Sunday, June 4, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ለክቡር ሚኒስትሩ ሌላ ሚኒስትር ስልክ ደወሉላቸው

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚስታቸው ጋር ቁርስ እየበሉ ነው]

  • ምነው ተከዝክ?
  • እንዴት አልተክዝ?
  • ቡናህ እኮ ቀዘቀዘ፡፡
  • እዚህ አገር ምን ያልቀዘቀዘ ነገር አለ?
  • ቁርሱም እኮ እየቀዘቀዘብህ ነው ብላ እንጂ?
  • ባክሽ ዘግቶኛል፡፡
  • መቼም ጉሮሮህን ወጣቶቹ አላገኙትም?
  • የትኞቹ ወጣቶች?
  • መንገድ የሚዘጉት ናቸዋ፡፡
  • ተይኝ እስቲ ባክሽ?
  • ምነው?
  • ሁሉም ነገር እኮ ግራ ያጋባል፡፡
  • እንዴት?
  • አንዱን ስትይው አንዱ እያለ መከራችንን በላን፡፡
  • ብዙ አትጨነቅ ባክህ?
  • እንዴት አልጨነቅ?
  • ማለቴ ሁሉም ከልኩ አያልፍም ብዬ ነዋ፡፡
  • እየቀለድሽ ነው?
  • የምን ቀልድ ነው?
  • ታዲያ አገር እንዲህ ተወጣጥራ እያየሽ ከልኩ አያልፍም ስትይኝ ነዋ?
  • ምን ላድርግ ታዲያ?
  • በጣም አሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ ነን፡፡
  • እንዴት?
  • አንዱን ቀዳዳ ስንደፍን ሌላው እያንጠባጠበ ተቸግረናል፡፡
  • ዋናው ለራስ ማሰብ ነው ባክህ፡፡
  • ምን እያልሽ ነው?
  • መጀመርያ ለራስህ አስብ፡፡
  • አልገባኝም?
  • አንተ የተደላደለ ነገር ካለህ ሌላው ችግር የለውም፡፡
  • የአገሪቱ ጉዳይ አያሳስብሽም?
  • አንተ ጥሩ ነገር ካለህ መከራውም እኮ ቀስ ብሎ ነው የሚያገኝህ፡፡
  • እ…
  • አገሪቱ ላይ ችግር ሲከሰት እኮ ሀብታም በዜና ነው የሚሰማው፡፡
  • እንዳይመስልሽ?
  • እንዴት?
  • የከፋ ነገር ከመጣ ሀብታሙ ራሱ ዜና ሊሆን ይችላል፡፡
  • እ…
  • ሀብት መቼም የሁሉ ነገር መልስ እንዳልሆነ ታውቂያለሽ፡፡
  • በዚህ ሐሳብ ብዙም አልስማማም ባክህ፡፡
  • ለምን?
  • ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ የሚለው ነው ብዙ የሚገባኝ፡፡
  • እ…
  • ይኸው በቀድሞው ሥርዓት ሀብት የሰበሰቡ አሁን ምን ሆኑ?
  • እ…
  • ከሕግ በላይ የሆኑ ሰዎች እንዳሉ እኮ ግልጽ ነው፡፡
  • ማን ነው ያለው?
  • እሱንማ የአገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ነው የሚናገረው፡፡
  • ምን አልሽ?
  • ለማንኛውም አንተም የድርሻህን በጊዜ ብትወስድ ጥሩ ነው፡፡
  • ሲኖር ነዋ፡፡
  • እሱማ ከአንተ በፊት የነበሩት ጠራርገው እንደበሉት አውቃለሁ፡፡
  • ተይኝ እስቲ፡፡
  • ለማንኛውም ሌላው ቢቀር አንድ ነገር ለሁላችንም አመቻችልን፡፡
  • ምን?
  • ቪዛ!

[ለክቡር ሚኒስትሩ አንድ ባለሀብት ስልክ ደወለላቸው]

  • ያሳዝናል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምኑ?
  • ሁሉ ነገር፡፡
  • አልገባኝም?
  • ክቡር ሚኒስትር አገሪቱ እኮ ተስፋ አስቆራጭ ሆናለች፡፡
  • እንደዚህማ አትሁን፡፡
  • ምን ላድርግ ክቡር ሚኒስትር?
  • ለውጥ ላይ ነን እኮ፡፡
  • ተው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምነው?
  • ለውጡማ ተቀልብሷል፡፡
  • እ…
  • እሱን ማረጋገጥ እችላለሁ፡፡
  • እንዴት?
  • ክቡር ሚኒስትር ብዙ ጊዜ ነው እኮ ዕድል የሰጠናችሁ፡፡
  • እሱንማ እናውቃለን፡፡
  • ግን አገሪቱ እየባሰባት እንጂ ስትሻሻል አላየንም፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • ይኸው የእኔ ፋብሪካ እንኳን ለሦስተኛ ጊዜ እኮ ነው ጥቃት የደረሰበት፡፡
  • ለምን?
  • ገንዘብ አልሰጥም ስላልኩ ነዋ፡፡
  • ለማን?
  • ለስውር መንግሥቱ ነዋ፡፡
  • የምን የስውር መንግሥት ነው?
  • ይኼ እኮ የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡
  • ምኑ ነው የአደባባይ ሚስጥሩ?
  • ከመንግሥት ውጪ ሌላ ስውር ኃይል መኖሩ ነዋ፡፡
  • ምንድነው የምታወራው?
  • ክቡር ሚኒስትር ይህ ኃይል ባለሀብቶችን እያስጨነቀ ነው፡፡
  • ምን አድርጉ ብሎ ነው የሚያስጨንቀው?
  • ገንዘብ አምጡ እያለ ነዋ፡፡
  • እ…
  • አላመጣም ያለ ባለሀብት የእጁን ያገኛል፡፡
  • ወይ ጣጣ?
  • እኔም እንግዲህ የዚያ ገፈት ቀማሽ ነኝ፡፡
  • ማለት?
  • ይኸው ገንዘብ አልሰጥም በማለቴ ጥቃት ደርሶብኛል፡፡
  • ይኼማ ሕገወጥ ድርጊት ነው፡፡
  • የአገሪቱ ሕገወጥነት ከተንሰራፋ እኮ ቆየ፡፡
  • እ…
  • የሕግ የበላይነት ከተረሳ ሰነባበትን፡፡
  • እንደዚህ አትበል፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ራሱ ሕግ ማስከበር ካቃተው ሰነባበተ እኮ፡፡
  • እ…
  • ለማንኛውም አደዋወሌ ለመሰነባበት ነው፡፡
  • የምን ስንብት ነው?
  • ከእነ ቤተሰቤ ልንለቅ ነው፡፡
  • ምን?
  • አገር!

[ለክቡር ሚኒስትሩ ሌላ ሚኒስትር ስልክ ደወሉላቸው]

  • ምን እየተካሄደ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የት?
  • አገሪቱ ውስጥ ነዋ፡፡
  • ለውጥ ነዋ፡፡
  • ነውጥ ማለትዎ ነው?
  • ኧረ አይባልም፡፡
  • እንዴት አይባልም?
  • አንተ ሚኒስትር ነሃ፡፡
  • ብሆንስ?
  • እንዴት አገሪቱ ውስጥ ነውጥ አለ ትላለህ ታዲያ?
  • መቼም ሰላም አለ አልል ታዲያ?
  • ለውጥ ላይ ነን ነው የሚባለው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ሁሉም ነገር አንገሽግሾኛል፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • ሥልጣን ላይ የወጣነው እኮ ሕዝብን ለማገልገል ነው፡፡
  • ማን አይደለም አለህ ታዲያ?
  • እሱን እያደረግን ግን አይደለም፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • ሕዝብ እኮ እያለቀ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ምን ይደረግ ታዲያ?
  • ይኼ ምን ማለት እንደሆነ ያውቃሉ?
  • ምን ማለት ነው?
  • እኛ ሥራችንን እየሠራን አይደለም ማለት ነው፡፡
  • ያለብንን ፈተና ታውቃለህ አይደለም እንዴ?
  • ባውቅስ ክቡር ሚኒስትር?
  • ሁሉም ነገር በአንዴ አይለወጥማ፡፡
  • ሕግ ማስከበር ግን የእኛ ኃላፊነት ነው፡፡
  • እሱማ ልክ ነው፡፡
  • አሁን ግን ግለሰቦችና ቡድኖች ከሕግ በላይ እየሆኑ ነው፡፡
  • እ…
  • በዚህ ምክንያት ደግሞ በርካቶች እያለቁ ነው፡፡
  • አውቃለሁ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ታዲያ እንዴት እንቅልፍ ይወስድዎታል?
  • እ…
  • አገራችን ላይ ይኼ ሁሉ እየሆነ እንቅልፍ መተኛት አልቻልኩም፡፡
  • ጭንቀትህ ይገባኛል፡፡
  • እሱ መፍትሔ አይሆንም፡፡
  • አሁን እኮ እያደረግን ያለነው ከዚህ የባሰ ዕልቂት እንዳይመጣ ነው፡፡
  • እንደዚህ ግን ነገሮች አይቀጥሉም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ይደረግ?
  • ይኼንን ጥያቄ ነዋ መመለስ ያለብን፡፡
  • እ…
  • እኔ በበኩሌ የማደርገውን አውቃለሁ፡፡
  • ምን ልታደርግ ነው?
  • ሕዝብ እንደዚህ እያለቀ ሥልጣን ላይ መቀመጥ አልችልም፡፡
  • ማለት?
  • እለቃለሁ፡፡
  • ከምን?
  • ከሥልጣን!

[ክቡር ሚኒስትሩ ቢሮ ከአማካሪያቸው ጋር እያወሩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር በጣም ተጨንቄያለሁ፡፡
  • በአገሪቱ ጉዳይ ነው?
  • ከአገሪቱ በላይ ያስጨነቀኝ የፓርቲያችን ጉዳይ ነው፡፡
  • እ…
  • ያው ፓርቲያችን ፈረሰ ማለት እኮ አገር ፈረሰ ማለት ነው፡፡
  • ይህቺን ነገር የት ነበር የሰማሁዋት?
  • እ…
  • ፓርቲና አገርን ምን አገናኛቸው?
  • ክቡር ሚኒስትር እኛ አገር ሁለቱ መቼ ይለያያሉ?
  • ማወቅ ያለብህ ግን ሁለቱ አንድ ያለ መሆናቸውን ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ውህደቱ ግን ጠቃሚ አይመስለኝም፡፡
  • ለምን?
  • እውነቱን ልንገርዎት?
  • አዎ ንገረኝ፡፡
  • እንደ እኔ ዓይነት ሰዎች ምንም ቦታ አያገኙማ፡፡
  • እንዴት?
  • ማለቴ ፓርቲያችን ተዋህዶ አንድ ከሆነ አቅም ያላቸው ሰዎች ብቻ ናቸዋ ወደ ሥልጣን የሚመጡት፡፡
  • ዶሮ ብታልም ጥሬዋን አሉ፡፡
  • እ…
  • ስለራስህ ብቻ ነው አይደል የምታስበው?
  • ክቡር ሚኒስትር ይኼን ቦታ ያገኘሁት አቅም ኖሮኝ አይደለም እኮ፡፡
  • እሱንም ማወቅህ ጥሩ ነው፡፡
  • እውነቴን እኮ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለነገሩ አንተ ጥሩ አቅምህ ምን እንደሆነ ታውቃለህ?
  • ምንድነው?
  • ሴራህ ነዋ፡፡
  • እ…
  • ስለዚህ መቀላቀል ትችላለህ፡፡
  • ማንን?
  • ሴረኛ ፓርቲውን!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

ኢትዮጵያ በ2023 የሚኖራት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለ18 ቀናት ግዢ መፈጸሚያ ብቻ እንደሚሆን አይኤምኤፍ ተነበየ

ኢትዮጵያ በ2023 የሚኖራት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለ0.6 ወር ወይም...

ጦርነቱና ሒደቱ

ሦስት ሳምንታት ያስቆጠረው ሦስተኛው ዙር የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት አሁንም...

የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ ያለው ሦስተኛው ከግል ባንክ ሆነ

የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን ከ100 ቢሊዮን...

ወ/ሮ መሰንበት ሸንቁጤ የአዲስ አበባን ንግድና ዘርፍ ምክር ቤትን በፕሬዚደንትነት ለመምራት በተደረገው ምርጫ አሸነፉ

የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤትን በፕሬዚደንትነት ለመምራት፣...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...

ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመው ራሚስ ባንክ ዛሬ ሥራ ይጀምራል

በኢትዮጵያ ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመው...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...