Monday, May 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበመጪው ታኅሣሥ የምትወነጨፈው የኢትዮጵያ ሳተላይት

በመጪው ታኅሣሥ የምትወነጨፈው የኢትዮጵያ ሳተላይት

ቀን:

በቻይና የተሠራችውና 72 ኪሎ ግራም የምትመዝነው የኢትዮጵያ ሳተላይት ታኅሣሥ 10 ቀን 2012 .ም. ከቻይና ቤጂንግ 400 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትወነጨፋለች::

ከመሬት 700 ኪሎ ሜትር ርቃ የምትቀመጠው ሳተላይት፣ በግብርና በአካባቢ ጥበቃና  በአየር ሁኔታ ዙሪያ መረጃ የምትሰጥ ይሆናል፡፡

የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እንዳስታወቀው፣ ኢትዮጵያ የራሷን የሳተላይት ቴክኖሎጂ መጠቀሟ ከቀሪው ዓለም ጋር እንድትወዳደር ያስችላታል፡፡

የተለያዩ መረጃዎችን ለማግኘት ከፍተኛ የኪራይ ገንዘብትከፍል የነበረችው ኢትዮጵያ ሳተላይቱ ጥቅም ላይ ሲውል ግን በዓመት 350 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪን ማስቀረት ትችላለች፡፡

ሳተላይቱ ጥቅም ላይ ሲውል፣ አስፈላጊ መረጃዎችን በአራት ቀናት ውስጥ አደራጅቶ ማምጣት የሚቻል ሲሆን፣ የግብርና እና ሌሎች መረጃዎችን በፍጥነትናጥራት ለማግኘትም ያስችላል፡፡

ኢትዮጵያ ሳተላይት ለማልማትና ለማምጠቅ 2009 .ም. ከቻይና መንግሥት ጋር ከስምምነት መድረሷ ይታወሳል።

በእንጦጦ ኦብዘርቫቶሪና ምርምር ማዕከል ውስጥ ሲገነባ የቆየው የሳተላይት መቆጣጠሪያና መረጃ መቀበያ ጣቢያ መጠናቀቁንም ኢንስቲቲዩቱ አስታውቋል፡፡

የሳተላይት ቴክኖሎጂው ከቻይና መንግሥት ጋር በተደረገ ትብብር የተገነባ መሆኑ ይታወቃል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመስቀል አደባባይ የመግቢያ ክፍያ ለምን?

ወጣቶች፣ ሕፃናትና አረጋውያን ሳይቀሩ መንፈሳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሐሳባቸውን በነፃነት...

በሕገ መንግሥቱ የተዋቀረው ‹‹የብሔር ፖለቲካ›› እና ‹‹ሥርዓቱ›› ያስከተለው መዘዝና መፍትሔው

(ክፍል አራት) በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ) ባለፈው ጽሑፌ (በክፍል ሦስት) አሁን ያለው...

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብና የመንግሥት መሪ ምሥል

በበቀለ ሹሜ በ2015 ዓ.ም. መጋቢት ወር ውስጥ ይመስለኛል በ‹ሸገር ካፌ›...

ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ያደረገው አዋጅ የፍትሐዊነት ጥያቄ አስነሳ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ተቋማዊና...