Monday, March 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናለህዳሴው ግድብ ከመዋጮው በበለጠ ብሔራዊ መግባባት ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል ተባለ

ለህዳሴው ግድብ ከመዋጮው በበለጠ ብሔራዊ መግባባት ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል ተባለ

ቀን:

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሕዝብ ተሳትፎ ተጠናክሮ የቀጠለ ቢሆንም፣ ከመዋጮ በበለጠ ብሔራዊ መግባባት ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት እንደገለጸው፣ የግድቡ ግንባታ በኢትጵያውያን አስተዋጽኦ እንደሚጠናቀቅ ያለውን እምነት ገልጾ፣ ሕዝቡ የውስጥ አንድነቱንና መግባባቱን ጠብቆ ከቀጠለ የተጀመረው ግንባታ በአጭር ጊዜ ዕውን እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡

በ2011 ዓ.ም. 970 ሚሊዮን ብር በቦንድ ግዥ ድጋፍ መሰብሰቡን ያስታወሱት የጽሕፈት ቤቱ ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም፣ አሁንም የሕዝቡ ተሳትፎ በጥሩ ሁኔታ መቀጠሉንና በበጀት ዓመቱ ሩብ ዓመት 168.9 ሚሊዮን ብር የቦንድ ግዥ መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡

ሕዝባዊ ተሳትፎው ከግድቡ ግንባታ አፈጻጸምና የሦስትዮሽ ድርድሩ ጋር በተያያዘ ሞቅና ቀዝቀዝ እያለ እንደሆነ የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ የሕዝቡ ድጋፍ ግን ያለማቋረጥ መቀጠሉን አስረድተዋል፡፡ በ2012 ዓ.ም. የብሔራዊ ምክር ቤቱ ብሔራዊ መግባባትን የሚያጎለብቱና ለግድቡ ገቢ የሚያስገኙ ሁነቶችን አቅዶ ወደ ተግባር መግባቱን ጠቁመው፣ የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀት የተጀመረውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አክለዋል፡፡ ከውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በትብብር እየሠሩ መሆኑንም አቶ ኃይሉ ተናግረዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...