Saturday, June 10, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ጥቂት ነጥቦች ስለኮሮና ዓለም አቀፍ ወረርሽኝና የወቅቱ አሳሳቢ ጉዳይ

በሙሉጌታ ሞላ

የዚህ አጭር ጽፍ ዓላማ ስለኮሮና በሽታ ምንነት በጥቂቱ በተለይም የበሽታውን ርጭት ለመግታት መወሰድ ስላለባቸው ነገሮች የቀረበ የግል ምልከታ ነው፡፡ ይህንን ጽፍ በአስተያየት መስጫው ላይ በመግባት ሳብ በመስጠትና ለሌላ ውይይት የሚሆኑ ነጥቦችን በመጠቆም ብናዳብረው መልካም ነው፡፡

ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ምን ማለት ነው?

መንስዔያቸው የታወቀ/ያልታወቀ ከእንስሳ ወደ ሰው ብሎም ከሰው ወደ ሰው በመተላለፍ በአገር/በዓለም ላይ ተራጭቶ በከፍተኛ ሁኔታ ሰዎችን ሊያጠቁ የሚችሉ በሽታዎችን ያጠቃልላል፡፡ እነዚህ በሽታዎች በጣም ገዳይ ናቸው፡፡ ምክንያቱም የበሽታው ባህሪ፣ ርጭት፣ መንስ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ መንገዶች በጊዜው ማወቅ አዳጋች ስለሆነ በጣም ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳሉ፡፡

ስለዚህ የበሽታውን ርጭት ለመቆጣጠር በየአካባቢያችን ያሉትን የጤና ክትትልና ምርመራ ርዓትን ማሳደግ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ በዓለም ላይ ለሚፈጠር ከፍተኛ የበሽታ ርጭት በብዛት ሊያጠቃና ሊጎዳ የሚችለው ታዳጊ አገሮችን ነው፡፡ ምንም እንኳን ደጉ አገሮች ርዳታ ቢያደርጉም በሽታው በእነሱ ላይ ችግር የሚያስከትል ከሆነየራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች’ የሚለው ነገር እነርሱ ጋር አይራም፡፡ ለምሳሌ በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ እንደ ሰደድ እሳት እየተቀጣጠለ ያለውን የኮሮና በሽታ ብናይጣሊያን በዚህ ወቅት ኢትዮጵያን ምታግዝበት ምንም ምክንያት አይኖራትም፡፡ ኛውም የቅርብ ወዳጅ ቢሆን ቤቱን ዘግቶ የራሱን ችግር ለመፍታት ይሞክራል እንጂ ቤቱን እሳት እያጋየው የሌላን ለማጥት አይጓዝም፡፡ እናም በዚህ አስደንጋጭ ጊዜ ማንም እንደማይደርስልን አስበን አስላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ተግቢ ነው፡፡

      ማንኛውም ወረርሽኝ ፈንታ ጣራ ላይ ከደረሰ በኋላ (ከፍተኛ ሞት፣ኢኮኖሚያዊ ቀውስና ማበራዊ ምስቅልቅል አስከትሎ) ነገሮች ወደ ቀደመ ሁኔታቸይመለሳሉ (ወይም በሽታው ይቀንሳል/ይጠፋል)፡፡

ምክንያቱም፦

ሀ) በሽታው በብዛት ከተራጨና ጉዳት ካደረሰ በላ ማበረሰባዊ የበሽታ የመቋቋም አቅም (Herd Immunity) ይፈጥራል፡፡

ለ) በሽተኞች ከሞቱ የመራጨት አቅሙ በእጅጉ ይቀንሳል፡፡

ሐ) ማበረሰባዊ በሽታን የመከላከል መንገዶችን ስንጠቀም (ለምሳሌ፡ ስለ ኮሮና ራስን የማገገሚያ ቦታ በማስቀመጥ፣ እጅ ለእጅ ባለመጨባበጥ፣ ብዙ ሰው በተሰበሰበበት ባለመገኘት፣ ንጽህናን መጠበቅ) በሽታው ይጠፋል፡፡

መ) በዚህ መካከል በሽታው መድኒት ይገኝለታል፡፡ ስለዚህ እኛ የምናደርገው ቅድመ መከላከልና ክምና ዋናው ዓላማ በሽታው የሚያደርሰውን ጉዳት ለመከላከል ሲባል ነው፡፡ ይህ ካልሆነ ግን በገራችን ለረጅም ጊዜ ሊቆይ ይችላል፡፡

የኮሮና በሽታርጭት በጥቂቱ

የኮሮናን አስከፊነትና አሰቃቂነት ለማወቅ በሽታው በስፋትና በጥልቀት የተራጨባቸውን ቦታዎች ማየትና መገንዘብ ጠቃሚ ነው፡፡

በጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ድረ ገጽ እንደተዘገበው (ይህ ጽፍ እስከተጠናረበት ዓርብ ምሽት አንድ ሰዓት ድረስ)፣ በሽታው በዓለም ላይ 25,251 ሰዎች ለሞ ሲዳርግ፣ 558,502 ሰዎችን አጥቅቷል፡፡ ያገገሙት 127,615 ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች 16 ደርሷል፡፡

ይህን መረጃ ከኢትዮጵያ አንፃር ብናየው ማለት በአንድ ኢትዮጵያዊ ቤት በአማካአራት እስከ አምስት ሰው ቢኖር፣ አንድ ሰው ተያዘ ማለት በአንድ የአውቶስ ጉዞ እንበልና ሦስት ሰው ቢያስተላልፍ ይህ ሰው በአንድ ጊዜ የራሱን ቤተሰብ ጨምሮ የ20 እና ከዚያ በላይ ሰው ይወት አደጋ ላይ ይጥላል፡፡ ዚያ በኋላ በሽታው በፍጥነት ያድጋል ማለት ነው፡፡

ስለ በሽታው አስከፊነትና ስለሚያስከትለው ጉዳት በየብዙን መገናኛው ስለሚነገር እዚህ ላይ ገታ አድርገን አንዳንድ የመፍት ሳቦችን እጠቁማለሁ፡፡

በመንግ በኩል መወሰድ ያለባቸው

ሀ. የተወሰኑ ሆስፒታሎችን ለኮሮና ታካሚዎች ብቻ ማድረግ፡፡ ይህ ማለት በአንድ የኦክስጂን ማሽን ላይ ከአራት እስከ አምስት ሰው ተኝቶ በሚታከምባት አገር በሽታው ከመከሰቱ በፊት ለበሽታው ተዘጋጅተናል ማለት ለውስጥ አዋቂዎች (ጤና ባለሙያዎች) እጅግ በጣም አስደንጋጭ ነው፡፡ አንድ የሙት መለኪያ የሌላቸው መኝታ ክፍሎች በእያንዳንዱ ሆስፒታል ብዙ ናቸው፡፡ አቅምን አውቆ በቂ ዝግጅትና ርዳታ መጠየቅ ብልህነት ነው፡፡እውነታውን ማውጣት በገር ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ ስለምናውቅ ቁጥሩን ንገሩን ሳይሆን መፍትው ላይ እንበርታ ለማለት ነው፡፡

ለ. በእነዚህ ሆስፒታሎች ላይ የሙያ ስብጥሩን (diversity of expertise) ማስተካከል፡፡በአንድ ቡድን ውስጥ የኪም፣ ነርስ፣ ኢፒዲሞሎጂስት፣ ብረተሰብ ጤና አጠባበቅ፣ ላብራቶሪና ተያያዥነት ያላቸው ሙያተኞች ቡድን ማዘጋት፡፡

ሐ. አላስፈላጊ ስብሰባዎችን መከልከል አስገዳጅ ከሆነም ከ100 ሰው በላይ አለመሰብሰብ፡፡ ሲሰበሰቡም በ1.5 ሜትር ርቀት ማድረግ፡፡

መ. የበሽታውን ሁኔታ አሳንሶ (underestimate) አለመረዳትና ስለ በሽታው የተዛቡ ትርክቶችን (flawed narratives) ለምሳሌ፦ በሽታው በት መብዛት እንሚመጣ፣ወጣቶችንና ሕፃናትን እንደማያጠቃ፣ ነጮችን ብቻ እንሚያጠቃና በእነሱ የመጣ በሽታ ተድርጎ የሚነገሩ ንግግሮችን ማስተካከል፡፡

ሠ. በደካማ የጤና ርዓት ማለትም መመርመሪያ፣ መታከሚያ፣ የባለሙያ እጥረትና ዝቅተኛ የጤና ግንዛቤ (health literacy) ያለበት ገር ላይ እንደመሆናችን በሽታውን በቀላሉ እንቆጣጠራለን ብሎ አጉል መመካት (overconfidence) አያስፈልግም፡፡

ረ. ኅብረተሰቡ የሚሰጠውን ምር ካልሰማ አስተማሪ ቅጣት መቅጣት፡፡ ለምሳሌ፦በበሽታው ተጠርጥሮ ያመለጠ፣ ሆን ብሎ ያስተላለፈ፣ ራስን ማግለል (self-isolation) ያላደረገ ሰው ላይ አስተማሪ ቅጣት ማስተላለፍ፡፡

ሰ. መንግት ብቻውን ይወጣዋል ብ ስለማላምን ከባለብቶች ጋር በመወያየት አስፈላጊውን ርዳታና ቀድሞ በክምና ለመከላከል የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ማሟላት፡፡

ሸ. የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሚወስነው ውሳኔ እንደ አንድ ግለሰብና የጤና ባለሙያ አስተያየት መስጠት ከባድ ቢሆንም ከአገር ምልክትነት አንር እስካሁን እየራ ያለው ነገር ጥሩ ነው፡፡ ተወደደም ተጠላም ከበሽታ ማምለጥ አስቸጋሪ ስለሆነ አማራጩ አስፈላጊውን ጥንቃቄና መፍት ላይ ማተኮር የተሻለ ነው፡፡ በአገር ኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን በዲፕሎማሲ በኩል እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ ከግምት በማስገባት በረራዎችን እንደየ አስፈላጊነቱ ቢቀጥል መልካም ነው፡፡ ሆኖም ግን አየር መንገዱ ለወደፊቱ ትልቅ ሆስፒታልና የምርምር ማዕከል ከፍቶ በሰማይ ላይ ያለውን ተሞክሮ ወደ ምድር ማምጣት ይጠበቅበታል፡፡

ቀ. የበሽታ ርጭቱ እየከፋ ከሄደ ከአንድ ክልል ወደ ሌላ ክልል መዘዋወርን መከልከል፡፡

በ. የኢትዮ ቴሌኮም የጀመረውን መልካም ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥል ማገዝ፡፡

ተ. በሽታው እየከፋ ሲመጣ በተለይም የተለያዩ ማኅበራዊ ሁነቶች ለምሳሌ፦ ርግ፣ ዘን፣ ልደትና መሰል ጉዳዮች ብረተሰቡ እንዳይሳተፍ መንግት ጠንከር ያለ ትዕዛዝ ማስተላለፍ፡፡

ጤና ባለሙያዎች መወሰድ የሚገባቸው

ሀ. የእናንተን የነ ምግባርና ሞራላዊ ዕሴቶች የሚፈትን በሽታ እንደሆነ ብገነዘብም፣ ቅድሚያ መሰጠት ላለበት ታካሚ ቅድሚያ መስጠት ተገቢ ነው፡፡ የሚመከታቸው ውሳኔ ሰጪ አካላት የቅድሚያ አስጣጥ መመያዎችን ማዘጋጅት፡፡ ይህም ፍትዊ የሆነ የክምና ሳቁስ ርጭት (distributive justice) እና የክምና አሰጣጥ ላይ የሚያስከትለውን ችግር ከመከላከል አንር የጎላ አስጽኦ ይኖረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በጤና ባለሙያዎች ላይ የሞራል ምስቅልቅሎች (ethical dilemma) እና የጥፋተኝነት ስሜት (guilty feeling) እንዳይኖር ያግዛል፡፡ እንዲሁም የጤና ባለሙያዎች የራሳችሁንና የቤተሰቦቻችሁን ጤና መጠበቅ ለምሳሌ የበሽታው ርጭት እስኪንስ ድረስ ራስን ማግለል ብንችል መልካም  ነው፡፡

ለ. ታካሚው ከሆስፒታል አገግሞ (ተሽሎት) ቢወጣም ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ መምከር ተገቢ ነው፡፡

ሐ. በተቻለን አቅም በማበራዊ ብዙን መገናኛዎች የዓለም ጤና ድርጅት፣ የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና አጠባበቅ ኢንስቲትዩት የሚያወጡትን መረጃ በፍጥነት ማራጨት፡፡ በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና አጠባበቅ ኢንስቲትዩት የበሽታውን ርጭትና መጠን በድሜጾታ ያለበትን ደረጃ ከየክልሎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገርና በማሰባሰብ አስፈላጊውን መረጃ በየጊዜውና በፍጥነት ማድረስ፡፡

መ. የድንገተኛ ክፍሎችን በተቻለ መጠን ባለን አቅም ማጠናከርይህ ማለት የማበረሰቡንና የመንግትን ርዳታ በመጠየቅ ማሳካት ይቻላል ብ አምናለሁ፡፡

በሃይማኖት አባቶችች፣ በረሰብ አንቂዎች፣ ፖለቲከኞችና አርቲስቶች

ሀ. ቤተ እምነቶች ከመንግት ጋር በመነጋገር ተራርቆ መኖርን (social distancing) እንዲሁም በግል አምልኮ እንዲያድርጉ ለምእመኑ አስፈላጊውን ርምጃና መልዕክት በየጊዜው እንዲያስተላልፉ ቢደረግ መልካም ነው፡፡

ለ. የበርሰብ አንቂዎች ጊዜን፣ ሁኔታ፣ ችሎታና ሙያን እያገናዘብን ብናወራ መልካም ነው፡፡ ከልክ ያለፈ ቀልድና ቧልት ማበረሰባዊ ቀውስ ስለሚያስከትል አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ተቢ ነው፡፡

ሐ. ፖለቲከኞች ግብር ከፋይ ዜጋ ካጣችሁ የእናንተ የኢኮኖሚ፣ የጤና፣ የፖለቲካና የማበረሰባዊ ፖሊሲዎች  ከንቱ ናቸውና በስምምነት ስብሰባዎች ብታቆሙ መልካም ነው፡፡

መ. የግል ባለብቶች እንደነዚህ ዓይነት ውስብስብ የጤና ችግሮች ሲከሰቱ ማበረሰባዊ ላፊነታችሁን (corporate social responsibility) ጣት አለባችሁ፡፡

ሠ. አርቲስቶችና ታዋቂ ግለሰቦች ስለ በሽታው ቅድመ መከላከያና መተላለፊያ  መንገዶች በኪነ ጥበባዊ መንገዶች ብታስተምሩ መልካም ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ በግል ተነሳሽነት አንዳንድ ታዋቂ ግለሰቦች እያደረጋችሁት ያላችሁት አስተዋጽኦ እያመሰንን ተጠናክሮ ቢቀጥል ናይ ነው፡፡

በማበረሰቡ የሚጠበቅበት

ሀ. ስለበሽታው የማያውቁትን መጠየቅ እንጂ በመሰለኝና ደሳለኝ ወይም በግብዝነት እኔን ወይም እኛን አይዘም ብሎ በሳይንስ የተረጋገጡ (scientific evidence) ጉዳዮችን ወደ ጎን ቸላ ብሎ በአሉባልታዎች (conspiracy theories) እንዲሁም የሰት ወሬዎች (fake news) መጠመድ አደገኛ አካሄድ ስለሆነ ከወዲሁ መቅረፍ ይኖርብናል፡፡

ለ. በረሰባዊ ላፊነትን ከመወጣት አንር የበሽታው ምልክቶች የታዩት ግሰብ ራሱን በለይቶ ማቆያ (quarantine) ውስጥ በማድረግ ወደ ሌሎች እንዳይዛመት ማድረግሆነ ብሎ በሽታው እያለበት ራሱን የማይገልጽን ሰው ለሚመለከታቸው አካላት መጠቆም (social dobbing) አስፈላጊ ነው፡፡

ሐ. ታማሚን በመንከባከብ፣ በማስታመምና ከሞተም በኋላ ባሉ ርዓቶች የሚመለክታቸው አካላት ትዕዛዝና አቅጣጫ መከተል መተግበር ተገቢ ነው፡፡

መ. ስለበሽታው ከመጠን በላይ አለመደናገጥ በተለይም የስግብግብነት ግዥ (panic buying) አለማድረግ አንዳችን ለአንዳችን መተዛዘን ብሎም ከመጠን በላይ ሸቀጦችን በቤት ውስጥ አለማከማቸት (hoard) ይጠበቅብናል፡፡

ሠ. ወደ ገበያ፣ ባንክ፣ መዝናኛ ቦታዎችና የተለያዩ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ስንሄድ ቤተሰብ አለማስከተል፡፡ የተሰብሳቢ ቁጥር መቀነስ ብቻ ሳይሆን አደጋንም ከመቀነስ አኳያ የጎላ አስታዋኦ ይኖረዋል፡፡

ረ. ወጣቶች በየአካባቢያችሁ ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ በቡድን ተድራጅታችሁ እገዛ ለሚፈልጉ የብረተሰብ ክፍሎች (vulnerable groups) ቢውን እንክብካቤና እገዛ ብታደርጉ እንዲሁም በውጭ አገር ዜጎች ላይ ቀለምን መረት ያደረ ጥቃት (racial attack) እንዳይደርስ የበኩላችሁን አስተዋኦ ማረግ አለባችሁ፡፡

“ታሞ ከመማቀቅ አስቅድሞ መጠንቀቅ!!!”

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው  [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡ 

spot_imgspot_img
- Advertisment -

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

Related Articles