Sunday, April 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊልሂቁ ኢኮኖሚስት ነዋየ ክርስቶስ ገብረአብ (1934-2012)

ልሂቁ ኢኮኖሚስት ነዋየ ክርስቶስ ገብረአብ (1934-2012)

ቀን:

ለስድስት አሠርታት ያህል በኢትዮጵያና በዓለም አቀፍ ተቋማት በኢኮኖሚ (ምጣኔ ሀብት) ባለሙያነታቸው ከፍ ያለ አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ በተለይ ከ1983 ዓ.ም. የመንግሥት ለውጥ በኋላ፣ ከሩብ ምዕት ዓመት በላይ የኢትዮጵያ ሽግግር መንግሥትንና ተከታዩን ፌዴራላዊ ሪፐብሊክን በከፍተኛ የኢኮኖሚ አማካሪነት ያገለገሉት አቶ ነዋየ ክርስቶስ ገብረአብ ናቸው፡፡ በ1950ዎቹና በ1960ዎቹ መጀመርያ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን (1923-1967) በኢትዮጵያ ልማት ባንክና በፕላን ኮሚሽን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ሠርተዋል፡፡

በ1960ዎቹ አጋማሽ ባህር ማዶ በመዝለቅም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የንግድ ኢንቨስትመንትና የልማት ጉዳዮች ኮንፈረንስ በኢኮኖሚክስ ኦፊሰርነት፣ በዩኔስኮ ሥር በሌሴቶ የትምህርት ዕቅድ አማካሪ በመሆን አገልግለዋል፡፡ በመቀጠልም በተመድ የልማት ፕሮግራም (ዩኤንዲፒ) አማካሪ፣ በዓለም ምግብ ድርጅት (ፋኦ) እስከ 1983 ዓ.ም. ድረስ ሠርተዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለውጥን ተከትሎ አዲስ አበባ የተመለሱት አቶ ነዋይ፣ ከ1984 ዓ.ም. ጀምሮ በጡረታ እስከ ተሰናበቱበት ጊዜ ድረስ በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊነቶች አገልግለዋል፡፡ በሽግግር መንግሥት የፕሬዚዳንቱ የኢኮኖሚ አማካሪ፣ ፌዴራላዊ ሪፐብሊኩ ሲመሠረትም ከ1988 ዓ.ም. ጀምሮ በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ዋና የኢኮኖሚ አማካሪና የአማካሪዎቹ ቡድን መሪ በመሆን፣ ሁለቱን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትሮች አቶ መለስ ዜናዊና አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝን አማክረዋል፡፡ በዚሁ ረዥም የአገልግሎት ዘመናቸው ከሽግግሩ ጊዜ ጀምሮ በአገሪቱ ሥራ ላይ የዋሉት ተከታታይ የአጭር፣ የመካከለኛና የረዥም ጊዜ የልማት ስትራቴጂዎች ቀረፃ፣ ግምገማና ምዘና ሒደት ላይ ጉልህ ሚና ነበራቸው፡፡ የተከማቸ ብድር ጫና የነበረባቸውን ደሃ አገሮች ለማገዝዓለም የገንዘብ ድርጅትና የዓለም ባንክ ... 1996 የጀመሩት “Heavily Indebted Poor Countries Initiative” በተባለ ፕሮግራም መሠረት ከአበዳሪ ተቋማትና አገሮች ጋር ተደራድሮ ኢትዮጵያ የዕዳ ስረዛ ዕድሉ ተጠቃሚ እንድትሆን ለማድረግላፊነት የተሰጠው ቡድን አባል በመሆን ባደረጉት ጥረት፣ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የዕዳ ስረዛ ተጠቃሚ እንድትሆን አድርገዋል፡፡

በወሳኝ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ለመምከርና ለመወሰን የተቋቋመው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰብሳቢነት የሚመራው የማክሮ ኢኮኖሚ ምክር ቤት ውስጥ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ማገልገላቸው ይወሳል፡፡

የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ፖሊሲና ስትራተጂ በምርምርና ጥናት የታገዘ እንዲሆን ለማድረግ የኢትዮጵያ ልማት ምርምር ኢንስቲትዩት ሲቋቋም፣ በሚኒስትር ማዕረግ በዋና ዳይሬክተርነት በማደራጀትና በመምራት በአፍሪካ አሉ ከሚባሉ ቀዳሚ የምርምር ተቋማት አንዱ እንዲሆን በማድረግ፣ በተለይም በሰው ኃይል ግንባታ ያደረጉት ጥረት በአገሪቱ ከነበሩት ጥቂት ዩኒቨርሲቲዎች የላቀ ውጤት አምጥተው የጨረሱ ወጣት ምሩቃንን አወዳድሮ በመምረጥ፣ በአውሮፓና እስያ ዕውቅ ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ፒኤችዲ በማስተማር በአገሪቱ እያገለገሉ የሚገኙ በርካታ ወጣት ተመራማሪዎችን ለማፍራት አስችለዋል፡፡

1996 እስከ 2008 .. የኢትዮጵያ መንግሥትን በመወከል የአፍሪካ ልማት አዲስ አጋርነት  (ኔፓድ) አስተባባሪ ኮሚቴ አባል፣ ቀጥሎም ሊቀመንበር በመሆን ሠርተዋል፡፡ በተጨማሪም በዚሁ ዘመን የአፍሪካ የጋራ ግምገማ መድረክ (ኤፒአርኤም) አባል በኋላም ሊቀመንበር በመሆን አገልግለዋል፡፡ 2001 እስከ 2005 ዓ.ም. ድረስ በአፍሪካብረት በኩል በቡድን 20 ስብሰባዎች አፍሪካን ወክለው በመገኘት ሲሳተፉ፣ የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም የሚችል የረዥም ጊዜ የኢኮኖሚ ስትራቴጂ ቀረፃ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ሰብሳቢ ነበሩ፡፡ 2002 እስከ 2003 ዓ.ም. የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ በሰየሙትና የኖርዌይና የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሮች በጋራ ይሰበስቡት በነበረው የፋይናንስ አማካሪ ቡድን አባል ሆነውገልግለዋል፡፡ 1995 እስከ 2002 .. ድረስ የመንግሥትና የለጋሽ ድርጅቶች ኮሚቴ የዕርዳታ አፈጻጸም የቁጥጥርና የአስተዳደር ማሻሻያ ውስጥ ሰብሳቢ ሆነው ሠርተዋል፡፡ 1996 እስከ 2001 .. የኢትዮጵያ የንግድ ውድድር ኮሚሽን አባል በመሆን ያገለገሉት አቶ ነዋየ ክርስቶስ፣ትግራይ ልማት ማኅበር የቦርድ አባልም ነበሩ፡፡

ከአባታቸው ከአቶ ገብረአብ ቢያድግልኝ፣ ከእናታቸው ወ/ሮ እሌኒ መንገሻ ጥቅምት 17 ቀን 1934 ዓ.ም. በድሮ አጠራር በትግራይ ጠቅላይ ግዛት በዓድዋ አውራጃ ልዩ ስሙ ማይምሻም በተባለ ቦታተወለዱት አቶ ነዋየ ክርስቶስ፣ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ካዛንችስ አስፋ ወሰን አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በኮተቤ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በከፍተኛ ማዕረግ አጠናቀዋል፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ይባል በነበረው (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) በመግባት 1954 .. በኢኮኖሚክስ የመጀመርያ ዲግሪ ካገኙት ጥቂት ኢትዮጵያውያን አንዱ ነበሩ፡፡ 1958 .ም. እንግሊዝ ከሚገኘው የማንቸስተር ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ ድኅረ ምረቃ ዲፕሎማ፣ በመቀጠልም 1975 .ም.ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ የማስተርስ ዲግሪ ተቀብለዋል፡፡

ባለትዳርነበሩት አቶ ነዋየ ክርስቶስ፣ ለኢትዮጵያና ጃፓን ግንኙነት መጠናከር ላበረከቱት አስተዋፅኦ ‹‹Order of the Rising Sun Gold and Silver Star›› የተባለው በጃፓን ለአንድ ሲቪል ሊሰጥ የሚገባው ከፍተኛው ሽልማት ከጃፓን ንጉሥ ተበርክቶላቸዋል፡፡

አቶ ነዋየ ክርስቶስ በ1960ዎቹ የመጀመርያ ዓመታት በአዲስ አበባ ይታተም በነበረው ሳምንታዊው ‹‹አዲስ ሪፖርተር›› (Addis Reporter) የእንግሊዝኛ መጽሔት በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ይጽፉ ነበር፡፡ የመካከለኛው ምሥራቅ የገበያና የውል ጉዳዮችን የሚተነትን በለንደን የሚታተም ወርኃዊ መጽሔት (Middle East Economic Digest MEED) የዝግጅት አማካሪ በመሆንም ሠርተዋል፡፡

አቶ ነዋየ ክርስቶስ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚን በሚመለከት በርካታ ጽሑፎችን አዘጋጅተው ለንባብ ከማብቃታቸውም በላይ፣ የታዳጊ አገሮችን ኢኮኖሚ በሚመለከት አራት ጽሑፎችን አዘጋጅተዋል፡፡ ጡረታ ከወጡ በኋላም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አፈጻጸምና የልማት አቅጣጫዎች በሚመለከት ያዘጋጁትን መጽሐፍ ለማሳተም፣ በዓለም ከታወቁ አሳታሚዎች ጋር እየተነጋገሩ እንደነበር ገጸ ታሪካቸው ያስረዳል፡፡

አቶ ነዋየ ክርስቶስ ባደረባቸውመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው የካቲት 16 ቀን 2012 .. በ78 ዓመታቸው አርፈው፣ ሥርዓተ ቀብራቸው የካቲት 18 ቀን በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል፡፡

አቶ ነዋየ ክርስቶስ በአማካሪነት በሠሩባቸው ጊዜያት በሁለቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዶች ውስጥና ለአየር ንብረት የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ባወጣው ፖሊሲ ሥር በሚቀረጹ ዕቅዶች ከፍተኛ ሚና እንደነበራቸው የሚነገርላቸው ሲሆን፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና ለአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት እጅ ለእጅ መሄድ አለባቸው የሚል እምነት ስላላቸው፣ በሁሉም ተግባሮቻቸው ውስጥ ከግንዛቤ የሚከቱት ዕሳቤ መሆኑ ይወሳል፡፡

አቶ ነዋየ ክርስቶስ በአማካሪነት ባገለገሉባቸው ዘመኖች ማብቂያ ገደማ በኢትዮጵያ መንግሥት በይፋ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የኢኮኖሚ ጉዳዮች ኮሚሽነር ለመሆን እንዲወዳደሩ፣ እ.ኤ.አ. በ2017 ዕጩ ተደርገው ቀርበውም ነበር፡፡

የእሳቸውን ዕጩነት ያወጁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሒሩት ዘመነ፣ ‹‹የተሳካላቸውና የአሠርታትን ልምድ ያካበቱት አቶ ነዋይ አፍሪካን ወደ ዕመርታ ይመሯታል፤›› በማለት፣ በኢኮኖሚ ዘርፉ ያላቸውን ልምድ ያሞገሱ ሲሆን፣ ‹‹በኢትዮጵያ የመጣውን የኢኮኖሚ ተዓምር ለአፍሪካም ይደግሙታል፤›› ብለው ነበር፡፡

አቶ ነዋይ በዚህ ወቅት ባደረጉት ንግግር በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የኢኮኖሚ ጉዳዮች ኮሚሽን በአፍሪካ አገሮች የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂዎችና ዕቅዶች ውስጥ ተገቢውን ሥፍራ ሊይዝ ይገባል ያሉ ሲሆን፣ በዚህም ለአፍሪካ ኅብረት አጀንዳ 2063፣ ለኢኮኖሚ ትስስር፣ ለነፃ ገበያ፣ እንዲሁም ለኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ቃል ገብተው ነበር፡፡

(ለዚህ ጽሑፍ ብሩክ አብዱ አስተዋጽኦ አድርጓል)

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ኦቲዝምን ለመቋቋም በጥምረት የቆሙት ማዕከላት

ከኦቲዝም ጋር የሚወለዱ ልጆች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ...

አወዛጋቢው የወልቃይት ጉዳይ

የአማራና ትግራይ ክልሎችን እያወዛገበ ያለው የወልቃይት ጉዳይ ዳግም እየተነሳ...

ተጠባቂው የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የውድድር መለኪያ የሆነው የሞባይል ገንዘብ ዝውውር በኢትዮጵያ

የሞባይል ገንዘብ ዝውውር የሞባይል ስልክን በመጠቀም ሊገኙ የሚችሉ የፋይናንስ...

የአማራና ደቡብ ክልሎች ለሠራተኛ ደመወዝ መክፈል መቸገራቸውን የፓርላማ አባላት ተናገሩ

በአማራና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት...