- Advertisement -

ዋና ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግና የንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት ከኃላፊነታቸው ተነስተው የአምባሳደርነት ሹመት ተሰጣቸው

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ባቋቋሙት ካቢኔ ውስጥ ከተካተቱት የመጀመርያዎቹ የካቢኔ አባላት ውስጥ አንዱ የነበሩት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ባጫ ጊኒን ጨምሮ 15 በተለያዩ ኃላፊነት ሲሠሩ የነበሩ ግለሰቦች፣ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርና አምባሳደር ሆነው ተሾሙ፡፡

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ማክሰኞ የካቲት 24 ቀን 2012 ዓ.ም. በሰጡት ሹመት ዘጠኝ ባለሥልጣናት ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሲሆኑ፣ ስድስት ግለሰቦች ደግሞ በአምባሳደርነት ሥልጣን ተሹመዋል፡፡

አምባሳደሮቹ በተለያዩ አገሮች እንደሚመደቡ ከመግለጽ ባለፈ ማን በየትኛው አገር እንደሚመደብ ባይገለጽም፣ ዋና ዓቃቤ ሕግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ፣ የሕፃናት፣ ወጣቶችና ሴቶች ሚኒስትር ወ/ሮ የዓለም ፀጋዬ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሒሩት ዘመነ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ማርቆስ ተክሌ (አምባሳደር)፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ባጫ ጊና፣ አቶ ይበልጣል አዕምሮ፣ አቶ ምሕረት አብ ሙሉጌታ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አቶ ነብያት ጌታቸውና አቶ ተፈሪ መለስ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል፡፡

አቶ አድጎ አምሳያ፣ አቶ ጀማል በከር፣ አቶ አብዱ ያሲን፣ አቶ ለገሠ ገረመው፣ ወ/ሮ እየሩሳሌም ዓምደ ማርያምና አቶ ሽብሩ ማሞ ደግሞ በአምባሳደርነት መሾማቸው ተገልጿል፡፡

የአምባሳደርነት ሹመት የተሰጣቸው ግለሰቦች በተለያዩ ተቋማት በከፍተኛ ሥልጣንና ኃላፊነት ላይ ተሹመው በመሥራት ላይ ያሉ ቢሆንም፣ ማርቆስ ተክሌ (አምባሳደር) በኤርትራ የኢትዮጵያ አምባሳደር በነበሩት በሬድዋን ሁሴን (አምባሳደር) ከመተካታቸው በስተቀር፣ ሌሎቹን ማን እንደሚተካቸው ወይም ከሥልጣናቸው ተነስተው ለአምባሳደርነት ሹመት ያበቃቸውም ምክንያት አልተገለጸም፡፡  

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የኢትዮጵያ ጂዲፒ በውጭ ምንዛሪ ለውጡ ምክንያት ወደ 100 ቢሊዮን ዶላር መውረዱ ተገለጸ

የአገሪቱ የውጭ ዕዳ ጂዲፒ ጥምርታ ለደሃ አገሮች ከተቀመጠው ጣሪያ አልፏል የኢትዮጵያ ኖሚናል ጂዲፒ (የዋጋ ንረትን ታሳቢ ያላደረገ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት) በዶላር ሲተመን፣ በሰኔ ወር...

ከአፋር በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ለተፈናቀሉ ተጨማሪ ድጋፍ ተጠየቀ

የከሰም ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች በሙሉ ተፈናቅለዋል ተብሏል በአፋር ክልል ገቢ ረሱ ዞን በሚገኙት በአዋሽ ፈንታሌና በዱለቻ ወረዳዎች በቀጠለው የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ከአካባቢው ለተፈናቀሉ ዜጎች እየቀረበ ያለው...

በውዝግብ የተሞላው 18ኛው የአዲስ አበባ የንግድ ዘርፍ ማኅበራት ጉባዔና ምርጫ እያነጋገረ ነው

ከጉባዔው አንድ ቀን በፊት አባል ሆነው የተመረጡ 55 ነጋዴዎች ለቦርድ አባልነት መቅረባቸውም ግርምትን ፈጥሯል የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት መተዳደሪያ ደንብ፣ ጠቅላላ ጉባዔው...

የአየር ንብረት ለውጥ በግብርናው ዘርፍና አመጋገብ ሥርዓት ላይ አደጋ ደቅኗል ተባለ

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየበረታ የመጣው የአየር ንብረት ለውጥ ጫና በኢትዮጵያ ግብርናና የአመጋገብ ሥርዓት ላይ አደጋ ደቅኗል ተባለ፡፡ ይህ የተነገረው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብና...

በምርጫ ወቅት ማጭበርበር አምስት ዓመታት እንደሚያስቀጣ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011ን ለመተካት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተረቀቀው አዲስ አዋጅ፣ በተጭበረበረ መረጃ ለመወዳደርና ለመመረጥ የሚሞክሩ...

በመጀመሪያው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት 75 በመቶ ተጠቃሚዎች የመኪና ማቆሚያ መቸገራቸው በጥናት ተረጋገጠ

በኮሪደር ልማት ፕሮጀክት 75 በመቶ ተጠቃሚዎች የመኪና ማቆሚያ ቦታ ለማግኘት መቸገራቸው በጥናት መረጋገጡን፣ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮና ሁለት የግል ተቋማት አስታወቁ፡፡ ጥናቱ የቀረበው ጥር...

አዳዲስ ጽሁፎች

መንግሥት ገቢ ከመሰብሰብ ባሻገር ለሕዝብ ኑሮ ትኩረት ይስጥ!

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ ያለበት በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ ከሚሰበሰብ ታክስ ብቻ ሳይሆን ከግብርና፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከማዕድን፣ ከአገልግሎትና ከሌሎች ሀብት አመንጪ ዘርፎች ጭምር ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ቁጥራቸው...

የኢትዮጵያን ትንሳዔ ለማብሰርና ለመከወን ምን እናድርግ?

በጌታነህ አማረ ኢትዮጵያ ማለት ታላቅ አገር ቀደምት የሰው ዘር መገኛና የሥልጣኔ ባለቤት የሆነች አገር እንደነበረች ታሪክ ሲያወሳን ይኖራል። በዚያውም ልክ ይህች ታላቅ ነበረች የምትባል አገር...

የምድራችን (የሰው ልጆች) ተማፅኖ — አረንጓዴ ፖለቲካ!

(ወጥመዶችና ማምለጫችን) በታደሰ ሻንቆ የወጥመዶች ዓለም በአፍሪካ ቀንድ አገሮች ዘንድ ያሉ ውዝግቦችና ግጭቶች ምንም ተቀባቡ ምን፣ መሬትን ውኃን አፈርን ማዕድናትን ንግድንና መሰል ጥቅሞችን የተመለከቱ ናቸው፡፡ በእነዚህ...

‹‹መንግሥት ከሁሉም ነገር በላይ ቅድሚያ ሰጥቶ የኢኮኖሚ ጫናውን ለመቀነስ የነዳጅ ድጎማውን መቀጠል ይኖርበታል›› ሰርካለም ገብረ ክርስቶስ (ዶ/ር)፣  የነዳጅ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ

የነዳጅ ግብይት ሥርዓትን ለመዘርጋትና ለመቆጣጠር ያስችላል የተባለ አዲስ አዋጅ ባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቋል፡፡ በኢትዮጵያ በነዳጅ ሥርጭት ግብይትና በአጠቃላይ በዘርፉ ያሉትን ማነቆዎች...

ስለካፒታል ገበያ ምንነትና ፋይዳ ያልተቋረጠና የተብራራ መረጃ ማድረስ ያሻል!

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡ አገራዊ ኢኮኖሚውን ከመደገፍና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች የሚውል ካፒታል ለማሰባሰብ እንደ አንድ አማራጭ የሚወሰድና ለኢትዮጵያ እንደ አዲስ ምዕራፍ የሚታይ ዕርምጃ...

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘለት የሥነ ተዋልዶ ጤና ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

በኢትዮጵያ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተከሰቱ ጦርነቶችና ግጭቶች ምክንያት እየተስተጓጎለ የመጣውን የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት መልሶ ለማጠናከር ያስችላል የተባለ የ1.28 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን