Monday, December 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናኢትዮጵያ የህዳሴ ግድቡን የውኃ ሙሌት ብቻ የሚመለከት የድርድር ሰነድ ለግብፅና ለሱዳን ልታቀርብ...

ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድቡን የውኃ ሙሌት ብቻ የሚመለከት የድርድር ሰነድ ለግብፅና ለሱዳን ልታቀርብ ነው

ቀን:

ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የምትገነባውን ታላቁ የህዳሴ ግድብ የውኃ አሞላልና አለቃቀቅን በተመለከተ ከታችኞቹ የተፋሰሱ አገሮች ጋር ለመነጋገር የሚያስችላትን አዲስ የውይይት ሰነድ እንዳዘጋጀች፣ ሰነዱም በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ታወቀ።

በአዲስ ይዘት የተዘጋጀው የድርድር ሰነድ በኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን፣ በብሔራዊ የባለሙያዎች መማክርት፣ ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በተወጣጡ የሕግና የውኃ ምሕንድስና ባለሙያዎች፣ በጠቅላይቃቤግና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለሙያዎች በጋራ መረቀቁን ሪፖርተር ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

በቅርቡ ይፋ ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቀው የድርድር ሰነድ ለግብፅናሱዳን ብቻ እንደሚቀርብ፣ ነገር ግን በሦስቱ አገሮች ስምምነት መሠረት ሌሎች አጋሮች በድርድሩ ሚና እንዲኖራቸውም ክፍት መደረጉን ከመረጃው መረዳት ተችሏል።

የተዘጋጀው አዲስ ሰነድ የህዳሴ ግድቡውኃ አሞላልና አለቃቀቅን ብቻ የሚመለከት እንደሆነ፣ ኢትዮጵያ ድርድር የማታደርግባቸውን ጉዳዮች ለይቶ ማስቀመጡንና የኢትዮጵያን የማያወላዳ አቋም የያዘ እንደሆነ ምንጮች ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በግድቡም ሆነ በዓባይ ውኃ ላይ ያላትን ጥቅም የሚያስከብርና አሳልፎ የማይሰጥ እንደሆነ፣ የታችኞቹ የተፋሰስ አገሮችን ተጠቃሚነትም በዓለም አቀፍ መርሆች መሠረት የሚያረጋግጥ፣ በሦስቱ አገሮች መካከል ትብብርና መልካም ግንኙነትን የሚያሰፍን እንደሆነ ምንጮች አክለዋል።

በዚህ ሰነድ መነሻነት በሚደረገው ድርድር የሚመነጨው የመፍትሔ ሐሳብ ምን መምሰል እንደሚገባው፣ አመላካቾችንም ያስቀመጠ እንደሆነም ምንጮች አስረድተዋል።

ሰነዱን መነሻ በማድረግ የሚደረገውን ድርድር ለሦስቱም አገሮች ቅርብ የሆነው የአፍሪካ ኅብረት እንዲመራ በኢትዮጵያ በኩል ፍላጎት መኖሩን የገለጹት ምንጮች፣ መንግሥት ይህንን ዕውን ለማድረግ እየጣረ መሆኑን ጠቁመዋል።

የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎዛ እንዲያደራድሩ ኢትዮጵያ የጠየቀች መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከሁለት ወራት በፊት በደቡብ አፍሪካ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (/)፣ ይህንኑ የመንግሥታቸውን ፍላጎት ይፋ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በዚህ ወቅት ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይና ፕሬዚዳንት ራማፎዛ ይህንኑ ማረጋገጣቸው ይታወሳል።

የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት በወቅቱ እንደተናገሩት የኢትዮጵያን ጥያቄ መሠረት በማድረግ ከግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህልሲሲ ጋር መነጋገራቸውን፣ ከእሳቸውም በጎ ምላሽ እንዳገኙ ለጋዜጠኞች ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንት ራማፎዛ የአፍሪካብረት ሊቀመንበር ሆነው ለአንድ ዓመት እንዲያገለግሉ በቅርቡ መመረጣቸው ይታወሳል። ፕሬዚዳንቱ በአፍሪካ አኅጉር ያሉ የፖለቲካ ቀውሶችንና ግጭቶቸን ለመፍታት ትኩረት ሰጥተው እንደሚሠሩ የገለጹ ሲሆን፣ሊቢያን ቀውስ ኃያላን አገሮች ጣልቃ ገብተው እያባባሱት እንደሆነ በማውሳት ጉዳዩን ለአፍሪካውያን እንዲተውት አሳስበው ነበር።

ግብፅ በአሁኑ ወቅት የዓረብ አገሮች በዚህ ጉዳይ ላይ አብረዋት እንዲቆሙ ሰፊ የማግባባት ላይ መጠመዷን መረጃዎች ያመለክታሉ። የግብፅ የዘመቻ አካል መሆኑ በይፋ ባይረጋገጥም፣ ጀርመን የአውሮፓ ኅብረት አጋሮቿን በማስተባበር ለግብፅ የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ፣ ግብፅ ደግሞ ለኢትዮጵያ ካሳ እንድትከፍል አዲስ የድርድር ሐሳብ ይዛ መቅረቧ በርካታ ኢትዮጵያዊያንን ከማስገረም አልፎ አስቆጥቷል፡፡ አሜሪካ ድርድር ለማመቻቸት ብላ ቀጥታ ጣልቃ በመግባቷ ኢትዮጵያ ከድርድሩ ማፈግፈጓ አይዘነጋም፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...