አሥራ አራተኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ኅዳር 29 ቀን 2012 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል አስተናጋጅነት በአዲስ አበባ ስታዲየም “ሕገ መንግሥታዊ ቃል ኪዳናችን ለዘላቂ ሰላም” በሚል መሪ ቃል ተከብሯል። በሥነ በዓሉ የየብሔረሰቦችን ባህልና አኗኗር የሚያሳዩ ትርዒቶች ለዕይታ በቅተዋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኰንን፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ተገኝተዋል፡፡ ለከርሞ በዓሉን የሚያስተናግደው የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር መሆኑ ታውቋል፡፡ የዘንድሮውን በዓል ምክንያት በማድረግ የቀቤና ብሔረሰብ ልዑካን ቡድን አባላት የደም ልገሳ አድርገዋል፡፡
- Advertisement -
- Advertisement -
- Advertisement -
ፌርማታ ፅሁፎች
ትኩስ ፅሁፎች
- Advertisement -
- Advertisement -