Sunday, March 26, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትበአዲስ አበባ በ122 የሥልጠና ጣቢያዎች 2,680 ታዳጊዎች ለማሠልጠን ታቅዷል

በአዲስ አበባ በ122 የሥልጠና ጣቢያዎች 2,680 ታዳጊዎች ለማሠልጠን ታቅዷል

ቀን:

የበርካታ ስፖርቶች መሠረት መሆኗ የሚነገርላት አዲስ አበባ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በክልል ከተሞች ብልጫ ሲወሰድባት መመልከት የተለመደ ሆኗል፡፡ ለዚህ በማሳያነት በእግር ኳሱ እየተወሰደባት ያለውን ብልጫ መመልከት በቂ ይሆናል፡፡ በፕሪሚየር ሊግ ብቻ ከስድስትና ሰባት ክለብ በላይ የነበራት አዲስ አበባ አሁን ላይ በቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ብቻ ተወክላ ትገኛለች፡፡

የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ለዚህ ችግር መፍትሔ እንዲሆን የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት ላይ ለመሥራት እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ስፖርት ኮሚሽን ከሰሞኑ ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያስረዳው ከሆነ፣ በ2012 የውድድር ዓመት በከተማዋ ከሁሉም ወረዳዎች የተውጣጡ 2,680 ታዳጊዎች በ122 የሥልጠና ጣቢያዎች ዘመናዊና ሳይንሳዊ ሥልጠና እንዲያገኙ ቅድመ ሁኔታዎችን እያመቻቸ ይገኛል፡፡

ኮሚሽኑ ለዚህ ይረዳው ዘንድ በከተማ አስተዳደሩ ሥር የሚገኙ ሁሉም ፌዴሬሽኖች ከእግር ኳስ በስተቀር ዓመታዊ ጉባዔያቸውን ማድረግ ብቻ ሳይሆን እንደየስፖርቱ ባህሪ ዕውቀቱና ብቃቱ ያላቸው አዳዲስ አመራሮች ምርጫ እንዲያከናውኑ መመሪያ ማስተላለፉ ታውቋል፡፡

ምርጫ ካደረጉ ፌዴሬሽኖች አትሌቲክስና ወርልድ ቴኳንዶ ጨምሮ የተሻለ ውጤት እያስመዘገቡ ካሉት መካከል የአዲስ አበባ ብስክሌት ፌዴሬሽን ይጠቀሳል፡፡ ባለፉት አራት ዓመታት ፌዴሬሽኑን በፕሬዚዳትነት ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ ረዘነ በየነ በድጋሚ በነበሩበት ኃላፊነት እንዲቀጥሉ በሙሉ ድምፅ መመረጣቸውን ጭምር በስፖርት ኮሚሽኑ ድረ ገጽ የተለቀቀው መረጃ ያመለክታል፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...