Friday, June 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
እኔ የምለዉየዓብይ አህመድ ‹‹መደመር››

የዓብይ አህመድ ‹‹መደመር››

ቀን:

ሊንዳ ዮሐንስ

‹‹መደመር›› የተሰኘውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድን መጽፍ የገዛሁት በኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ በሥልጣን ላይ ባለ መሪ ለኢትዮጵያ ድገት መመያ እንዲሆን የተጻፈውን ፍ ባላነ፣ ራሴን ኢትዮጵዊ ብዬ ለመጥራት አ እንደማይኖረኝ ከራሴ ጋር ካደረኩት ሙግት በኋላ ነበር፡፡ የተወሰኑ ገጾችን ካነበብኩ በኋላ ግን ‹‹ማንበብ አለብኝ›› የሚለው ይህ ስሜት ማንበብ ወደ መፈለግና መጓጓት ተለወጠ፡፡ 

መደመር ረታዊ ሳብ፣ ማኅበራዊና ቁሳዊ ሀብታችንን በመደመር ወደ ዎንታዊ ለውጥ አቋራጭ ስለመውሰድ ነው፡፡ ተከፋፍለን ከምናስገኘው ውጤት ይልቅ በአንድነት ውስጥ እጥፍ ድርብ ውጤት እንዳለ ይሰብካል፡፡ እንደ ግለሰቦች፣ እንደ ንግድ ተቋማት፣ እንደ መንግሥታት፣ እንደ አገሮች፣ እንደ የዓለም ክልሎች እንዲሁም አንዳችን ከሌላው ጋር እንደመራለን፡፡ እንደ ጸሐፊው አባባል የድህነት መንስዔ የመደመር አለመኖር ነው፡፡

መደመር የደሃ ሕዝቦች አገር ሆነችው ኢትዮጵያ ለም የደረሰበት ላይ ለመድረስ ዕድል እንዲኖራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ የሚያሰሙት የማንቂያ ደውል ነው፡፡ በምሳሌ ብናየው የኢትዮጵያ የቡና ላኪ ነጋዴዎች ለገበያ መወዳደራቸው እንዳለ ሆኖ፣ የጋራ የሆኑ ግቦችን ለማሳካት ገበሬዎችን በጋራ በመደገፍ ወይም የጋራ ጎተራን የመገንባት ሥራዎች ላይ በመሳተፍ መተባበርን ይመስላል፡፡ ወይም ደግሞ በአንድ ቤት ውስጥ የሚተባበሩ ሆኖም የግል ችሎታቸውን ለማውጣት የሚወዳደሩ የቤተሰብ አባላትን፡፡

እንደ ብራዊ ዕሳቤ አፍሪካውያ ሁሉ ባህሪ ነው ተብሎ ከሚታሰበው ‹‹ኡቡንቱ›› ከሚባለው የደቡብ አፍሪካው ማበረሰባዊና አብሮነት ሳቤ ይልቅ፣ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የተመቸ ነው፡፡ ወይም ደግሞ ‹‹ኡጃማ›› ሚባለው በስዋሂሊ ተመሳሳይ ፍቺ ካለው የታዛኒያው ጁሊየስ ሬሬ ለአገሪቱ ሶሻሊስት ዕቅዳቸውን የገለጹበት በውስጡ የአንድ ፓርቲ ሥርዓት፣ ኢንዱስትሪዎችን ብራዊ ማድረግና ግብርና በተደራጀ የደቦ ርዓት ማካሄድን ከሚያካትተውም ዕሳቤ እን፡፡

መደመር በሰው ልጆች ሁሉ ውስጥ ያለው የውድድርና የመተባበር ባህሪ በፍፁም ሚዛን ታርቀው የሚሄዱበት ዕሳቤ ነው፡፡ መወዳደርና መተባበር፣ ሰዎች የሉዕነት ስሜት እንዲሰማቸው የየራሳቸውን ሚና የሚጫወቱና አንዱ በአንዱ የማይተካ የተፈጥሮ ሕግጋት ናቸው፡፡ ለዚህም ነው ሰዎች ማኅበራዊ ግንኙነቶችን የሚያደርጉት፣ ለመተባበርና ለመወዳደር። አንድ ሰው ከሌሎች ጋር የሚያደርገው ግንኙነት ከመጠን ያለፈ የመወዳደር ስሜት ካለው፣ አንዳቸው ከግንኙነቱ ራሳቸውን ማግለላቸው አይቀርም፡፡ ምክንያቱም ሉዕነት ከማግኘት ይልቅ የባዶነት ስሜትን ስለሚያበዛ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ግንኙነቱ ከመጠን በላይ ትብብር የበዛበት ከሆነ፣ የፈጠራ ራን የማሳለጥ ብቃት እንዲዳከም ስለሚያደርግ፣ ሰዎች ውድድር ባለመኖሩ ምክንያት ተነሳሽነታቸው ስለሚጠፋ ከግንኙነቱ ይሸሻሉ፡፡ ሰዎች ከኅብረት ሲሸሹ ደግሞ ብቸኝነት ይፈጠራል፡፡

የመደመር ዕሳቤ ጥልቀት፣ ስፋትና ልዩነት ያለው በመሆኑ ለአገሪቱ ፖለቲካዊና ሥነ ምጣኔያዊ መመርያዎች መሠረት ሆኖ ማገልገልም አልፎ፣ ከታሪካችን ሊወረሱ የሚገባቸውን ነገሮች የያዘና አሁን ላለውም ወደ ፊት ለሚመጣውም ትውልድ ሊያገለግል የሚችል ኢትዮጵያዊ ፍልስፍና ነው፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ መደመር ንድፈ ሐሳብ ብቻ ነው። ተፈጻሚነቱንም ለመገምገም ይከብዳል፡፡ ሆኖም የመደመር ታላላቅ ተስፋዎች ፍሬ ያፈሩ ዘንድ በትዕግሥት፣ ሐሳ ሰፊ በመሆን፣ ጠቃሚ የሆኑ አስተያየቶችንሶችን በመስጠትና ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ማዳበር ይኖርብናል፡፡

በመደመር ውስጥ

አሁን ስለጠቅላይ ሚኒስትራችን በሕዝ ዘንድ ያለው አስተያየት የተለያየ በመሆኑ፣ መጽፋቸውን ይዤ ስታይ ትንሽ እንዳስብ አድርጎኛል፡፡ ከት ለፊቴ ካስክ ውስጥ የነበሩ ሴቶችዩኝ አስተያየት ይህንኑ የሚያመላክት መሰለኝ። ለማንኛውም ሐፉን ቶሎ መጨረሴ ቅሞኛል፡፡

መጽፉ ሦስት ዓበይት ክፍሎች አሉት፡፡ የመጀመርያው ክፍል ስለመደመር ዕሳቤ ይተርካል፡፡ በተለመደው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥተኛ፣ ቀልድ አዘልና ውስጥን በሚያነሳሳ የአነጋገር ዘይቤ ስለመደመር ባህሪያትና ለመደመር አስፈላጊ ስለሆኑ ቅድመ መጠይቆች፣ በዋነኝነት ስለቅንነት ያብራራል፡፡ ሥልጣን ላይ ያሉትን ለማስደሰት ማሸርገድን ጨምሮ አሁን ላይ የሚስተዋሉ የኢትዮጵያውያን አሉታዊ ባህሪያትንም ይገልጻል (‹‹ገራችን ይህ አድርባይነት አስተሳሰብ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየጨመረ በመምጣቱ ምክንያት የዝብን ድጋፍና ተቃውሞ መለየት እስኪሳነን ድረስ ደርሶ ነበር፡፡››67)፡፡ ሕዝቦች ሀቀኛና ጠንካራ ሠራተኛ እንደሆኑ ያለውን አዎታዊ ተፅዕኖም አስረግጦ ያብራራል፡፡  

ይህ ክፍል የኢትዮጵያን አብዮታዊ፣ ዴሞክራሲያዊ መንግሥት በጥልቀት ይወቅሳል፣ እንዲሁም ያወድሳል፡፡ ሆኖም ስላለፉት ባለልጣናት ‹‹ሰነድ የሚሸጥ›› ጽሑፍ በጭራሽ አይደለም፡፡ እንዲያውም ስላለፉት መንግሥታ ጥፋት ሲገልጽ ከአድራጊዎቹ ይልቅ ድርጊቶቹ ላይ በማተኮር፣ ቁጥብነት በሚታይበት መንገድ በደፈናው መገር የሚገባውን በደፈናው፣ የተወሰነ አካልመውቀስ ሚያስፈልግበት ጊዜ ደግሞ በግልጽ የሚናገር ጽሑፍ ነው። ጸሐፊው ያለፉ መሪዎችን ወይም ሁነቶችን ስም ብዙም አሱም፡፡ ሆኖም በመጀመርያው ምዕራፍ ስለሜቴክ እንዲህ ተብ፡፡ ‹‹መንግሥት ቀስ በቀስ ከገበያው እየወጣ ይሄዳል የሚለው መርህ ተዘንግቶ በጥቂት መታት ውስጥ በፕራይቬታይዜሽን ወደ ግል ካዞርናቸው ተማት የሚበልጡ ተማትን እንደገና አቋቋምን። በብረታ ብረትና መሰል ግዙፍ ዘርፎች እንዲሰማሩ ያቋቋምናቸው ተማት ቴሌቪዥን መገጣጠም ጀመሩ ብለን ፈነደቅን።››

የመጽየመጨረሻዎቹ ሁለት ክፍሎች ደግሞ ከፍልስፍና ይልቅ ስለኢትዮጵያ ፖለቲካዊና ተቋማ ነባራዊ ሁኔታ የሚተነትኑ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ መዋቅራዊና ግለሰባዊ ጭቆና ምክንያት የተከሰቱ ብዙ ችግሮች አሉ፡፡ ፖለቲካችን የዘረኝነት ጉዳይ ጎልቶ እንዲታይበት ካደረጉ ምክንያቶች ውስጥ አንዱ በድሮ ጊዜ የነበረው ጭቆና ነው፡፡ አንድ የኅብረተሰብ ክፍል የመጨቆን ታሪክ ካለው ሰዎች ስለ ዘር ማንነታቸው፣ (ትውል፣ ከመደታ ማንነታቸው በላይ) ያላቸውን አመለካከት ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ ዓብይ አህመድ እንደሚገ ዘር ሕዝብን ለትግል ለማንቀሳቀስ የሚያገለግለው ግን በዋነኝነት ልሂቃን ዘርን ለፖለቲካ እንቅስቃሴ መጠቀሚያ አድርገው በሚያውሉበት መጠን ነው፡፡

ኢትዮጵያ ያሉ ተቋማ ቴክኒካዊ ብቃት በሌላቸው፣ ሕዝቡን ማገልገል በማይፈልጉ፣ የግል ጥቅማቸውን ከማኅበረሰቡ ደኅንነት በሚያስቀድሙ፣ ራሳቸውም አግባብ ባልሆነ መንገድ ቦታውን በያዙ ሰዎች የተሞላ እንደሆነ መደመር ይገልጻል፡፡  ተቋማ ሥር የሰደደ የግትርነት ችግር አለባቸው፡፡ ሆኖም ለውጥ ግን ቀላል አይሆንም፡፡ እንደ ቢፒአርና ካይዘን በተደጋጋሚ የተነሱ አገር አቀፍ እንቅስቃሴዎችም የተነሳ በአገሪቱ ውስጥ ‹‹የለውጥ ዝለት›› አለ። ይልቁንም እንደ ጸሐፊው የሚያስፈልገን በጠንካራ አመራር የተደገፈ፣ በለውጥ ዋርያ የሚመራ እንደ ዘርፉ ልዩ ባህሪይ ለየዘርፉ የሚተለም ለውጥ ነው፡፡

ከምዕራፍ አምስት እስከ አሥር ያለው ክፍል በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ሐደት ውስጥ የተስተዋሉ መልካም ሁኔታዎችንና ህፀፆችን ያብራራል፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየውን የዘር ክፍፍል መሠረታዊ ምክንያቶች በመዘርዘር፣ ክፍፍሉን አቻችሎ አገራዊ መግባባትና ሰላም ለማምጣት የሚረዳ መመርያ ያቀርባል፡፡ በጣም አከራካሪ ለሆኑ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጥያቄዎች ደግሞ የክርክሮቹ መሪዎች አመለካከታቸውን በመደመር አመለካከት መቃኘት እንዳለባቸው መጽየሚያሳስብ ይመስላል፡፡ ይኸውም እነዚህ አካላት ሰላማዊ ውይይቶችን እንዲያደርጉ፣ ለተከታዮቻቸውም መልካም መሪ በመሆን ለማሳመን እንዲሞክሩ፣ ማኝነትን ለመግዛት እንዳይሞክሩ፣ ያለፈውን እንዲያልፍ በመተውና የከፋ ኢፍትሐዊነት ያጋጠመበት ታሪክ ካለ ደግሞ ጥልቅ ጥናት በማድረግ እውነቱን አጣር ስህተትን ማረምና ሁልጊዜም የፖለቲካ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ዘ ላይ ማተኮር ይልቅ፣ ሌሎች የማንነት ቡድኖችን ለመመረት ማሰብ እንዳለባቸው ይገል፡፡

ምዕራፍ ስድስት ምናልባትም በጣም አስደሳች የሆነውን ርዕስ፣ ‹‹ኢትዮጵያ ምን ዓይነት ዴሞክራሲ ያስፈልጋታል?›› የሚለውን ይዳስሳል፡፡ ጸሐፊው ኢትዮጵያዊ የሆነ ዴሞክራሲ የመገንባት ሒደት እንዴት ማስጀመር እንዳለብን ያስረዳሉ፡፡ በመጀመርያ በልዩነት ላይ ባተኮሩ ቲዎች መካከል ትብብርን የሚያበረታታ የዴሞክራሲ ሥርዓት ሊኖረን ይገባል፡፡ ባለፈው የሕገ መንግሥት ግንባታ ወቅት በረሰባዊ ርተኞች ላይ በማተኮር፣ ገሸሽ ተደርገው ከነበሩ ሲቪክ ብሔርተኞች ጋር ቀጣይነት ያለው ድርድር ያስፈልጋል፡፡

ይህንን ደግሞ ያለ አድልኦና ቅሬታ ለማድረግ አገራዊ ሰላምና ዕርቅ ላይ ቀድሞ ሊደረስ ይገባል። ጥልቅ የሆነ ጥናትና ታሪካዊ ኢፍትሐዊነትን ለማራት እውነታን የመፈለግ ሥራም ሊያስፈልግ ይችላል። ከዚህ በፊት ተቁነው የነበሩ የኅብረተሰብ ድምፆች የሚናገሩበት አገራዊ መድረኮች ሊዘጋጅ ይገባል። ልሂቃንና የአገሪቱ ምሁራን ውድድርና ከትብብር ዕጦት የተነሳ ብቻቸውን እየሞቱ ካሉበት ሊወጡና በንቃት ሊሳተፉ ይገባል፡፡ እንዲሁም ሕዝባዊ ማኅበራትና ሚዲያዎች ሊጠናከሩና ምክንያታዊ አስተሳሰብን ሊያስተምሩ ይገባል፡፡ ይህ ሒደት በሙላት መንቀሳቀስ ሲጀምር ልዩ የሆነ፣ ለእኛ ማንነት የሚስማማ ዴሞክራሲ መታሰብ ይጀምራል ይላሉ፡፡

ምዕራፍ ዘጠኝ ስለአመራር ዓይነቶች በማስረዳት ራሳቸው መሪውን የምንገመግምበትን ጠቃሚ ፈርት ይሰጣል፡፡ ከምዕራፍ አሥራ አንድ እስከ አሥራ ስድስት ያለው ክፍል ከሞላ ጎደል ሙያዊ (ቴክኒዊ) ነው፡፡ ስለኢትዮጵያ ሥነ ምጣኔና ፖለቲካ ሊታሰቡ የሚችሉ ርዕሶች ሁሉ በዳሰስና ጉዳዮቹ በመደመር ዓይን እንዴት እንደሚታዩ አጭር አስተያየት ብቻ በመስጠት፣ የትምህርት መጽፍ በሚመስል ደረቅ አገላለጽ ያቀርባል። የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ የኢኮኖሚ ርዓቱ መዛባቶችሥራ አጥነትን፣ የገቢ ልዩነት፣ የኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ውድቀትን፣ የውጭ ዕርዳታን፣ በግሉ ዘርፍና በንግድ ውስጥ የመንግሥት ተሳትፎን በተመለከተ ምክንያታቸውንና ውጤታቸውን፣ እንዲሁም መጨረሻ ስለመደመርና የውጭ ግንኙነትን በተመለከተ ይዳስሳል፡፡

ሐሳቡ ጥልቅ ነገሩ ጥብቅ 

መጽሐፉ የንግድ ዓላማ የለውም፣ የሽያጭ ገቢውም ለገጠር ትምህርት ቤት ግንባታ እንደሚውል ተገልጿል፡፡ ባይሆንም ግን መደመር ራሱን ለመሸጥ የሚሞክር መጽፍ አይደለም። መጽሐፉ ብዙ ጊዜ በአገራችን እንደሚስተዋለው ሳይሆን ዲዛይኑ፣ አርትኦቱ ኅትመቱ ጥራት ዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ነው ማለት ይቻላል። ሆኖም ልክ ቴሌቪዥን እንደምናየው የዓብይ አህመድ መጽጻጻ ‹ውሰዱት ወይም ተውት› ዓይነት ድምፀት አለው፡፡ መግቢያው አንባቢን አንቆ ለመያዝ አይሞክርም፡፡ አንባቢውንም እንዲያነበው የሚለምን ዓይነት አይደለም። ጸሐፊው የእኔ ያሉትን እውነ ረጋ ቀለል አድርገው ነው የገለት። ሳብ የመሰብሰብ ችሎታውና ራስን የመጠራጠር ፍንጭ እንን የሌለው መሆኑ ድንቅ ነው፡፡ 

መጽሐፉ የምረዳው አንድ ነገር ቢኖር ጸሐፊው ለሚዛናዊነት ትልቅ ቦታ እንደሚሰጡ ነው። ሚዛናዊነት በወግ አጥባቂነትና በተራማጅነት መሀል፣ ሚዛናዊነት ርተኝነትና በሲቪክ ብሔርተኝነት መል፣ ሚዛናዊነት ባህላዊ ዕውቀትን ይዞ መቀጠልና የውጭውን ዕውቀት ማስገባት መሀል። ጸሐፊው አዲስ ዕውቀትን ለመፈልሰፍ ዓላማ እንደሌላቸው ይገልጻሉ፡፡ ‹‹ዕውቀት ሁላችንም የምንጋራው፣ የሁላችንም ንብረት የሆነ ፀጋ እንደሆነ መርሳት የለብንም፤›› ይላሉ፡፡ የመደመር ሥነ ምጣኔያዊ አስተሳሰብም በዓለምና በኢትዮጵያ ከካፒታሊዝምና ከሶሻሊዝም ልምድ በመውሰድ የተወለደ አስተሳሰብ ይመስለል፡፡ መደመር ዕድሜ ልክ ከቆየ ጥልቅ ሳብሁለት ፅንፍ አመለካከቶችን ካሰላሰሉ በ የመነጨ ንድፈ ሐሳብ ይመስላል፡፡ ሆኖም መደመር ከምሳጤ አስተሳሰብ የተወለደ መስልም ኃይለኛና ፅዕኖ ፈጣሪ ነው፡፡ በአንድ ቦታና ጊዜ ከተገደበ ዕምነት ይልቅ፣ ጊዜ የማይገድበው የማሰቢያ መሣሪያ ነው፡፡

መደመር ከሞላ ጎደል የፍልስፍና መጽፍ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ስእውነት፣ ጊዜ፣ የሰው ልጆች ርካታ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ ስላለው ዋጋ ስለዴሞክራሲ ለማንበብ ደስታን በሚሰጡ አጻጻፎች አቅርቧል። አስተሳሰባችንን ካለፈው ልምዳችንና ለወደፊቱ ካለን ተስፋ ማስተካከል እንዳለብን የገለጹት አንዱ የማልረሳው በውስጤ የቀረልኝ ምሳሌ ነው፡፡ ‹‹ዛሬውን ጉልበታችንን የሚያጠነክር፣ ከትናንት የወኔ ስንቅ የሚቀበል የተስፋ መነር ነው የሚያስፈልገን። ትናንትን ከዛሬ ጋር ፈትለን ከህልማችን ሰም ውስጥ ስንነክረው ነው ተስፋችን ጧፍ ሆኖ ጭለማውን የሚያሻግረን፤›› ይላሉ፡፡

ተስፋችን ጧፍ

መደመር ቀለል ባለ ቋንቋ ቢሆንም የተጻፈው ነገሮችን የሚያቃልል ግን አይደለም፡፡ አማርኛው በጣም መሳጭ ነው፡፡ እንዲያውም ለመጀመርያ ጊዜ ሥራ ላይ የዋሉ ናቸው ብዬ ያሰብኳቸውን ቃላት አግኝቼበታለሁ (ውላጅ፣ ዳረጎት መንግታት፣ ራስበቅ፣ ክሱትነት፣ ቀቢፀተስፋ አዲስ ቃላት ካልሆኑ ጥፋቱ የኔ ይሆናል)፡፡ ይህን ለመሰለ ኦፊላዊ አጻጻፍ አማርኛው ባልተለመደ ሁኔታ ምቹ ነው፡፡ እንሊዝኛ ጭራሽ አይጠቀምም ማለት ይቻላል፡፡ ይህ በእንዲህ እያለ መደመር ቀላል መጽፍ አይደለም፣ በተለይ ደግሞ ሁለተኛው ክፍል፡፡ የመጨረሻዎቹን ምዕራፎች ለመጨረስ ትንሽ ትዕግ የሚፈልግ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ የመጽፉ አንባቢያን ሊሆኑ የሚችሉት የረም ንባብ ልምድ ያላቸው በደንብ የተማሩ ኢትዮጵውያን ናቸው ማለት ነው፡፡ 

ይህ ደግሞ ስለማንበብ ባህላችን እንዳስብ ያደርገኛል፡፡ ‹የተማሩ ኢትዮጵያውያን› ከባሉት ውስጥ ምን ያህሉ ይህንን መሐፍ አነበቡት? ምን ያህሉስ የፖለቲካ ልዩነትን አሳበው ሳያነቡት ቀሩ? የሌሎችን ሐሳብ ለመረዳትና ራሳችንን ለመግለጽ ምን ያህሎቻች በእውነት እንችላለን የሚለው አጠያያቂ ነው፡፡ ያ ደግሞ ለዴሞክራሲ ወሳኝ ነው፡፡ ምክንያቱም ዴሞክራሲ ‹‹አላዋቂ ብዙኃን›› አገዛዝ እንዳይሆን ነው፡፡

በመጽሐፉ መገባደጃ ላይ ጸሐፊው በውስጤ እየጠየቅኩ የነበረውን ብዙኃን ለመድረስ በሌላ መንገድ ቢቀርብ የተሻለ ተቀባይነት ይኖረው ነበር ወይ የሚለውን ጥያቄ ዳሰዋል፡፡ መጽፉ በሌሎች ዓይነት ቅጂዎች እየመጣ ነው፡፡ በተጨማሪም በእንግሊዝኛም ቅጂ እየመጣ ነው፡፡

ሳጠቃልል ለመጽሐፉ ያለኝ ምሥጋና ቁጥብ መሆን እንዳለበት ይሰማኛል፡፡ ብዙ ማድነቁ የጥልቀት ማጣት ተደርጎ ሊወሰድ ስለሚችል ወይም ምሥጋና ሲበዛ አመዛዝኖ አሳቢነትን ጥያቄ ውስጥ እንዳያስገባው ከመሥጋት ነው። እውነታው ግን በመጽፉም ሆነ መጽፉን ለመጻፍ ተነሳስተው ስለጀመሩት፣ ጀምረውም ለጨረሱት በጣም ተደምሜያለሁ፡፡ መደመርን እንድታነቡት አበረታታለ፡፡ ችግር የሚያረዱ ሰበር ዜናዎችን በሰማችሁ ቁጥር ያጣችሁትን ተስፋ ለማደስ ስትሉ አንብቡት፡፡

ኢትዮጵያ ልዩ አገር እንደሆነች ያላችሁን እምነ የሚገዳደሩ ንግግሮችን ወደ ጎን ትታችሁ፣ በእምነታችሁ እንድትቀጥሉ አንብቡት፡፡ ኢትዮጵያ የአንባቢያን አገር እንድትሆን የምትወስዱት የመጀመርያው ዕርምጃ ስለሚሆን አንብቡት፡፡ አንድ ሰው እውነቱን ለማስረዳትና መልዕክቱን ለማስተላለፍ ሚያደርገው ሙከራ ክብር ለማሳየት ስትሉ አንብቡት፡፡ እናም ሌሎች እውነት ካላቸው እንዲሁ በርዓ ማቅረብ እንዳለባቸው መልዕክት ለማስተላለፍ አንብቡት።

ከአዘጋጁ፡– ይህ ጽሑፍ በመጀመርያ በ‹‹Ethiopia-Insight.com›› ላይ በእንግሊየታተመ ሲሆን፣ ይህ ትርጉም በማህሌት ልሳወርቅና ሊንዳ ዮሐንስ ነው፡፡ ጽሑፉ የጸሐፊዋን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...