Sunday, March 26, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ ለአንድ ባለሀብት ስልክ ደወሉ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚስታቸው ጋር ቁርስ እየበሉ ነው]

  • ብላ እንጂ?
  • በቃኝ እባክሽ፡፡
  • መቼ በላኸው?
  • ዘግቶኛል፡፡
  • አልጣፈጠህም እንዴ?
  • እሱስ አሪፍ ነበር፡፡
  • ታዲያ ለምን አትበላም?
  • አልወርድልህ አለኝ፡፡
  • ምን ሆነሃል?
  • ምን አልሆንኩም ብለሽ ነው?
  • ምነው?
  • የአገራችን ጉዳይ ነዋ፡፡
  • የሚያሳስብ ነገር ተፈጠረ እንዴ?
  • አገራችን አሳሳቢ ከሆነች እኮ ሰነባበተች፡፡
  • አንተ ደግሞ የማያስጨንቅ ነገር ያስጨንቅሃል፡፡
  • እንዴት?
  • አሁን ስንት የሚያስጨንቅ ነገር እያለ ስለአገር ትጨነቃለህ?
  • ከአገር በላይ ምን የሚያስጨንቅ ነገር አለ?
  • ስለራስህ ነዋ መጨነቅ ያለብህ፡፡
  • እ…
  • ተመልከተን እስቲ?
  • ማንን ነው የምመለከተው?
  • እኛን ነዋ፡፡
  • ምን ሆንን?
  • አንተ ምን አለብህ?
  • እንዴት?
  • እኔ እኮ ሁሉንም ነገር ሳጣራ ነበር፡፡
  • ምንድነው የምታጣሪው?
  • ስለበፊቶቹ ባለሥልጣናት ሕይወት ነዋ፡፡
  • ማለት?
  • ለምሳሌ በጥምቀት የሚያደርጉትን ልንገርህ፡፡
  • ምን ያደርጋሉ?
  • እንደ ጥምቀት የሚወዱት በዓል አልነበረም አሉ፡፡
  • ለምን?
  • ብዙ ነገር የሚወራወሩበት በዓል ነዋ፡፡
  • አልገባኝም?
  • መቼም በጥምቀት ሎሚ እንደሚወረወር ታውቃለህ?
  • እንዴት ማለት?
  • በቃ ከባለሀብቶች ጋር የሚተጫጩበት በዓል ነው፡፡
  • እ…
  • አያንዳንዱ ባለሀብት መኪና ይወረውራል አሉ፡፡
  • ለማን?
  • ለክቡር ሚኒስትሩ ነዋ፡፡
  • እሺ፡፡
  • ሌላው ደግሞ ቪላ አሉ፡፡
  • እ…
  • ሙሉ የቤት ዕቃ የሚወረውርም አለ አሉ፡፡
  • ወይ ጣጣ፡፡
  • እሱ ብቻ መሰለህ እንዴ?
  • ሌላ ደግሞ ምን አለ?
  • የባንክ ሼር በለው ኧረ ስንቱን ልጥራው?
  • እ…
  • ባለሥልጣናቱም ግን በተራቸው ይወረውራሉ፡፡
  • ምንድነው የሚወረውሩት?
  • መሬት!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከተቃዋሚ መሪ ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው]

  • ምንድነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ምኑ?
  • አገሪቱ ወዴት እያመራች ነው?
  • ወደ ብልፅግና ነዋ፡፡
  • ፅድቁ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ አሉ፡፡
  • ተረት ትችላለህ እንዴ?
  • ምን ለማለት ፈልገው ነው?
  • ማለቴ ያው ዳያስፖራ ነህ ብዬ ነው፡፡
  • ወድጄ አይደለም እኮ ዳያስፖራ የሆንኩት፡፡
  • ደግሞ ማን አስገደደህ?
  • አላታግል ሲሉኝ እኮ ነው ከአገር የሸሸሁት፡፡
  • ታዲያ ምን አጠፉ?
  • ምን አሉኝ?
  • ምንም፡፡
  • ልታባርሩን አስባችኋል እንዴ?
  • መቼ ይቀራል?
  • እ…
  • ምነው?
  • እኛ እኮ መንግሥትን አምነን ነው የመጣነው፡፡
  • መንግሥትም አምኖ ነበር የጠራችሁ፡፡
  • ምን አምኖ?
  • አገሪቱ ሰላም ትሆናለች ብሎ ነዋ፡፡
  • እ…
  • አተርፍ ባይ አጉዳይ አሉ፡፡
  • ማን ነው እሱ?
  • መንግሥት ነዋ፡፡
  • እንዴት?
  • ይኸው የአገሪቱ ሰላም በየጊዜ እየደፈረሰ ነዋ፡፡
  • እኛ እጃችን የለበትም፡፡
  • እሱን ስትጠየቅ ታወራለህ፡፡
  • ማን ነው የሚጠይቀኝ?
  • ምን አስቸኮለህ?
  • እያስፈራሩኝ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ዓላማህ ለመሆኑ ምንድነው?
  • ሕዝቤን ማገልገል ነዋ፡፡
  • ማጋደል ነው ያልከኝ?
  • ተው እንጂ ክቡር ሚኒስትር?
  • ትንሽ ግን አያሳዝናችሁም፡፡
  • ማን ነው የሚያሳዝነን?
  • ሕዝቡ ነዋ፡፡
  • ትግል፣ ትግል ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ይኼ ሕዝብ መቼ ይሆን የሚያልፍለት?
  • አሁን በእኛ ያልፍለታል፡፡
  • በእናንተማ ሕይወቱ እያለፈ ነው፡፡
  • ምን አሉኝ?
  • ለማንኛውም ደርሰንበታል፡፡
  • ምኑን?
  • ዓላማህን፡፡
  • ምንድነው?
  • ማተራመስ!

[ለክቡር ሚኒስትሩ የቀድሞ ሚኒስትር ስልክ ደወሉላቸው]

  • ምን አለ ብታምኑ ክቡር ሚኒስትር?
  • ምኑን?
  • ሁሉም ነገር እያፈሰሰባችሁ እኮ ነው፡፡
  • አልገባኝም?
  • ፖለቲካውን ስትሉት ኢኮኖሚው እያለ አስቸገራችኋ?
  • እ…
  • ለምን አትለቁልንም?
  • ለእናንተ?
  • የውጭዎቹም መቼ ቻሉት?
  • ምን?
  • የእነሱን ምክር መስማት እንደማያዋጣ ተናግረን ነበር፡፡
  • የምነግርህ ነገር የእነሱ ምክር ቢያንስ ከእናንተ ይሻላል፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር የሁሉም ነገር መፍቻ በእጃችን ነው፡፡
  • እናንተ ማጥፊያ እንጂ መፍቻ የላችሁም፡፡
  • እ…
  • ተስፋ እንዴት አትቆርጡም?
  • እኛማ መመለሻ ትኬታችንን ነው መቁረጥ የምንፈልገው፡፡
  • የት ነው የምትመለሱት?
  • አራት ኪሎ፡፡
  • ወደዚህ ከተመለሳችሁም የምትመለሱት አንድ ቦታ ነው፡፡
  • የት?
  • ቂሊንጦ፡፡
  • እንግዲያው እንቀጥላለን፡፡
  • ምኑን?
  • ትግላችንን ነዋ፡፡
  • ትግል እኮ ድሮ ቀረ፡፡
  • እንዴት?
  • በዚህ ዘመን ምርጫ ነው ያለው፡፡
  • እ…
  • እናንተ ደግሞ ተመራጭ አለመሆናችሁን መቼም ታውቁታላችሁ?
  • ክቡር ሚኒስትር እኛ ተመራጭም ተደማጭም ነን፡፡
  • ደፍጣጭ ነን ብትል ነው የሚያምርብህ፡፡
  • ሥልጣን የያዝነው በምርጫ መስሎኝ?
  • እኔ ለዚህ አይደል እንዴ ደፍጣጮች ናችሁ የምልህ?
  • ክቡር ሚኒስትር እርስዎንም ለዚህ ያበቃንዎት እኛ መሆናችንን አይርሱት፡፡
  • ወዳችሁ ሳይሆን ተገዳችሁ ነው እባክህ?
  • እ…
  • ለማንኛውም አደብ ብትገዙ ይሻላችኋል፡፡
  • እናንተም አገሩን በሥርዓቱ ብታስተዳድሩት ይሻላችኋል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እናንተ እያላችሁ እንዴት አድርገን?
  • ታዲያ አንድ ላይ እናስተዳድረዋ?
  • እሱ የማይታሰብ ነው፡፡
  • በቃ?
  • አዎ በቃ፡፡
  • እንግዲያው ተከታታይ ድግሶች አዘጋጅተንላችኋል፡፡
  • የምን ድግስ?
  • የብጥብጥ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ለአንድ ባለሀብት ስልክ ደወሉ]

  • እንኳን አደረሰዎት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለምኑ?
  • ለጥምቀት ነዋ፡፡
  • በደረቁ ምን ያደርጋል ብለህ ነው?
  • በምን ላርጥብልዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • ለበፊቶቹ ሚኒስትሮች በምን ነበር የምታረጥብላቸው?
  • እ…
  • የማላውቅ መሰለህ እንዴ?
  • ምኑን ክቡር ሚኒስትር?
  • ለበፊቶቹ ምን ታደርግ እንደነበር ነዋ፡፡
  • ምን እያሉኝ ነው?
  • አሁን ምነው በደረቁ እያልኩህ ነዋ፡፡
  • አልታወቀም ብዬ ነው፡፡
  • ምኑ?
  • መቀመጫችሁ ነዋ፡፡
  • ከአሁን በኋላ ማን ይነቀንቀናል?
  • ክቡር ሚኒስትር ከየአቅጣጫው እየተወዘወዛችሁ እኮ ነው፡፡
  • እ…
  • ባይሆን ቀልጣፋ ከሆኑ ያቀላጥፉኝ፡፡
  • ምን?
  • አንድ አሪፍ ፕሮጀክት ነበረኝ፡፡
  • ታዲያ ምን ገጠመህ?
  • ፕሮጀክቱን ለመተግበር ዋነኛ እንቅፋት የሆነብኝ ነገር አለ፡፡
  • ምንድነው?
  • መሬት፡፡
  • እ…
  • በቃ እሱን ከቀረፉልኝ የፈለጉትን ነገር እወረውርልዎታለሁ፡፡
  • እውነት?
  • ምን ጥያቄ አለው፡፡
  • እንግዲያው ወርውርልኝ፡፡
  • ምን?
  • ቪላ!                                                                                         

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

በወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የተሰበሰበው ከፍተኛ ሀብት ጥቅም ላይ እየዋለ አይደለም ተባለ

በኢትዮጵያ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የተሰበሰበው የተቀማጭ ገንዘብ መጠን...

መንበሩ ካለመወረሱ በስተቀር መፈንቅለ ሲኖዶስ መደረጉን ቤተ ክህነት አስታወቀ

ቅዱስ ሲኖዶስ ከነገ ጀምሮ ውይይት እንደሚጀምር ተነገረ ‹‹እኛ ወታደርም ሆነ...

ወ/ሮ መሰንበት ሸንቁጤ የአዲስ አበባን ንግድና ዘርፍ ምክር ቤትን በፕሬዚደንትነት ለመምራት በተደረገው ምርጫ አሸነፉ

የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤትን በፕሬዚደንትነት ለመምራት፣...

ግራ አጋቢው የኤሌክትሪክ መኪና ጉዳይ

በያዝነው ዓመት መጀመሪያ በወርኃ ጥቅምት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 39...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...

ብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይፋ ሊያደርግ ነው

የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት የሚረዳ ሪፎርም ማጠናቀቁን የገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...