Friday, March 24, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
እኔ የምለዉመጪው ምርጫ ለትናንት ሙሾ በሚያወርዱና ለነገ ራዕይ ባላቸው መካከል ነው

መጪው ምርጫ ለትናንት ሙሾ በሚያወርዱና ለነገ ራዕይ ባላቸው መካከል ነው

ቀን:

በጥበበ ሳሙኤል ፈረንጅ   

ሰበብህን ቆጥበው፡፡ ጊዜ የማግኘት ጉዳይ ሳይሆን ጊዜ የመስጠት ጉዳይ ነው፡፡ ላንተ በጣም አስፈላጊ ከሆነ ጊዜ ስጥ” ያልታወቀ ሰው ከተናገረው የተወሰደ፡፡

ገራችን የፖለቲካ ጉዳ በተለይም ኢሕአግ ሥልጣን ከተቆጣጠረበት ጊዜ ጀምሮ ምርጫ አወዛጋቢ ያልሆነበት ጊዜ የለም፡፡ ኢሕአዴግ በጉልበቱ የሽግግር መንግሥት አቋቁሞ ራሱን ያፀደቀውን ቻርተር ጥሶ ጊዜውን ካራዘመ በኋላ፣ አገራችን ውስጥ “ቋሚ የሆነ መንግሥት” ይመሠረት ዘንድ በግንቦት 1987 ዓ.. ነበር የመጀመርያው “ገራዊ ምርጫ” የተካሄደው፡፡ ይህ ምርጫ ከመደረጉም በፊት ሆነ ከተደረገ በኋላ ከፍተኛ ውዝግብ ያስነሳ ከመሆኑም በላይ በተቃዋሚ ጎራ የተለፈው ይል ሜዳውን ሙሉ ለሙሉ ለገዥው ፓርቲ ትቶ ገዥው ፓርቲ ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠረው መንግት ተቋቋመ፡፡

ከሌሎች የምርጫ ጊዜዎች የ1987 ዓ.ም. ምርጫ የተለየ የሚያደርገው ለዚህ ምርጫ ምዕራባውያን ትኩረት ሰጥተው ተቃዋሚዎች በምርጫ ሊሳተ የሚችበትን መንገድ ለማመቻቸት ያደረጉት ከፍተኛ ጥረት ነበር፡፡ የአሜሪካ መንግት ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በየካቲት 1987 ዓ.. የፕሬዳንቱ የፀጥታ ጉዳዮች አማካሪ የነበሩት አንቶኒ ሌክ የመሩት ቡድን፣ ከገዥው ፓርቲና ከተለያዩ የተቃዋሚ ኃይሎች ጋር በኋይት ሃውስ ያደረጉቧቸው በርካታ ውይይቶች የጥረቱ ምሳሌ ሆኖ ይጠቀሳል። ለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ምዕራብውያኑ ትኩረት ሰጥተው በገዥው ፓርቲ ላይ ያደረጉት ግፊት አንዳንድ ተቃዋሚ ጎራ ውስጥ የነበሩ “የፖለቲካ ልሂቃን” የተሳሳተ የፖለቲካ ሥሌት በማድረግ፣ የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ በመድረሳቸውም ምዕራብውያኑ ከሚገባው በላይ በገዥው ፓርቲ ላይ ከፍተኛ ጫና አድርገው ገዥው ፓርቲ የፖለቲካ ምኅዳሩን ይበረግዳል ብለው ገመቱ። በዚህም የተነሳ በየነ ጴጥሮስ (ፕሮፌሰር) ይመሩት ከነበረው የፖለቲካ ድርጅት በስተቀር፣ ሁሉም በሚባል ሁኔታ ገዥው ፓርቲ የምርጫ ጊዜውን ካላራዘመና የምርጫ ቦርዱን ካልቀየረ በስተቀር በምርጫው አንገባም ሲሉ ደመደሙ። ፕሮፌሰር በየነም በተቃዋሚው ጎራ በተደረገባቸው ከፍተኛ ጫና ወደ ምርጫው ለመግባት ውሳያቸውን በመከለስ፣ በግንቦት 1987 ዓ.ም. ምርጫ እንደማይሳተፉ ገለጹ።

ይህ በተቃዋሚው ጎራ የተወሰደው የተሳሳተ ውሳኔ የፖለቲካ ምኅዳሩን ከማስፋት ይልቅ በማጥበቡ አገራችንን ከፍተኛ ዋጋ አስከፍሏል። ይህ ጸሐፊ በወቅቱ በዋሽንግተን ዲሲ ይተላለፍ የነበረው የኅብረት ሬዲዮ አዘጋጅና አቅራቢ ከነበሩት አንዱ ነበር። የዚህ ሬዲዮ ዝግጅት የፈጠረለትን አጋጣሚም ተጠቅሞ በተቃዋሚ ጎራ የነበረው የፖለቲካ ኃይል ወደ ምርጫው እንዲገባ ከፍተኛ ግፊት አድርጓል። ለኦነግ፣ ለኢዲኃቅ ለመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት፣ ለአማራጭ ኃይሎች፣ እንዲሁም በወቅቱ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር በአሜሪካ ለነበሩት ለአምባሳደር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ ቃለ መጠይቅ በማድረግ መንግሥትና ተቃዋሚዎች ስምምነት ፈጥረው ምርጫው ሁሉን አሳታፊ እንዲያደርግም በቃለ መጠይቆቹ ሞግቷል። ሆኖም በተቃዋሚዎች እምቢተኝነትና ያለ ምንም ስትራጂ በተወሰደ ርምጃ ተቃዋሚዎችለም መድረክ ላይ የነበራቸውን ተደማጭነት አ። ምዕራብውያኑም ተቃዋሚዎች ሰበብ ፈላጊ እንጂ የተፈጠረላቸውን አጋጣሚ ተጠቅመው በትግሉ የፖለቲካ ምዳሩን ለማስፋት ተግቶ ለመታገል የቆረ አይደም ሲሉ ደመደሙ።

ምንም እንኳን የተቃዋሚው ይል ሕዝቡ በ1987 ዓ.ም. ምርጫ ባለመሳተፍ ገዥው ፓርቲ መንግሥት የመሆ “ሕጋዊነት” (Legitimacy) እንዳይኖረው በምርጫው ላይ ማዕቀብ እንዲደረግ ቢሞክርም ሕዝቡ በምርጫው ተሳተፈ፡፡ ከዚያም በላይ በርካታ ግለሰቦች “በግል ተወዳዳሪነት” ገዥውን ፓርቲ ተቃውመው በምርጫው በመሳተፍ ገዥው ፓርቲ ብቻውን መንግሥትን እንዲቆጣጠርና መንግሥትም ምርጫው “ፍትዊና ነፃ” ነው እንዲል አደረጉት። የሚያሳዝነው የተቃዋሚው ኃይል፣ በደመነፍስ የሚንቀሳቀስ ሁኔታዎችን ለመምራት፣ የረጅምና የአጭር ጊዜ ዓላማና ግቡን ነድፎ የማይንቀሳቀስ፣ ለሚፈጠሩ ነገሮች ምላሽ በመስጠት የተጠመደ በመሆኑ፣ ትግሉን በቅጡ ሊመራ አልቻለም። ይህ ጸሐፊ ኢሕአፓ በሳንዲያጎ አዘጋጅቶት ለነበረው ስብሰባ “Lack of Strategic Planning, the Deficiency in the Ethiopian Opposition Camp” የሚል ሰፊ ሃተታ ያለው ጽፍ በማቅረብ ገና ከጅምሩ ተቃዋሚው የአጭርና የረጅም ጊዜ ላማና ግብ እንዲሁም የሚጓዝበትን መንገድ እንዲነድፍ የምክር ሳብ አቅርቦ ነበር። ሆኖም እስከ መጨረሻው ያነው ነገር ተቃዋሚው በደመነፍስ የሚንቀሳቀስ መሆኑን ነው። በዚህም ምክንያት ነው “አንጋፋ የነበሩት” እንደ ኢዲኃይነትና መድን የተባሉት ድርጅቶች ከኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ሊከስሙ የቻሉት።

በዚህ ጸሐፊ እምነት የተቃዋሚው ጎራ ትልቁ ችግር ከስህተቱ ለመማር ፈቃደኛ አለመሆኑ ነው። ከ1987 ዓ.ም. ምርጫ ምንም ዓይነት ትምህርት ያልወሰደው የተቃዋሚ ይል ለግንቦት 1992 ዓ.ም. ምርጫም የማይሳተፍ መሆኑን በአደባባይ አወጀ፡፡ በምርጫ ለመሳተፍ ያንገራግሩ የነበሩ በአገር ውስጥ የነበሩ ድርጅቶች ላይ የወከባ ዘመቻ ተጀመረ፡፡ ምርጫ ውስጥ መሳተፍ እንደ ክህደትም ተቆጠረ፡፡ አንዳንዶቻችን የምርጫው ሜዳ ለገዥው ፓርቲ መተው የለበትም ብለን በማመናችን በተለይም በግል እንወዳደራለን ብለው ዝግጅት ያደርጉ የነበሩ ሰዎችን በአንድ አጀንዳ ር በማስተባበር በየምርጫ ጣያው የሚኖረው ውድድር አንድ የኢሕአግ ተወዳዳሪ ከአንድ ተቃዋሚ ጋር ሊወዳደር የሚችልበትን መድረክ ለማዘጋጀትኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ አንጋፋ ሚና ካላቸው ሰዎችም ጋር ውይይት ተደረገ። ይህ ሁኔታ በውይይትና በጥናት ደረጃ ላይ በነበረበት ጊዜም፣ የኢትዮጵያና የኤርትራ ጦርነት በመጀመሩ ለተጀመረው ንድፈ ሐሳብ እንቅፋት ሆነ። በዚህ ውስብስብ ጊዜም ነበር የኢትዮጵያውያን ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኢዴፓ) የተባለ በአቶ ልደቱ አያሌው የተመራ ድርጅት ገና ብቅ ከማለቱ፣ በግንቦት 1992 ዓ.ም. ምርጫ እንደሚሳተፍ ያበሰረው፡፡ ይህ ለኢትዮጵያ ጥሩ ዜና ነበር፡፡ ኢዴፓን ተከትሎ ሌሎች በገር ውስጥ የነበሩ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅቶች በምርጫው ተሳተፉ በምርጫ 1992 ተቃዋሚው ጎራ ገዥውን ፓርቲ ምጥ አስያዘው፡፡

በምርጫ 1992 ተቃዋሚው ባደረገው የምርጫ ተሳትፎ ምክንያት፣ በራል ምክር ቤትም ውስጥ ሆነ በአንዳንድ የከተማና ክልል ምክር ቤቶች መቀመጫ ለማሸነፍ በመቻሉ በየምክር ቤቶቹ ስብሰባዎች ገዥውን ፓርቲ በመሞገትና የፖሊሲዎቹን ድክመትና አደገኛነት በማጋለጥ ለፖለቲካው ደት ያበረከቱት አስተዋጽኦ የሚናቅ አልነበረም። ተቃዋሚው ይህንን ያገኘውን ድል በማስፋት የኅብረተሰቡን ልብ በማሸነፍ ገዥውን ፓርቲ በራሱ የፖለቲካ ቁማር ከጨዋታ ውጪ ከማድረግ ይልቅ፣ እርስ በርሱ በመጠላለፍና አንዱ ሌላውን በመተንኮስ ጊዜና ኃይል ማባከኑን ቀጠለ። “ተባበሩ ወይ ተሰባበሩ” የሚለው የሕዝብ ግፊት በማየሉም ነው በነሐሴ 1995 ዓ.ም. በአሜሪካ  ሜሪላንድ ግዛት ውስጥ የኢትዮጵያ ሞክራሲያዊ ይሎች ብረት (ብረት) የተባለው ድርጅት የተመረተው፡፡ ብረት ግን ወደ ታሰበለት ግብ ሳይደርስ ገና ከጅምሩ በውስጡ የነበሩት ድርጅቶች መንጠባጠብ ስለጀመሩ ጉልበት አጣ፡፡ ያው ፖለቲካው ለመደው መጠላለፍ ቀጠለ፡፡ የዚ መጠላለፍ ምክንያት ነው በዳር 1997 ዓ.ም. ቅንጅት ለአንድነትና ለሞክራሲ (ቅንጅት) የተባለውን ድርጅት የፈጠረው፡፡

ቅንጅት ትግሉ ከኢሕአግ ጋር ከብረት ጋር ነበር፡፡ በሁለቱ መካከል የነበረው ሹክቻ ቀርቶ ትግላቸውን በኢሕአግ ላይ እንዲያነጣጥሩ ብዙ ግፊት በሚያዚያ 1997 ዓ.ም. ምርጫው አንድ ወር ብቻ ሲቀረው በቅንጅትና በብረት መካከል ትብብር ተፈጠረ፡፡ ይህ የሚያሳየው ተቃዋሚው በደመነፍስ የሚንቀሳቀስና ገራዊ ራዕዩ የደከመ እንደነበር ነው፡፡ የግንቦት 2002 ዓ.ም. ሆነ የግንቦት 2007 ዓ.ም. በኢትዮጵያ የተደረጉት ምርጫዎች የሚያሳዩት በተቃዋሚው ጎራ መካከል ኢሕአግን በጠላትነት ከመፈረጅ ባለፈ ምንም ዓይነት የአጭርና የረጅም ጊዜ የጋራ አጀንዳ ነድፎ የማይንቀሳቀስ መሆኑን ነው። ምንም እንኳን መድረክ የተባለ ስብስብ ቢኖርም በመድረክ ውስጥ ያሉ ብሔር ተኮር ድርጅቶች የየብሔራቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ ከመቆም በቀር ምንም ዓይነት ብሔራዊ የጋራ አጀንዳ ነድፈው የማይንቀሳቀሱ ናቸው፡፡ ለዚህም ነው በዳር 2007 ዓ.ም. የተነሳው አመ ያለ ምንም ፖለቲካ ድርጅት መሪነት በወጣቱ ግብታዊ ስሜት ሊቀሰቀስ የቻለው፡፡

ይህ ግብታዊ አመ በገዥው ፓርቲ ውስጥ ለውስጥ ለለውጥ ሲንቀሳቀሱ ለነበሩ ይሎች ጉልበት በመፍጠሩ ገዥው ፓርቲ ከውስጡ ተገዝግዞ ዛሬ ያለንበት ደረጃ ላይ ደርሰናል። ዛሬ ደግሞ ለውጡን የሚመራው ይል በገራችን የሞክራሲያዊ ልተ ርዓት እንዲገነባ ሕዝቡ ወዶና ፈቅዶ የመረጠው የፖለቲካ ይል የመንግሥትን ይል እንዲቆጣጠር ተግቶ በሚራበት ወቅት የዚህ ደት እንቅፋት በመሆን ላይ ያሉት በተቃዋሚ ጎራ ውስጥ የተልፉ ይሎች መሆናቸው አስገራሚ ነው። ሌላው ቀርቶ ለመጀመርያ ጊዜ በታሪካችን ሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶች በምርጫ ፖለቲካ ውስጥ እንዲሳተፉ ፈ ቀዳጅ ሆኖ ድፍረት የሰጠው ኢዴፓ እንኳን “የምርጫው ጊዜ ይራዘም” ሲል መስማቱ አስገራሚ ነው። ሌላው አስገራሚ ነገር በተቃዋሚ ጎራ የተለፈው ይል አቅሙን ሰብሰብ አድርጎ ለገር ይጠቅማል የሚለውን የፖለቲካ የኢኮኖሚና የማበራዊ ኑሮ ቅድ ነድፎ ለግንቦት ለመጪው 2012 ምርጫ ራሱን ለማዘጋጀት ከመትጋት ይልቅ ምርጫው ውስጥ ላለመሳተፍ “ሰበብ” መደርደሩ ነው፡፡ በገራችን ውስጥ ከ130 በላይ የፖለቲካ ድርጅቶች መኖር ራሱ በተቃዋሚ ጎራ የተለፈው ይል መሪ ያጣ የፖለቲካ ይል ለመሆኑ ምስክር ነው፡፡ በመቶ የሚቆጠሩ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶችን አስተባብሮ ቁጥራቸውን መቀነስ ያልቻለ የፖለቲካ ይል ስንት የተወሳሰ ችግር ያለባትን ገር በመሪነት ተረክቦ ሊያስተዳድር ይችላል ብሎ መገመት ይቻላል ወይ?

የምርጫ ቦርድ በተወካዮች ምክር ቤት ያስፀደቀውን የምርጫ ሕግ ተከትሎ ከተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች የምንሰማው አቤቱታ ሰበብ እንጂ፣ ምርጫ ውስጥ እንዳይሳተፉ የሚያግድ አይደለም። ጊዜ ሰጥቶ ተግቶ በመሥራት ፖሊሲ ነድፎ አሥር የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን ማሳመን የማይችል የፖለቲካ ድርጅት እንዴት ነው በሚሊዮን የሚቆጠር መራጭ ሊያሳምን የሚችለው? ይህንን ተከትሎ የምንሰማቸው አቤቱታዎች ትንትና ላይ ቆመው የወደፊቱን ማየት በማይፈልጉ የፖለቲካ ይሎች ነው፡፡ 2012 ዓ.ም.ኢትዮጵያ ውስጥ ብሔራዊ ምርጫ እንደሚካሄድ ለማንም ሚስጥር አይደለም፡፡ ይህ ከአምስት መታት በፊት ጀምሮ ይታወቅ ነበር፡፡ በገር ውስጥም ያሉ ይሁኑ ከገር ውጪ የነበሩ የፖለቲካ ድርጅቶች በአሁኑ የለውጥ የፖለቲካ ደት ውስጥ ለመሳተፍ የወሰኑት በ1987 ዓ.ም. ደቀውን ሕገ መንግት ተቀብለው  ነው፡፡ ሕገ መንግቱም በየአምስት ዓመቱ ብሔራዊ ምርጫ እንደሚኖር ደንግጓል፡፡ ከዛም አልፎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ምርጫው እንደሚካሄድና ተቃዋሚ/ተፎካሪ ድርጅቶች መር ግብራቸውን በመንደፍ ለሥልጣን እንዲወዳደሩ ሥልጣን መያዝ የሚቻለውም በሕዝብ ምርጫ ብቻ መሆኑን ደግመው ደጋግመው መክረዋል፡፡ የዘንድሮ ምርጫ መካሄድ ለማንም አዲስ ዜና ሊሆን አይገባውም፡፡

አሳዛኙ ነገር በተደጋጋሚ በኢትዮጵያ የምርጫ ደት ውስጥ የታዘብነው ለምርጫ ውድድር ከመዘጋጀት ይልቅ በሙሾ ፖለቲካ ጊዜ ማባከንን የሕዝብን ተስፋ ማጨለምና የራስን ድክመት ለመሸፈን ስበብ በማብዛት የተገኙ ድሎችን ማበላሸት ነው፡፡ ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ ሁለት ዓይነት የፖለቲካ ይሎች አሉ፡፡ አንደኛው ይል ትንት ላይ ቆሞ የወደፊቱን ለማየት ያልፈቀደና በሙሾ ፖለቲካ የፖለቲካ ሕይወቱን ማርዘም የሚችል የሚመስለው እንዲሁም በአቤቱታ ሊፈጠር በሚችል ትርምስ ሥልጣን በአቋራጭ ይዛለሁ ብሎ በቅዠት ውስጥ ያለ ነው፡፡ ሌላው የፖለቲካ ይል ደግሞ ካለፈው ተምሮ ዛሬን ተጠቅሞ ነገ ሕዝቡ የተሻለ ሕይወት እንዲኖረው ገራችን ነገ የተሻለች ገር እንድትሆን ተግቶ የሚራ ነው፡፡ ብዙዎቹ የብሔር ድርጅቶች መሪዎቻቸው ትንት ላይ ቆመው የሚያላዝኑ በመሆናቸው በምርጫው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊኖራቸው ይችላል። ይህን አሉታዊ ተፅዕኖ ግን አቅጣጫ ሊያስቀየር የሚችለው በተለይ የድርጅቱ አባላት በአጠቃላይ ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትናንት ላይ ቆመው በቀሩትና በወደፊት መፃኢ ዕድሉ ላይ ባተኮሩ ድርጅቶች መካከል ያለውን ልዩነት በመረዳት፣ የወደፊት ዕድሉን ብሩህ የሚያደርጉ የፖለቲካ ድርጅቶችን በመምረጥና የፖለቲካ ነጋዴዎችን አጨበርባሪነት እምቢ በማለት ነው።

ስለትናንትና እያጋነኑ በማውራት በሕዝቡ ውስጥ ጥላቻን በመዝራት ጊዜና ኃይል የሚያባክኑ የፖለቲካ ድርጅቶች ለሕዝብ የሚጠቅም ምንም ዓይነት መርሐ ግብር የላቸውም፡፡ ሕዝቡም ይህንን በቅጡ ሊረዳ ይችላል። ዛሬ ላይ ሆነን እንደ ኦፌኮ መሪዎች የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ ከጥቁር አሜሪካውያን ታሪክ ጋር በሚያነፃፅር የሐሰት ትርክት ሕዝብ በመቀስቀስና ስለኢሕአዴግ ኢፍትሐዊነት በማውራት፣ ምርጫ ላይ ተሳትፎ ማሸነፍ የሚቻል አይመስለኝም። ጥያቄው እነዚህና መሰል ድርጅቶች የኢኮኖሚ የማኅበራዊ መርሐ ፣ እንዲሁም የፖለቲካ ፍልስፍናቸው ምንድነው የሚል ነው። እንደ ጃዋር መሐመድ ያሉ ጽንፈኞች በምርጫ ከተሸነፉ ሁከት ለመፍጠር እየተዘጋጁ መሆናቸው ምልክቶቹ እየታዩ ነው። ጃዋር ለኒውዮርክ ታይምስ በሰጠው ቃለ ምልልስ ምርጫው ፍትሐዊና ነፃ መሆኑን የሚመዝነው በእሱ መመረጥና አለመመረጥ መሆኑን መግለጹ አስቂኝ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ እንጭጭ መሆኑን ፍንትው አድርጎ ያሳየበት ነው። ይኸው ግለሰብ በቅርቡ የምርጫ ቦርድን የሚያምነው 50 በመቶ መሆኑን ሰምተናል፡፡ የምርጫ ቦርድን ተዓማኒነትም ሆነ ምርጫው ነፃና ፍትሐዊ መሆኑን የሚመዘንበትን መሥፈርቱን የሚነግሩን እንደ ጃዋር ዓይነት ሰዎች ዓላማቸው አንድ ነው፡፡ ይህም እኛ ካላሸነፍን ምርጫው ነፃ አልነበረም ለማለት ነው። እነዚህ ኃይሎች ግን ቀጣዩን ምርጫ ሊያሸንፉ የሚችሉበት መርሐ ግብራቸውና አማራጭ ሐሳባቸው ምን እንደሆነ እንኳን አይነግሩንም።

በዚህ ጸሐፊ እምነት እነዚህ የፖለቲካ ኃይሎች ሙሾ ከማውረድ ባለፈ አቅም የላቸውም። ኦፌኮም ሆነ በመድረክ ሥር የተሰባሰቡት የፖለቲካ ድርጅቶች ለኢትዮጵያ ሕዝብ አማራጭ ንፈ ሐሳብ አቅርበው የሚያውቁት መቼ ነው? እስከ ዛሬ የነበረው “ፖለቲካ” “ኢሕአዴግን በመኮነን” ላይ ብቻ ያተኮረ ነው፡፡ ዛሬ ትንት አይደለም፡፡ ኢሕአዴግን በመኮነን ብቻ መደቅ አይቻልም፡፡ “የራስን የድቅ” ርቶ ማሳየት ያስፈልጋል፡፡ በሚቀጥለው ምርጫ ኢሕአዴግ የሚባል የፖለቲካ ድርጅት አይኖርም፡፡ ስለዚህ ኢሕአግ አሳሪ ነው፡፡ ገራፊ ነው ገዳይ ነው የሚል አጀንዳ ቦታ አይኖረም፡፡ በዚህ ጸሐፊ ግምት ዛሬ ላይ ሆነው የነገን ተስፋ በመሰነቅ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ሁለት የፖለቲካ ድርጅቶች ናቸው፡፡ ከእነዚህ የፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥ እጅግ የሚደነቅ ተግባር እያከናወነ ያለው ኢዜማ የተባለው የፖለቲካ ድርጅት ነው፡፡ በኢዜማ ውስጥ የተሰባሰቡ የፖለቲካ ይሎች ብቃታቸውንና የድርጅት ርዓታቸውን (ዲፕሊን) በተግባር አሳይተዋል፡፡

ምርጫው አይቀሬ መሆኑን በመረዳት ተመሳሳይ አመለካከት ያላቸው የፖለቲካ ድርጅቶች አሰባስቦ አንድ ድርጅት ያዋቀረው ይህ ድርጅት ስለትንትና ስሞታ በማቅረብ ጊዜውን ሲያባክንም ሆነ በትንትና ታሪክ ላይ “የፖለቲካ ልፍያ” ውስጥ ሲንቦጫረቅ አናየውም፡፡ ይህ ጸሐፍ ኢዜማ ውስጥ ካሉ ከማናቸውም ጋር ግላዊ ግንኙነት የለውም። በአንድ ወቅት ብቻ ከብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) እና ሳሙኤል ዮሐንስ (ዶ/ር) ጋር በአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ላይ ለውይይት ከመቅረብና የተወሰነ ውይይት በግል ከማድረግ ውጪ፣ ምንም ዓይነት የጠበቀ ግንኙነት የለውም። ይህ ጽሑፍም ዓላማው ኢዜማንም ሆነ ሌላውን የፖለቲካ ድርጅት ምረጡ ወይም አትምረጡ ለማለት የተዘጋጀ አይደለም። የጽሑፉ ዓላማ አገር ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች የሚፈጥሩትን ሰበብ አቁመው፣ ጊዜያቸውን ተጠቅመው ለሕዝብ አማራጭ እንዲያቀርቡ ለማሳሰብ ነው።

ከኢዜማ አካሄድ ብዙ መማር ይቻላል፡፡ ኢዜማ ለበርካታ የምርጫ ጣቢያዎች ዕጩዎቹን አዘጋጅቷል፡፡ ለአይቀሬው ምርጫ መርሐ ግብሩን ነድፎ አባላቶቹ እንዲወያዩበት አድርጓል፡፡ “የእናቴ መቀነት አደናቀፈኝ” ዓይነት ሰበብ ከኢዜማ አይሰማም። ኢዜማ ዛሬ ላይ ሆኖ ለነገ ለአገር ያለውን ራዕይ በወረቀት አስፍሮ የምርጫ ዘመቻ በማድረግ ላይ ያለ የፖለቲካ ድርጅት ነው። አገራችን ዛሬ የምትፈልገው እንዲህ ዓይነት የፖለቲካ ኃይል ነው። ለኢዜማ ተመጣጣኝ ተፎካካሪ የሚሆነው በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) መሪነት የተመሠረተው የብልጽግና ፓርቲ ነው። የብልጽግና ፓርቲ ከኢሕአዴግ የወረሳቸው ድርጅታዊ መዋቅሮችና ሀብት ስላለው፣ በአገር አቀፍ ደረጃም ሆነ በክልሎች ደረጃ የመወዳደር ብቃት አለው። በዚህ ጸሐፊ ግምት ብልጽግና ፓርቲ እንደ ኢዜማ በፖለቲካም ሆነ በኢኮኖሚ ጉዳይ በእውቀት የተካኑ ሰዎች የሉትም። ብዙዎች ብልጽግና ፓርቲ ውስጥ ያሉ የአመራር አካላት አቅማቸው ውስን ነው።

ሆኖም እንደ ዶ/ር ዓብይ ያሉ ብቃት ያላቸው መሪዎች ሌሎች ብቃት ያላቸውን ልሂቃን ወደ ብልጽግና ፓርቲ ሊጎትቱ ይችላሉ። ትልቁ ነገር ብልጽግና ፓርቲ በትናንትና ላይ ቆሞ ሙሾ እያወረደ አይደለም፡፡ ለሕዝብ የነገ ራዕዩን እያቀረበ ያለና ለሕዝብ ተስፋ የሰጠ የፖለቲካ ድርጅት ነው። ቀጣዩ ምርጫ ስለፍትሕ፣ ዴሞክራሲ፣ የፕረስ ነፃነት፣ ወዘተ ዓይነት አጀንዳዎች ብዙውን የክርክር ቦታ የሚወስዱ ሳይሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚደረግው የሥራ ፈጠራ፣ የቤት ዕጦት፣ የሕክምና ተቋማት ማስፋፍያ፣ የትምህርት ፍኖተ ካርታና ትምህርት ቤቶችን ማሻሻያ፣ በአገሪቱ ውስጥ የብሔራዊ ከበርቴውን ሊያሳድግ የሚችል የቀረጥ ሕግ፣ ሕፃናትና አዛውንት ተኮር መርሐ ግብር፣ የፍትሕ ሥርዓት ማሻሻያ፣ እንዲሁም በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን መሠረታዊ ልማቶችን ማሻሻያ፣ ተገቢ የሆነ የሞኒተሪና የፊስካል ፖሊሲውን ቀርፆና የምርት አቅርቦት አሻሽሎ የኑሮ ውድነትን መቀነስ፣ በተለይም ደግሞ የሕዝብ ቁጥርን ጭማሪ ፍጥነት የሚገድብ ዕቅድን የተመለከቱ ክርክሮች ትኩረት የሚያገኙበት ይሆናሉ የሚል ግምትም አለ። ከምንም በላይ ቀጣዩ ምርጫ ትናንት ላይ ቆመው ሙሾ በሚያወርዱና ዛሬ ላይ ሆነው ስለወደፊቱ የአገራችን ዕድገት ራዕይ ባላቸው ኃይሎች እንደሚሆን በርካታ ምልክቶች እየታዩ ነው። ስለዚህ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ጎራዴያቸውን ሳይሆን አዕምሮአቸውን በመሳል ለውድድር ይዘጋጁ እላለሁ።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ።

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ኩባንያ አስተዳደር ለኢትዮጵያ ባንኮች ውጤታማነት

የጠቅላላ ጉባኤ፣ የጥቆማና ምርጫ ኮሚቴ፣ የተቆጣጣሪ ቦርድ፣ የዳይሬክተሮች ቦርድና...

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...