Thursday, June 8, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ለክቡር ሚኒስትሩ የቀድሞ ሚኒስትር ስልክ ደወሉላቸው

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ ቢሯቸው ገባች]

  • ምን ፈለግሽ?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ሥራ ይዣለሁ፡፡
  • ተቆጡኝ እኮ፡፡
  • እኮ ለምን መጣሽ?
  • እንዲህ ተቆጥተውኝማ እንዴት እነግርዎታለሁ?
  • ታዲያ ለምን መጣሽ?
  • እሱማ አንድ ነገር ልነግርዎት ነበር፡፡
  • ምን?
  • አዲሱ የተመሠረተውን ፓርቲ የተመለከተ ነው፡፡
  • ምንድነው እሱ?
  • ትንሽ ፈርቼ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምንድነው ያስፈራሽ?
  • እንደ እኔ ዓይነቷን ጸሐፊ የሚቀንስ እየመሰለኝ ነው፡፡
  • ለምን?
  • ከዚህ በኋላ ሥራ የሚገኘው በብቃት ነው ሲባል ሰማሁ፡፡
  • ታዲያ ምን ችግር አለው?
  • እ…
  • ምነው ደነገጥሽ?
  • ኧረ ምንም፡፡
  • ለነገሩ ሥጋትሽ ገብቶኛል፡፡
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • አንቺ እዚህ ቦታ ላይ የተቀመጥሽው በብቃትሽ አይደለማ፡፡
  • እንዴት?
  • እዚህ መሥሪያ ቤት ያለውን ዋነኛ የሙስና ኔትወርክ የመሠረትሽው አንቺ እንደሆንሽ አውቃለሁ፡፡
  • እ…
  • በዚያ ላይ ከዚህ ወደዚያ ወሬ እያመላለሽ ሠራተኛውን ታባያለሽ፡፡
  • ኧረ እኔ እንደዚህ ዓይነት ሰው አይደለሁም፡፡
  • ስለሁሉም ነገር መረጃ አለኝ፡፡
  • እኔ እኮ የኢሕአዴግ ደጋፊ ነኝ፡፡
  • እሱም እያበቃለት እንደሆነ አልሰማሽም?
  • እ…
  • ከዚህ በኋላ የፓርቲ ደጋፊ በመሆን ሥራ አይገኝም፡፡
  • ምን አሉኝ?
  • ብልፅግና ፓርቲ በብቃት ብቻ ነው የሚያምነው፡፡
  • ምን ተሻለኝ ታዲያ?
  • ራስሽን ማብቃት ነዋ፡፡
  • ትምህርት እኮ ብዙም አይገባኝም፡፡
  • ለነገሩ አንቺ ሴራ ነው የሚገባሽ፡፡
  • እ…
  • ሲቀጥል ሌብነት፡፡
  • አይስደቡኝ እንጂ ክቡር ሚኒስትር?
  • ይኼም ሲያንስሽ ነው፡፡
  • ተው እንጂ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ከዚህ በኋላ ከሠነፎች ጋር መጓዝ አንችልም፡፡
  • ወይ ጣጣ፡፡
  • ስለዚህ በጊዜ አስቢበት፡፡
  • ምኑን?
  • ቀጣይ ቦታሽን፡፡
  • ምን እያሉኝ ነው?
  • ወስኛለሁ፡፡
  • ምን ለማድረግ?
  • ላባርርሽ!

[ለክቡር ሚኒስትሩ አንድ ደላላ ስልክ ደወለላቸው]

  • ደስ ይላል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምኑ?
  • ብልፅግና ነዋ፡፡
  • ምኑን ወደድከው?
  • ስሙ ራሱ ደስ ሲል፡፡
  • ወደድከው?
  • ምን ጥያቄ አለው?
  • ለምን ወደድከው?
  • በቃ ሁላችንም ልንበለፅግ ነዋ፡፡
  • ዝም ብሎማ አይበለፀግም፡፡
  • ማለት?
  • ብልፅግና በሥራ ነው የሚመጣው፡፡
  • እሱማ እንሠራለን፡፡
  • አንተ መቼ ሠርተህ ታውቃለህ?
  • ምን እያሉ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ያለፋህበትን አይደል እንዴ የምታጭደው?
  • አልገባኝም?
  • ሰዎችን ከባለሥልጣን ጋር አገናኘሁ ብለህ አይደል እንዴ ገንዘብ የምትቀበለው፡፡
  • ምን ችግር አለው?
  • ያለሥራ ገንዘብ እያገኘህ አገሪቱን ወደኋላ ታስቀራታለሃ፡፡
  • ምን?
  • ስማ ከዚህ በኋላ እያጭበረበሩ መክበር አይቻልም፡፡
  • ማን ነው አጭበርባሪው?
  • እንደ አንተ ዓይነቱ ነዋ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እኔ እኮ ለእርስዎ ብዙ ነገር እያሰብኩልዎት ነው፡፡
  • ምንድነው የምታስብልኝ?
  • እንዴት እንደሚበለፅጉ ነዋ፡፡
  • እንዴት ነው የምበለፅገው?
  • ይኸው እኔ የማውቃቸው በርካታ ባለሀብቶች አሉ፡፡
  • እሺ፡፡
  • የተለያዩ ጥያቄዎች ነው ያሏቸው፡፡
  • እሺ፡፡
  • ስለዚህ የባለሀብቶቹን ጥያቄዎች ይመልሳሉ ከዚያም የእርስዎ የሕይወት ጥያቄ ይመለሳል፡፡
  • ትሰማኛለህ?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • አዲሱ ፓርቲ ለእንደ አንተ ዓይነቱ ሌባ ቦታ የለውም፡፡
  • ምን?
  • ከዚህ በኋላ እየሰረቁ ሀብት ማካበት ይቀራል፡፡
  • ማን ሲሰርቅ አዩ?
  • አንተ ነሃ፡፡
  • ምን?
  • ስለሁሉም እንቅስቃሴህ መረጃ አለኝ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትሩ እኔ የፓርቲው አባል መሆን እፈልጋለሁ፡፡
  • የትኛው ፓርቲ?
  • የብልፅግና ነዋ፡፡
  • ለአንተ እንኳን ቦታ የለንም፡፡
  • ለምን?
  • ባይሆን ለአንተ የሚሆነውን ሌላ ፓርቲ አለ፡፡
  • ምን የሚሉት?
  • የሌቦች ፓርቲ!

[ለክቡር ሚኒስትሩ አንድ ባለሥልጣን ስልክ ደወሉላቸው]

  • ብዙ ጥያቄ አለኝ ክቡር ሚኒስትር?
  • የምን ጥያቄ?
  • አዲሱ ፓርቲ ላይ ነዋ፡፡
  • እኮ ምን ዓይነት?
  • የሕዝባችን ጥያቄ መቼ ተመለሰ?
  • ምን እያሉ ነው?
  • መጀመሪያ የሕዝቡ ጥያቄ መመለስ አለበት፡፡
  • የትኛው ሕዝብ?
  • የክልላችን ሕዝብ፡፡
  • የክልላችን ሕዝብ ጥያቄ እኮ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ የተለየ አይደለም፡፡
  • ቢሆንስ ምን ያስቸኩለናል?
  • ምኑ ላይ ነው የቸኮልነው?
  • ውህደቱ ላይ ነዋ፡፡
  • ውህደቱ እኮ ለዓመታት ስንወያይበት የነበረ ነው፡፡
  • እ…
  • በአገሪቱ ጉዳይ አንዱ በዪ ሌላው ተመልካች መሆን የለበትም ስንባባል ነበር እኮ፡፡
  • ብቻ እኔ አላማረኝም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምኑ ነው ያላማረህ?
  • አሁን እየሄድንበት ያለው መንገድ፡፡
  • ለምን?
  • ምንም ሊገባኝ አልቻለም፡፡
  • ለዓመታት የታገልንበት አጀንዳ እኮ ነው፡፡
  • እ…
  • ችግር በፈጠረው ሥርዓት መፍትሔ ማፍለቅ አይቻልም፡፡
  • ማን ነው ያለው?
  • አንተም ከዚህ በፊት ስትለው ነበር፡፡
  • ሐሳቤን መቀየር አልችልም?
  • ምንም አታስብ፣ አሁን የምንገነባው ሥርዓት የሐሳብ ልዩነትን የሚደግፍ ነው፡፡
  • እኔ ግን ውህደቱን አልደግፍም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለምን እንደማትደግፈው ትነግረኛለህ?
  • የሕዝባችን ጥያቄ አልተመለሰማ፡፡
  • የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ ሲመለስ እኮ ሁሉም ጥያቄ ይመለሳል፡፡
  • የእኔስ ጥያቄ?
  • ምንድነው የአንተ ጥያቄ?
  • የሥልጣን ነዋ፡፡
  • ኪኪኪ…
  • ምን ያስቅዎታል ክቡር ሚኒስትር?
  • ለሕዝቡ ነው የምታገለው አላልከኝም እንዴ?
  • እኔስ የሕዝቡ አካል አይደለሁም እንዴ?
  • አንድ ነገር ልንገርህ፡፡
  • ምን?
  • ከዚህ በኋላ በዚህች አገር አንድ ነገር ይቀራል፡፡
  • ምን?
  • ተረኝነት!

[ለክቡር ሚኒስትሩ የቀድሞ ሚኒስትር ስልክ ደወሉላቸው]

  • አገር እያፈራረሳችሁ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • አገር እየነባን ነው እንጂ፡፡
  • ማን ያፈረሰውን?
  • እናንተ፡፡
  • አሃዳዊ ሥርዓት በመገንባት ነው አገር የምትገነቡት?
  • አሃዳዊውማ የእናንተ ነበር፡፡
  • እ…
  • አገሪቱን በአንድ ሐሳብ ረግጣችሁ ስትገዙ የነበራችሁት እኮ እናንተ ናችሁ፡፡
  • ሕገ መንግሥቱን እየናዳችሁት እኮ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እናንተ መቼ አክብራችሁት ታውቁና?
  • እ…
  • እንደፈለጋችሁ አልነበር እንዴ ስትፈነጩበት የነበረው?
  • ግድ የለም አሁን ጊዜው የእናንተ ነው፡፡
  • ጊዜው የሕዝቡ ነው፡፡
  • እንዴት?
  • የኢትዮጵያ ሕዝብ ተባብሮ በመሥራት የሚበለፅግበት ጊዜ ነው፡፡
  • በእኛ ጊዜ አገሪቱ በ11 በመቶ ስታድግ እንደነበር እንዳይረሱ ክቡር ሚኒስትር?
  • 11 በመቶ ያደገችው አገሪቱ ሳትሆን እናንተ ናችሁ፡፡
  • እኛ እነማን ነን?
  • ሌቦች ባለሥልጣናት ናችኋ፡፡
  • ለማንኛውም እኛ አገር የማዳን ኮንፈረንስ እናዘጋጃለን፡፡
  • የኮንፈረንሱን ስም ቀይሩት፡፡
  • ምን እንበለው?
  • ራስን የማዳን ኮንፈረንስ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

በኦሮሚያ ክልል በስድስት ከተሞች የተዋቀረውን ሸገር ከተማን የማደራጀት ሥራ ተጀመረ

በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ስድስት ከተሞች የተዋቀረው ሸገር ከተማን...

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው አሠራር ወጣ ያለውን ‹‹የወደፊት ግብይት›› ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው የማገበያየት ተግባሩ ወጣ ያለና በኢትዮጵያ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው አሠራር ወጣ ያለውን ‹‹የወደፊት ግብይት›› ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው የማገበያየት ተግባሩ ወጣ ያለና በኢትዮጵያ...

የባንክ ማቋቋሚያ መሥፈርት እንደሚጠነክር ሚኒስትሩ ተናገሩ

 ባንኮች ስለውህደት እንዲያስቡም መክረዋል በኢትዮጵያ ውስጥ ባንክ ለማቋቋም የሚያስፈልገው መሥፈርት...

ማን ይቻለን?

በጠዋት የተሳፈርንበት ታክሲ ውስጥ በተከፈተው ሬዲዮ፣ ‹‹ይኼኛው ተራራ ያን...

በኢትዮ ኤርትራ ግንኙነት አንድ ድንጋይ ደጋግሞ እንዳይመታን

ከጣሊያን ቅኝ ተገዥነት በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን በኮንፌዴሬሽን፣ ቆየት ብሎም እንደ አንድ የኢትዮያ ግዛት አካል የነበረችው ኤርትራ ከደርግ ሥርዓት መውደቅ በኋላ ነፃ አገር ሆናለች፡፡ ነፃ አገር መሆንና ከኢትዮጽያ ጋር መቀጠል በወቅቱ ብዙ ሲባልለት የነበረ ጉዳይ ነበር፡፡
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አመሻሹን መኖሪያ ቤታቸው ሲደርሱ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈው የማዕከላዊ ኮሚቴ ገለጻ እየተከታተሉ አገኟቸውና አጠገባቸው ተቀምጠው የደረሱበትን አብረው መከታተል እንደጀመሩ፣ ባለቤታቸው ቴሌቪዥኑን ትተው መጠየቅ...

እኔ ምለው? እሺ... አንቺ የምትይው? የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ አባላት እንዲያወሩ ወይም እንዲጠይቁ አይፈቀድም እንዴ? እንዴት ይከለከላል? ታዲያ ለምንድነው ፕሬዚዳንቱ ብቻ የሚያወሩት? እያወሩ አይደለም፣ ገለጻ እያደረጉ ነው። ቢሆንም አንድም አባል...

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...