

የምርጫ አዋጁን የተቃወሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከረሃብ አድማው በተጨማሪ፣ በሰላማዊ ሠልፍና በአዳራሽ ስብሰባዎች ተቃውሞአቸውን ለመቀጠል መስማማታቸውን ገልጸዋል፡፡ አዋጁ የዜጎችን የመደራጀት መብት የሚገድብና ለፖለቲካ ፓርቲዎችም ህልውና አደጋ የደቀነ በመሆኑ እንደሚቃወሙት አስታውቀዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...