Sunday, March 26, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትበአፍሪካ ዋንጫ ምድብ ማጣሪያ ዋሊያዎቹ ዝሆኖቹን አሸነፉ

በአፍሪካ ዋንጫ ምድብ ማጣሪያ ዋሊያዎቹ ዝሆኖቹን አሸነፉ

ቀን:

ካሜሮን እ.ኤ.አ. በ2021 ለሚያስተናግደው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የአይቮሪኮስት (ዝሆኖቹ) አቻውን ያስተናገደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) በምድብ ማጣሪያው የመጀመርያውን ሦስት ነጥብ ያስመዘገበበትን ውጤት አግኝቷል፡፡

ኅዳር 9 ቀን 2012 ዓ.ም. በተካሄደው ጨዋታ በእንግዳው ቡድን ከ1ለ0 ተመሪነት በሱራፌል ዳኛቸውና አምበሉ ሺመልስ በቀለ አማካይነት ባስቆጠራቸው ሁለት ጎሎች 2 ለ1 አሸንፏል፡፡

በነጥብ ጨዋታ ሽንፈት ያላስተናገደው የባህር ዳር ስታዲዮም ዋሊያዎቹ በሜዳቸው የሚያደርጓቸውን ሁለት ጨዋታዎች ማለትም የኒጀርና የማዳጋስካር ጨዋታዎችን እንደሚያስተናግድ ይጠበቃል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአሠልጣኝ አብርሃም መብርሃቱ እየተመራ እስካሁን ካደረጋቸው ስድስት የነጥብ ጨዋታዎች ሦስት ጊዜ ሽንፈትን ሲያስተናግድ፣ ሦስት ጊዜ ነጥብ ሲጋራና አንድ ጊዜ ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...