Friday, June 2, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ ከሾፌራቸው ጋር እያወሩ ወደ ቢሮ እየሄዱ ነው

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሾፌራቸው ጋር እያወሩ ወደ ቢሮ እየሄዱ ነው]

  • ምን ተሻለ ክቡር ሚኒስትር?
  • ምን?
  • በሽታው ነዋ፡፡
  • እንዴት?
  • እየጨመረ እኮ ነው፡፡
  • መፀለይ ነው የሚያዋጣው፡፡
  • እርስዎ ይፀልያሉ እንዴ?
  • ለምን አልፀልይም?
  • ያው በሥልጣንዎት ነው የሚያምኑት ብዬ ነዋ፡፡
  • የሥልጣናችን ገደብማ ታየ፡፡
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • ይኸው የዓለም ታዋቂ ግለሰቦች ሳይቀር በበሽታው እየተጠቁ እኮ ናቸው፡፡
  • እኔም ዜናውን ሰምቻለሁ፡፡
  • የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ራሱ ከፍተኛ ሕክምና እየተደረገለት እኮ ነው፡፡
  • በአንድ በኩል ግን በሽታው ደስ ይላል፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • ሁላችንም እኩል መሆናችንን አሳየና፡፡
  • እ. . .
  • ክቡር ሚኒስትር በሽታው ጥቁር አይል ነጭ፣ ደሃ አይል ሀብታም ሁሉንም ነዋ የሚይዘው፡፡
  • ተነፈስን እኮ አሁን፡፡
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • በቃ ሥልጣናችንም ገደብ እንዳለው ተረዳና፡፡
  • ምን ያደርጋል ታዲያ?
  • እንዴት?
  • ክቡር ሚኒስትር ለሥልጣን ስትሉ አልነበር እንዴ ሕዝቡን ስትፈጁት የነበረው?
  • መስሎን ነዋ፡፡
  • አሁን ግን አንድ ነገር እየፈራሁ ነው፡፡
  • ምን?
  • ከኮሮናው በላይ ያስፈራኝ እሱ ነው፡፡
  • ምንድነው?
  • ኢኮኖሚው ነዋ፡፡
  • እስኪ እሱን ተወው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር በርካታ ሰዎች እኮ እየተቸገሩ ነው፡፡
  • ገና ካሁኑ?
  • አብዛኛው ሰው የዕለት ጉርስ ፈላጊ መሆኑን አይርሱት፡፡
  • መቼ ጠፋኝ?
  • ጣሊያን ውስጥ የማኅበራዊ ቀውስ ተፈጥሯል አሉ፡፡
  • ለምን?
  • ሕዝቡ የሚበላው አጥቶ ነዋ፡፡
  • ወይ ጣጣ?
  • ክቡር ሚኒስትር እዚህም አገር እንዲህ ዓይነት ቀውስ እንዳይፈጠር መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡
  • ምን ይደረጋል ብለህ ነው?
  • ከአሁኑ መዘጋጀት ነዋ፡፡
  • የምን ዝግጅት ነው?
  • ባለፀጋዎች መዘጋጀት አለባቸው፡፡
  • በምንድነው የሚዘጋጁት?
  • ሀብታቸውን ለማካፈል ነዋ፡፡
  • ይሆናል ብለህ ነው?
  • ካልሆነማ የሚጠብቃቸውን ያዩታል፡፡
  • ምንድነው የሚጠብቃቸው?
  • ሙሉውን ያጡታል!

[ክቡር ሚኒስትሩ አማካሪያቸውን ቢሮ አስጠሩት]

  • አቤት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ይቅርታ አድርግልኝ፡፡
  • ለምኑ ክቡር ሚኒስትር?
  • ታውጇል አይደል እንዴ?
  • የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታወጀ እንዴ?
  • ኧረ የፀሎትና የምልጃ አዋጅ ነው እንጂ፡፡
  • ታዲያ የምን ይቅርታ ነው?
  • በቃ ፈርቻለሁ፡፡
  • ምንድነው የሚያስፈራዎት?
  • ኮሮና ነዋ፡፡
  • ለእሱ እኮ መጠንቀቅ ነው የሚያስፈልገው፡፡
  • እኔ ግን ውስጤ ፍርኃት ፍርኃት እያለኝ ነው፡፡
  • ለምን?
  • ብዙ ወንጀል የሠራሁ ሰው ነኝ እኮ፡፡
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • እዚህ ቦታ ለመድረስ ያላደረግኩት ነገር የለም፡፡
  • ምን አደረጉ?
  • ያደረግኩትን ለማውራት ብጀምር ወራት አይበቁኝም፡፡
  • ይኼን ያህል?
  • አሁን ያስጠራሁህ እኮ ለዚያ ነው፡፡
  • ኑዛዜ ሊያጽፉኝ?
  • ኧረ ይቅርታ ለመጠየቅ፡፡
  • ለምኑ?
  • አንተን ምን ያልሠራሁህ ነገር አለ፡፡
  • ኧረ ምንም አላደረጉኝም፡፡
  • በየቀኑ እኮ ነው የማሴርብህ፡፡
  • እኔ ላይ?
  • እህሳ፡፡
  • ለምን?
  • ብዙ ሚስጥር ስለምታውቅ ነዋ፡፡
  • ቢሆንም እኔም እኮ እርስዎን ለማንም አሳልፌ አልሰጥዎትም፡፡
  • አሁን ግን ኮሮና አሳልፎ ሊሰጠኝ ነው፡፡
  • ለምን ፈሩ ክቡር ሚኒስትር?
  • መተኛት አልቻልኩም፡፡
  • ለምን?
  • በህልሜ ሁሉ ተይዤ ሲያበቃልኝ ነው የማየው፡፡
  • ሞት ይፈራሉ እንዴ?
  • ቆጭቶኝ ነው፡፡
  • ምኑ ነው የቆጨዎት?
  • ለዚችው ነው እንዲያ በሴራ ሕይወቴን የጨረስኩት ብዬ ነዋ፡፡
  • እ. . .
  • ቀን ተሌት ሳሴር ነበር እኮ የማድረው፡፡
  • ይኼን ያህል?
  • እና ይኼን ሁሉ ሀብት ያከማቸሁትስ በዕውቀቴ ይመስልሃል?
  • እሱማ በሥልጣንዎት ነው፡፡
  • እዚህ ለመድረስ የብዙ ሰዎችን ሕይወት አበላሽቻለሁ፡፡
  • አሁን መንቃትዎትም ጥሩ ነው፡፡
  • ስለዚህ ይቅርታ አድርግልኝ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ከእኔ በላይ ይቅርታ መጠየቅ ያለብዎት አካል አለ፡፡
  • ማንን ይቅርታ ልጠይቅ?
  • ሕዝቡን!

[ለክቡር ሚኒስትሩ አንድ ባለሀብት ስልክ ደወለላቸው]

  • ሰላም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ሰላም አለ ብለህ ነው?
  • ቁጥሩ እኮ እያሻቀበ ነው፡፡
  • ምን ይደረግ?
  • ሁሉም ነገር ተዘጋግቷል፡፡
  • ሌላ አማራጭ አጥተን እኮ ነው፡፡
  • ገና ከጅምሩ እንዲህ ከሆነ ወደፊት እንዴት ሊኮን ነው?
  • እኔም ራሱ ጨንቆኛል፡፡
  • ሥራ ለለመደ ሰው ቤት ውስጥ መታሸግ ከባድ ነው፡፡
  • ሥራ ለለመደ አልክ?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • አንተ ስርቆት እንጂ የምን ሥራ ታውቃለህ?
  • እኔ እኮ ስርቆትን እንደ ሥራ ነው የማየው፡፡
  • እንዲያ ከሆነ እንኳን ልክ ነህ፡፡
  • እርስዎም ግን ከእኔ ብዙም አይለዩም፡፡
  • እንዴት ማለት?
  • ያው እዚህ ቦታ የደረሱት ብዙ ግፍ ፈጽመው ነዋ፡፡
  • ለማንኛውም እኔ ያስቀየምኳቸውን ሰዎች እየደወልኩ ይቅርታ እየጠየቅኩ ነው፡፡
  • ፈርተዋል ማለት ነው?
  • ስማ እንደኛ ዓይነቱን እኮ በሽታው ክፉኛ ነው የሚያጠቃው፡፡
  • ለነገሩ እኔም ኑዛዜዬን እየጻፍኩ ነው፡፡
  • ለማን ነው የምትናዘዘው?
  • ለልጆቼ ነዋ፡፡
  • ቀልደኛ ነህ እባክህ፡፡
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የአንተ ሀብት የማን እንደሆነ አታውቅም?
  • የማን ነው?
  • የሕዝቡ ነዋ፡፡
  • መቼም ቀልደኛ ነዎት፡፡
  • የምን ቀልድ ነው?
  • አንድ ነገር ግን ልንገርዎት፡፡
  • ምን?
  • ለካ ሱስ ነው፡፡
  • ምኑ?
  • መስረቅ፡፡
  • እ. . .
  • ይኸው አሁን እየተሰቃየሁ ነው፡፡
  • ማለት?
  • ምን ልስረቅ?
  • እ. . .
  • ቤት ውስጥ ታሽጌ ማለቴ ነው፡፡
  • እኔን እንኳን ያስቸገረኝ ሌላ ሱስ ነው፡፡
  • ምን?
  • እንዲህ ያለ እሱ መኖር እንደማልችል አላውቅም ነበር፡፡
  • የምን ሱስ ነው ያለብዎት?
  • የስብሰባ!

[ለክቡር ሚኒስትሩ አንድ አክቲቪስት ስልክ ደወለላቸው]

  • እስከ መቼ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ምኑ?
  • አገራችን የምትዘጋው፡፡
  • አልገባኝም?
  • ምርጫውንም አስተላለፋችሁት፡፡
  • ሕዝብ ይለቃ ታዲያ?
  • እኛም እኮ ሥራችንን ተቀማን፡፡
  • ማን ነው የቀማችሁ?
  • መንግሥት ነዋ፡፡
  • እንዴት?
  • ሁሉን ነገር ማዘጋት የሚያምረው በእኛ ነበራ፡፡
  • እ. . .
  • ይኸው አሁን መንግሥት ሁሉን ነገር ቆላልፎት ቤት ተቀመጥን፡፡
  • ለነገሩ ሌላ ሥራ ተፈጥሮላችኋል እኮ፡፡
  • የምን ሥራ?
  • ሕዝቡን አካላዊ መራራቅ ላይ ትክክለኛ ግንዛቤ ማስጨበጡ አስቸግሮናል፡፡
  • ምን እያሉኝ ነው?
  • በሽታውን ከሚከላከሉ ተግባራት መካከል አካላዊ ርቀትን መጠበቅ ዋነኛው ነዋ፡፡
  • ስለዚህ?
  • እናንተ ዕርዱን፡፡
  • ምን በማድረግ?
  • ሕዝቡን በማራራቅ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅን የሚተካ ረቂቅ ተዘጋጀ

ከቫት ነፃ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ገደብ ተቀመጠለት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሃያ...

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

አዋሽ ባንክ ለሁሉም ኅብረተሰብ የብድር አገልግሎት የሚያስገኙ ሁለት ክሬዲት ካርዶች ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መንገድ ብድር ማስገኘት...

መንበሩ ካለመወረሱ በስተቀር መፈንቅለ ሲኖዶስ መደረጉን ቤተ ክህነት አስታወቀ

ቅዱስ ሲኖዶስ ከነገ ጀምሮ ውይይት እንደሚጀምር ተነገረ ‹‹እኛ ወታደርም ሆነ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...