- Advertisement -

ኢቦላን ለመከላከል ከ55 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለመደገፍ ቃል ተገባ

የአፍሪካ ኅብረት ባዘጋጀው አፍሪካን ከኢቦላ የመቋቋም ፎረም ላይ ከ55 ሚሊዮን ዶላር በላይ ድጋፍና የተለያዩ ዕርዳታዎችን ለመስጠት የአፍሪካ ኅብረት አባል አገሮችና አጋሮች ቃል ገቡ፡፡

ሰኞ ኅዳር 22 ቀን 2012 ዓ.ም. በተካሄደውና በአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ በተመራው መርሐ ግብር፣ በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እየተሠራጨ የሚገኘውን የኢቦላ ቫይረስ እስከወዲያኛው ለማስቆም የሚሆን ድጋፍ ከአፍሪካ ኅብረት አባል አገሮችና አጋር አገሮች ለመሰብሰብ ነበር፡፡

የአፍሪካ ኅብረት የማኅበራዊ ጉዳዮች ኮሚሽነር አሚራ ኤልፋዲል፤ መርሐ ግብሩ የተሳካ እንደነበርና ተሳታፊዎቹ በገንዘብ እንዲሁም ከገንዘብ ውጪ ያሉ ድጋፎችን ለማበርከት ቃል መግባታቸውን ገልጸዋል፡፡

ከሁሉም ተሳታፊዎች አንድነትን እንዳዩ የገለጹት ኮሚሽነሯ፣ መርሐ ግብሩ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መንግሥት ኢቦላን ለመከላከልና ለማጥፋት በሚያደርገው ዝግጁነትና አቅም ግንባታ ላይ ድጋፍ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል፡፡

እሳቸው እንደገለጹት፣ ቃል ከተገባው 55 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ ትልቁን ቦታ የያዘው የአውሮፓ ኅብረት ድጋፍ ነው፡፡ ቻይና አንድ ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት አንድ ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል ከገቡት መካከል እንደሆኑ ታውቋል፡፡

ከገንዘብ ውጪ ስለተደረገው ድጋፍም ሲገልጹ፣ የተለያዩ የአፍሪካ ኅብረት አጋር አገሮች በሰው ኃይል፣ በሕክምና ቁሳቁሶች፣ በመድኃኒቶች እንዲሁም በሰው ኃይል አቅም  ግንባታ ላይ ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡

- Advertisement -

በመጪው ጥር ወር ተመሳሳይ መርሐ ግብር እንደሚኖር፣ ይህም እንዲሁ የተለያዩ የአፍሪካ አገሮችን ለመደገፍ የሚካሄድ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡

የኢቦላ ቫይረስ ለመጀመርያ ጊዜ የተከሰተው በ1976 ዓ.ም. ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው በማዕከላዊና ምዕራብ አፍሪካ አገሮች ገጠራማ አካባቢዎች እየተሠራጨ ይገኛል፡፡ በተለይ በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሱዳን፣ ጋቦን፣ አይቮሪኮስት እንዲሁም ዩጋንዳ በሽታው በተደጋጋሚ ሲከሰት ታይቷል፡፡

የዓለም የጤና ድርጅት በቅርብ ባወጣው መረጃ መሠረት፣ እስካሁን በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብቻ 3‚313 ኬዞች ያጋጠሙ ሲሆን፣ ከዚህ መሀል 3‚195 ኢቦላ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ ከእነዚህም 2200 ሲሞቱ፣ 1078 ድነዋል፡፡ የተቀሩት በሕክምና ክትትል ላይ ናቸው ተብሏል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘለት የሥነ ተዋልዶ ጤና ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

በኢትዮጵያ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተከሰቱ ጦርነቶችና ግጭቶች ምክንያት እየተስተጓጎለ የመጣውን የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት መልሶ ለማጠናከር ያስችላል የተባለ የ1.28 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ...

ከአፋር በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ለተፈናቀሉ ተጨማሪ ድጋፍ ተጠየቀ

የከሰም ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች በሙሉ ተፈናቅለዋል ተብሏል በአፋር ክልል ገቢ ረሱ ዞን በሚገኙት በአዋሽ ፈንታሌና በዱለቻ ወረዳዎች በቀጠለው የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ከአካባቢው ለተፈናቀሉ ዜጎች እየቀረበ ያለው...

የአየር ንብረት ለውጥ በግብርናው ዘርፍና አመጋገብ ሥርዓት ላይ አደጋ ደቅኗል ተባለ

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየበረታ የመጣው የአየር ንብረት ለውጥ ጫና በኢትዮጵያ ግብርናና የአመጋገብ ሥርዓት ላይ አደጋ ደቅኗል ተባለ፡፡ ይህ የተነገረው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብና...

በመጀመሪያው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት 75 በመቶ ተጠቃሚዎች የመኪና ማቆሚያ መቸገራቸው በጥናት ተረጋገጠ

በኮሪደር ልማት ፕሮጀክት 75 በመቶ ተጠቃሚዎች የመኪና ማቆሚያ ቦታ ለማግኘት መቸገራቸው በጥናት መረጋገጡን፣ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮና ሁለት የግል ተቋማት አስታወቁ፡፡ ጥናቱ የቀረበው ጥር...

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ልምድ ያላቸው ሠራተኞች እየለቀቁብኝ ነው አለ

በደመወዝ ማነስ ምክንያት ልምድ ያላቸው ሠራተኞች እየለቀቁ መሆናቸውን፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የአገልግሎቱ የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዓለምሸት መሸሻ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ አገልግሎቱ...

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከቀዬአቸው ተፈናቅለው የነበሩ 563 ሺሕ ዜጎች መመለሳቸው ተገለጸ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልና ከክልሉ ውጪ በነበሩ የፀጥታ ችግሮች ምክንያት ተፈናቅለው በተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎች ተጠልለው ይገኙ የነበሩ 563 ሺሕ ዜጎች ወደ መኖሪያ ቀዬአቸው መመለሳቸውን፣ የክልሉ...

አዳዲስ ጽሁፎች

መንግሥት ገቢ ከመሰብሰብ ባሻገር ለሕዝብ ኑሮ ትኩረት ይስጥ!

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ ያለበት በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ ከሚሰበሰብ ታክስ ብቻ ሳይሆን ከግብርና፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከማዕድን፣ ከአገልግሎትና ከሌሎች ሀብት አመንጪ ዘርፎች ጭምር ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ቁጥራቸው...

የኢትዮጵያን ትንሳዔ ለማብሰርና ለመከወን ምን እናድርግ?

በጌታነህ አማረ ኢትዮጵያ ማለት ታላቅ አገር ቀደምት የሰው ዘር መገኛና የሥልጣኔ ባለቤት የሆነች አገር እንደነበረች ታሪክ ሲያወሳን ይኖራል። በዚያውም ልክ ይህች ታላቅ ነበረች የምትባል አገር...

የምድራችን (የሰው ልጆች) ተማፅኖ — አረንጓዴ ፖለቲካ!

(ወጥመዶችና ማምለጫችን) በታደሰ ሻንቆ የወጥመዶች ዓለም በአፍሪካ ቀንድ አገሮች ዘንድ ያሉ ውዝግቦችና ግጭቶች ምንም ተቀባቡ ምን፣ መሬትን ውኃን አፈርን ማዕድናትን ንግድንና መሰል ጥቅሞችን የተመለከቱ ናቸው፡፡ በእነዚህ...

‹‹መንግሥት ከሁሉም ነገር በላይ ቅድሚያ ሰጥቶ የኢኮኖሚ ጫናውን ለመቀነስ የነዳጅ ድጎማውን መቀጠል ይኖርበታል›› ሰርካለም ገብረ ክርስቶስ (ዶ/ር)፣  የነዳጅ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ

የነዳጅ ግብይት ሥርዓትን ለመዘርጋትና ለመቆጣጠር ያስችላል የተባለ አዲስ አዋጅ ባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቋል፡፡ በኢትዮጵያ በነዳጅ ሥርጭት ግብይትና በአጠቃላይ በዘርፉ ያሉትን ማነቆዎች...

ስለካፒታል ገበያ ምንነትና ፋይዳ ያልተቋረጠና የተብራራ መረጃ ማድረስ ያሻል!

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡ አገራዊ ኢኮኖሚውን ከመደገፍና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች የሚውል ካፒታል ለማሰባሰብ እንደ አንድ አማራጭ የሚወሰድና ለኢትዮጵያ እንደ አዲስ ምዕራፍ የሚታይ ዕርምጃ...

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘለት የሥነ ተዋልዶ ጤና ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

በኢትዮጵያ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተከሰቱ ጦርነቶችና ግጭቶች ምክንያት እየተስተጓጎለ የመጣውን የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት መልሶ ለማጠናከር ያስችላል የተባለ የ1.28 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን