የኢትዮጵያ ትልቁ ጣና ሐይቅ 84 ኪ.ሜ. ርዝማኔ እና 65 ኪ.ሜ. ስፋት ሲኖረው ባጠቃላይ 3,600 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። የዓባይ ወንዝ ከምንጩ የሚያልፍበትና ከ37 በላይ ደሴቶችን ያቀፈው ጣና በርካታ ገዳማትን ከጥንታዊ ቅርሶቻቸው ጋር አቅፎ ይዟል፡፡ ከማዕከላዊ ጎንደር ጋር ከሚያያዘው ሰሜናዊ ጣና የጎርጎራ ወደብ መነሻ አድርገን የቃኘው ሐይቁና የተወሰኑት ደሴቶች ገጽታን እነዚህ ፎቶዎች ያሳያሉ፡፡