Friday, June 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
እኔ የምለዉኮሮና ወረርሽኝና የምግብ ዋስትና

ኮሮና ወረርሽኝና የምግብ ዋስትና

ቀን:

አማረ ተግባሩ (ዶ/ር)

ይህ ጽሑፍ የሮና ወረርሽኝ በለም አቀፍ የኢኮኖሚና ፖለቲካል ሥርዓት ላይ ጥገኛ በሆኑ፣ እንደ ኢትዮጵያ በመሳስሉ የምግብ ዋስትናን፣ ጤናንና ሰላምን ለዝባቸው ማረጋገጥ ባልቻሉ አገሮች ላይ ሊያሳር የሚችለውን ጉዳት ለመዳሰስ ይሞክራል። ይህ ወረርሽኝ ካለፈ በኋላ ለም አቀፋዊ (Globalized) የሆነው የኢኮኖሚ፣ ፖለቲካዊና ማበራዊ ግንኙነት እንዴት ሊቀጥል እንደሚችልና ለእኛ የሚያተርፍልን ተጨማሪ መከራ ይሁን ዕድል ምን ሊሆን እንደሚችል በትክክል ለመተንበይ እንደሚያስቸግር ያስገነዝባል። ይህ ወረርሽኝ አገርና መንግሥት፣ ያል ይሁን ደካማ፣ ብታም ይሁን ደሃ፣ ጥቁር ይሁን ነጭ ወይም ቢጫ ሳይለይና ሳይዘጋጅበት ሁሉንም እኩል ያዳሸቀና ጉዳቱም ሆነ ምስቅልቅሉ በታሪክ አቻ የማይገኝለት መሆኑን እስካሁን የቀረቡት በርካታ ጥናቶች ይናገራሉ። ይ በራሱ አዲስ ይነት ለም አቀፋዊ የአስተሳሰብና አቀራረብ (Paradigm Shift) ለውጥ ያስከትል አያስከትል እንደሆነ አሁንም በትክክል መገመት ባይቻልም። አንደኛው ይነት የአመለካከት ለውጥ ብታም አገሮች ይበልጥ ነጣይና የኔ ብቻ የሚል (Isolationist and Protectionst) ፖሊሲ ምርጫ ሊሆን ይችላል። ሁለተኛው አዲስ ይነት ለም አቀፍ ትብብርን ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ አስፈላጊነቱን የተቀበለ ለም አቀፍ ደንብና ሥርዓት (Global Order) ሊሆን ይችላል። ምን እንደሚከት መገመት ባይታወቅም የምርምር አቅምና ብቃት ያላቸው ወገኖች በዚህ ጉዳይ ላይ መረባረብ ለመጀመራቸው ምልክቶች እየታዩ ነው።

እኛን በሚመለከት አገራችን ለሕዝቦቿ የምግብ ዋስትናን በዘላቂነት ለመቅረፍና በተቻለም የውስጥ ሰላም በማረጋጥና የአካባቢ መረጋጋት በማስፈን  ዝቦቿን ወደ መካከለኛ ገቢ ለማሸጋገር ያልቻለች መሆኗ ሲታሰብ ይህ ወረሽኝ ካለፈ በኋላ የሚከሰተው ለም አቀፍ ሁኔታ ማሳሰቡ አይቀርም። ለኛም ቢሆን ጉዳቱ በድረ ኮሮና ዘመን ጭምር የሚከተለን መሆኑ ሲታሰብና ሌላም ዓይነት ተመሳሳይ ወረርሽኝ ወይም ተፈጥሯዊና ተፈጥሯዊ ያልሆነ መቅሰፍት በድጋሚ ሊከ እንደሚችል ሲገመት በምግብ ራስን ከመቻል አልፎ በግብርና ላይ የተመረኮዘ ብልግናን እንዴት መጎናፍ እንደሚቻል ከአሁኑ መታሰብ ይኖርበታል።

አማራጩም በውል የተመከረበት የረጅም ዘመን መርሐ ግብር በአስቸኳይ መቅረፅ ነው። ይህም አማራጭ ችግር የማይፈታው፣ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋጥ፣ ተመፅዋችነትንና የምግብ ርዳታ ተቀባይነትን የሚያስቀር፣ አገር በቀል የግብርና ምግብ ሥርዓትና ዘላቂ የሆነ የአቅርቦት ሰንሰለት (Resilientdomestic Agri-Food System and Sutainable Supply Chain) መገንባት ነው። ይህንንም አማራጭ በየጊዜው ለውጥ ሊደግበትና ሊስተካከል እንደሚችል አድርጎ አድርጎ መቅረፅ ይቻላል። በዚህ በኩል ሃቀኛ ፍላጎት ካለ ስትራጂውም ውቀቱም በአገራችን እንደሚኖርና እንዳለም አልጠራጠርም። በአጭርና መካከለኛ ዘመን በኤች አይ ቪ ኤድስ ዘመን የነበረውን ልምድ መልሶ በማሰስ፣ በሌሎች አገሮች በዚሁ ኤች አይ ቪ ኤድስና ቦላ ወረርሽኝ ዘመን የምግብ ዋስትናን ከጤናው ዘርፍ ጋር በማቀናጀት ከተገኘው የተሳካ ውጤት ትምህርት መቅሰም እንደሚቻል አምናለሁ። ይህም ትምህርት ምን ሊሆን እንደሚችል በአንድ ግብረ ይል በፍጥነት ለውጤት መብቃት (Fast Track) ቢችል ጠቃሚ እንደሚሆን በመጠቆም ሑፉን እደመድማለሁ። 

የኮሮና ወረርሽኝና ከጤና ችግር ባሻገር ሊያስከትል የሚችለው መዘዝ 

የኮሮና ወረርሽኝ ለማንም ይቅርታ የለሽ ለም አቀፍ  (Global) መቅሰፍት እንደሆነ ምንም ተጨማሪ ማረጋገጫ የማያሻው ነው። ይህም በመሆኑ በለም ዝቦች ጤና ላይ ያከተለው ሰቆቃ ከዚህ በፊት በሰው ልጅ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ እንደሆነ የተባበሩት መንግሥታት የጤና ድርጅትና መንግሥታትም ከዳር እስከ ዳር ተስማምተውበታል። መዘዙ ለም አቀፍ (Global) ኢኮኖሚውንና ማበራዊ ግንኙነቶችን ሁሉ ያመሳቀለና ያስከተለውም ድቀት ገና በድረ ኮሮና ዘመን ጭምር እንደሚዘልቅ ሳይንሳዊ ጥናቶችና ትንበያዎች (Forecast) እየቀረቡ ነው።

ለምሳሌ ያህል እንደ (William A. Kerr (2020) እና (B. James Deaton et al (2020) የመሳሰሉ ታዋቂ ኢኮኖሚስቶች ባቀረቡት ጥናት ይህ ወረርሽኝ  በለም (Global) ኢኮኖሚው ላይ ያደረሰው ምስቅልቅል 2007 እና በ2008 ከደረሰው ግሎባል የፋይናንስ ቀውስና ከሁለተኛው የለም ጦርነት ቀደም ብሎ ከተከሰተው የ1930 ታላቅ የኢኮኖሚ ዝቅጠት (Great Depression) የከፋ ነው ብለውታል። እነሁ ሳይንቲስቶች ከዚህ ቀውስና ኢኮኖሚ ድቀት በኋላ ሊከሰት የሚችለው ለም አቀፍ ሁኔታ ምን ሊሆን እንደሚችል በትክክል ለመገመት እንደሚያስቸግር በቅርቡ ባሳተሟቸው ጥናቶች ገልውታል።

ይህ ቀውስና ከዚህ ጋር ተያይዞ የተከተለው መሸበር እጅግ ፈጣን፣ ሥ የሰደደና ቀውሱም ገና ያላከተመ በመሆኑ መቼ ከዚህ ቀውስ ለመውጣት እንደሚችልና የገበያውም እንቅስቃሴ መልሶ ነፍስ በመዝራት መቼ መስተካከል እንደሚያሳይ ለመተንበይ ጊዜ የሚጠይቅ እንደሆነ ጥናታቸው ያመለክታል። የእነዚህ ሳይንቲስቶች ጥናት በተለይም የግብርና ምርትና ንግድ የህልውናቸው መረት ላደረጉ አገሮች የምግብ ዋስትናን ለዝባቸው ለማረጋገጥ በሚያደርጉት ጥረት ላይ ትልቅ ፈተና እንደሚሆባቸው ግምት ውስጥ እንድናስገባ በቂ መንደርደሪያ ይሰጣል። ከዚህ በታች የማቀርባቸው ምልከታዎቼ በእነዚህና ሌሎችም ጥናቶች ላይ መረት ያድረገ ሲሆኑ ችግሩ ከጤና ችግር ዘልቆ የሚሄድ መሆኑን አስረግጣለሁ። ይህ ወረርሽኝ በተናጠል የማይታይ፣ ግዙፍና ውስብስብ (Compounded) ከሆነው የምግብ ዋስትና ችግር ጋር የተገናኘ በመሆኑ በግብርና ምርምርና ልማት ውቀትና ልምድ ያላቸውን የአገራችንን ኢኮኖሚስቶችን፣ የሥነ መንግ ሥርዓት ፆታና ፖሊሲ አማካሪዎችን፣ የምግብ ሳይንስ ቴክኖሎጂና የምርትና ድረ ምርት  ባለሙያዎችን (Food Science Technology & Postharvest Specialists) ገዛ ይጠይቃል። ስለዚህም በዚህ ውይይት ውስጥ በመሳተፍ ያቅማቸውን ያበረክታሉ ብ ተስፋ አደርጋለሁ። 

የኮሮኖ ወረረሽኝ በድንገት የተከሰተ መቅሰፍት መሆኑ እንዳለ ሆኖ እንደ ኢትዮጵያ የመሳሰሉ የምግብ ዋስትናን ሊያረጋግጡ ያልቻሉና የውጭ ምንዛሪያቸውን የምግብ ሸቀጦችን ወደ አገር በማስገባት ለም አቀፍ የእርሻ ንግድና የምግብ አቅርቦት ሰንሰለታዊ ርዓት ላይ ጥገኛ (Agriculture Trade and Food Supply Chain Depenedent) የሆኑ አገሮች ላይ ባጭርና ረጅም ጊዜ የሚያስከትልባቸው ጉዳትና ምስቅልቅል ቀላል አይሆንም። ከዚህ የተነሳ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ለመሳሰሉ አገሮች ከውጭ በግዥ መልክ የግብርናና ምግብ ነክ ሸቀጦችን ለሚያስገቡ አገሮች ለተጨማሪ ችግር በማጋለጥ ይብሱን ወደ ፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ሰላም መደፍረስና ግጭት ሊጋብዝባቸው ይቻላል። ዘርዘር አድርገን እንመልከተው ያልን እንደሆነ በኮሮና ወረርሽኝ ሳቢያና ርጭቱንም ለመግታት አገሮች በሰዎችና የሸቀጦች ዝውውርና የንግድ ልውውጥ ላይ ከፍተኛ ቁጥጥርና ማዕቀብ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። የራሷ የባህር በር የሌላት አገር አብዛኛውን የውጭ ንግዷን በአየር የምታጓጉዝ እንደ ኢትዮጵያ የመሰለችን አገር ከውጭ ንግድ ይገኝ የነበረውን ገቢ እጅግ አድርጎ ማዳከሙ የማይቀር ነው። በዚህ ሳያበቃ እስከ ዛሬ የእኛን የግብርና ምርት ሲቀበሉ የነበሩ አገሮች የቫይረሱን ርጭት ለመግታት በሚል እጅግ የተወሳሰና ለሟሟላት የሚከብድ የቁጥጥር መመዘኛ እንድናሟላ ሊያስገድዱን ይችላሉ።

አልፎ ተርፎም የምግብ ጥራትንና ደንነትን (Quality and Safety)  የሚመለከቱ አዳዲስ የቁጥጥር ሥርዓቶችን በማውጣት የውስጥ ገበያቸውን በእኛ ላይ ለመዝጋት አይመለሱ ይሆናል። ወደ ውጭ የምንልካቸው አብዛኞቹ የግብርና ምርቶቻችን ጥራትና ደረጃን በመጠበቅ በኩል የተዋጣልን እንዳልሆነ የታወቀ ነው። በለም ገበያም ተፎካካሪ በመሆን ብቃት የጎደላቸው በመሆኑ በገቢ ደረጃ የማሽቆልቆል ችግር እንዳለብን የአደባባይ ሚስጥር ነው። እኛም በበኩላችን የውጭ ምንዛሪ እየተከፈለባቸው ወደ አገራችን በሚገቡት የምግብ ምርቶች፣ ስንዴም ይሁን በቆሎ፣ አኩሪ አተርም ይሁን የምግብ ዘይት ወይም የቆሮቆና የታጉ አትክልትና ፍራፍሬዎች በተመሳሳይ መንገድ ጥራታቸውን (Standaradized Food Safety Regulation and Product Sepcification) በመመርመር አስተማማኝ ባልሆኑት ላይ ገዳ እናድርግ ብንል እነሁ ምግብ ነክ ምርቶቻቸውን ማራገፊያ ያደጉን አገሮች ሊበቀሉን ይችላሉ።

ሌሎች የእኛ የግብርና ምርት ተፎካካሪ ሊሆኑ የሚችሉ ምርቶችን ከውጭ ለማስገባትም ሆነ በአገር ውስጥ ለማምረት የሚችሉበትን ታሳቢ ቢያደርጉ በለም አቀፍ የእርሻ ንግድና የምግብ አቅርቦት ሰንሰለታዊ ርዓት (Global Agricultre Trade and Food Supply Chain) ላይ ያለን ጥገኝነት (Dependency) ያመጣብን መዘዝ ነውና ጥገኛነታችንን ሳንወድ በግድ ተቀብለን እንድንቀጥል ልንገደድ እንችላለን። ይህ ብቻ ሳይሆን በፖሊሲ ደረጃ ወዳገር እንዳይገቡ የታገዱት የዘር ውርስ ይዘታቸው የተለወጡ አዝርዕት (GEMO Crops) በእጅ አዙር በታሸጉ ምግቦች በኩል ወደ አገራችን ከመግባት የሚቆጣጠርና የሚያግድ ምንም ጉልበት ባለመኖሩ ሌሎችም የዘር ውርስ ይዘታቸውን እንደ ልብ ለማድረግ የተለወጡ (Gene Manipulated) እንደ ንጅብል፣ ቀይና ነጭ ሽንክርት፣ ስንዴ፣ በቆሎና አኩሪ አተር በገበያው በሰፊው ለመገኘታቸው ወይም ላለመገኘታቸው የግብርና ምርምር ባለልጣኖች ለማረጋገጥም ለማስተባበልም እንዳይችሉ ሊገደዱ ይችላሉ።

አማራጫችን ችግር የማይፈታው (Resilient) የሆነ አገር በቀል የምግብ አቅርቦት ሰንሰለታዊ ርዓት (Domestic agri-food System and Sutainable Supply Chain) መገንባት ነው በሚለው መስማማት ችግር የለውም። ይህንን ለማድረግ ግን የግድ ከኮሮና በአገራችን ከመከሰቱ በፊት የምግብ ዋስትና በተመለከተ የምንገኝበትን ሁኔታ በሚገባ መረዳት ይኖርብናል። አለበለዚያ የአጭርና መካከለኛ ዘመን የመፍት ሳቦች የሚባሉትን ለማቅረብና ከረጅሙ ስትራትጂ አካል ጋር አገናዝቦ ያሰቡት ግብ ለመድረስ ያስቸግራል። 

በአገራችን የምግብ ዋስትና ምን ላይ ይገኝ ይሆን?

የምግብ ዋስትናን በሚመለከት የምንገኝበት  ሁኔታ ምን ይመስላል ወደሚለው ጉዳይ ከማለፌ በፊት ኢትዮጵያ ከውጭ በምታስገባው የምግብ ምርት ምን ያህል ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እንደምታጠፋ ማውሳት ያስፈልጋል። ይህንንም በማስላት አገራችን ከውጭ በሚገቡ የምግብ ሸቀጦች ላይ ምን ያህል ጥገኛ እንደሆነች መገንዘብ ያስችላል። ይህም ጥገኝነት የዝቧ ቁጥር በአደገ መጠን እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ ለመሄዱ ምንም ምልክት እንደማይታይ ጥናቶች አጣቅሶ ማለፍ ያስፈልጋል። በ2015 ብቻ 1.8 ቢዮን ዶላር የተደረገ ሲሆን ከዚህም መካል አብዛኛውን ድርሻ የያዙት የስንዴና በቆሎ፣ የምግብ ዘይት፣ ስኳር፣ እንደ ፓስታና ማኮርኒ የመሳሰሉ የስንዴ ምርት ውጤቶች፣ አኩሪ አተርና፣ አተር። ይገኙበታል። በ2016 ደግሞ ከአገሪቱ ባጀት 8.4 በመቶ የውጭ ምግብ ለመግዛት ወጭ ተደርጓል (www.kneoma.com) በ2019 አተር ከውጭ ለመግዛት 53 ሚሊዮን ዶላር ሆኗል። ይህ አንግዲህ አገሪቱ በየ ዓመቱ ከምታገኘው 20 ሚሊዮን ዶላር ሚጠጋ ተጨማሪ የምግብ ርዳታን ሳይጨመር ነው። የዚህ ጥናት አቀናባሪዎች ወደ ፊትም አገሪቱ ከውጭ ለምታስገባው የምግብ ሸቀጥ በውጭ ምንዛሪ የምታወጣው ክፍያ እየጨመረና የውጭ ምንዛሪዋን እያራቆተና ይበልጡን ዕዳ ውስጥ እየጨመራት እንደሚሄድ ያትታሉ። ከዚህም የተነሳ አገራችን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የዋጋ ግሽበትን ለመግታት አስቸጋሪ እንደሚሆንባትና ይህ ደግሞ ‹‹ንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ በመሆን›› ወደ ከፋ የፖለቲካ ትርምስና ግጭት ሊያስገባት እንደሚችል መረዳት አያስቸግርም። 

በያዝነው እ.ኤ.አ. 2020 ማለትም የኮሮና ወረርሽኝ በአገራችን ከመግባቱ ቀደም ብሎ የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ድርጅት አንድ ሪፖርት ይፋ አድርጓል። በዚህ ሪፖርት መረት በ2019 ከለም እጅግ የከፋ የምግብ ዋስትና ችግር ያለባቸው ተብለው ከተዘረዘሩት አሥር አገሮች መካከል አገራችን ኢትዮጵያ አንዷ ሆና ተመዝግባለች። ከአፍሪካ ደግሞ ከደቡብ ሱዳንና ሞክራቲክ ሪብሊክ ኮንጎ ጋር በተርታ ተቀምጣለች (2020:93-96)። በዚሁ ሪፖርት (WFP 2020) እንደተገለጸው ምንም አንኳን ኢትዮጵያ ባለፉት ሃያ መታት በኢኮኖሚው መስክ ዕድገት ያሳየችና ይህም ልማቷን ለማፋጠን አጋዥ ይሆናል ተብሎ ቢገመትም አሁንም ከዝቡ 27 በመቶ ማለትም 30.2 ሚሊዮን ዝብ ከድህነት ወለል (አንድ ዶላር በቀን) በታች ይገኛል። ከ70 በመቶ በላይ በገጠር የሚኖረው ዝብ ለበርካታ ይነት የድህነት መለኪያዎች (Multidimensional Poverty Index) የተጋለጠ ሲሆን በተደጋጋሚ በሚከት ድርቅ ለዘር ያስቀመጠውን በልቶ የጨረሰ፣ አርሶም ሆነ አርብቶ ለማደር የቋጠረው ቅርስ የወደመበትና የተሻለ አየር ንብረት ለውጥ እንኳን ቢያጋጥም ከተረጂነት ተላቆና አገግሞ በቶሎ አምራች ለመሆን የማይችል እንደሆነ በሌላም ተጨማሪ ጥናት ተዘክሯል (See OPHI, September 2019)። 

የተባሩት መንግሥታት የምግብ ድርጅት (WFP, January 2020) ሪፖርት  እንደሚለው ከሆነ የምግብ ዋስትና አለመረጋገጥራ አጥ (በተለይም የወጣት ራ አጥ ቁጥር) ሊቀረፍ ባለመቻሉ በየክልሉ፣ ወረዳ፣ ዞንና መንደር የሚታየው የርስ በርስ ግጭት ሊያባስ ይችላል። በሌላ በኩል የተባሩት መንግሥታት ርዳታ ማተባሪያ ድርጅት (United Nations Office for the Coordination of Humanitarina Affairs) ባወጣው ሪፖርት ከመንግሥት ቁጥጥር ው በነፃ የሚንቀሳቀሱ በርካታ የታጠቁ ይሎች ለአዳዲስ መፈናቀሎች ምክንያት በመሆናቸው በሰው ይወት ላይ ከሚደርሰው ሰቆቃ ባሻገር ከግብርናው ዘርፍ ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው ምርት ጨርሶ እንዲያሽቆልቁልና የገበያው ሥርዓት የባሰ ቀውስ ውስጥ በማስገባት የምግብ ዋስትናው ላይ ከባድ ጫና በመፍጠር ለመንግሥት ተጨማሪ ችግር እንደሆበት ያትታል (OCHA, 2020)። በዚሁ ድርጅት ሪፖርት ከ1.6 ሚልዮን በላይ ከሚሆነው ተፈናቃይ መካከል ከሁለት እስከ ሦስት የሚሆነው የተፈናቀለው በብርና ብረሰብ መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት ሲሆን ይህን የመሰለው መፈናቀል ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰበት ከጥር እስከ መጋቢት ወር 2019 ድረስ ያለውን ቁጥር ይዘን በድርቅና አየር ንብረት ለጥ ምክንያት ከተፈናቀለው ጋር ስናዳምረው ከ3.2 ሚልዮን ይደርሳል (OCHA, 2020)። በዚህ ኮሮና ወረሽኝ ጊዜ የተባሩት መንግሥታት ርዳታ ተባሪያ ድርጅትም ሆነ ሌሎች ለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች እንቅስቃሴያቸው በተገታበትና ምናልባትም ባጀታቸውን ወደ ጤናው ዘርፍ ለማዞር በሚገደዱበት ሰት ይህንን ያህል ቁጥር ያለው ዝብ ለተደራራቢ የምግብ ዋስትናና ለተወሳሰበ የጤና ችግር እንደሚጋለጥ አያጠራጥርም።

በያዝነው 2012 ዓ.ም. (በፈረንጅ 2020) ከጥር እስከ መጋቢት ወር ባለው ብቻ የበቆሎ ዋጋ በ30 እስከ 65 በመቶ መጨመሩን የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ድርጅት ሪፖርት ይናገራል (FAO-GIEWS, December 2019)።  በጥቅምት ወር ብቻ በተለይ በአዲስ አበባና በሌሎችም የክልል ከተሞች  የጥራ ጥሬ ህል በተለይም የጤፍ፣ ስንዴና ማሽላ የመሳሰሉት ዋጋቸው ከ40 በመቶ በላይ መጨመሩን ጥናቱ ያሳያል (FAO-GIEWS, December 2019)። ይህ የዋጋ ግሽበት በተለይም በአዲስ አበባና በሌሎችም የክልል ከተሞች መታየቱ የብርን የመግዛት አቅም ዝቅ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በተለይም እንደ ነዳጅ፣ ለግብርና የሚያስፈልጉት ግብዓቶችና ትራንስፖርት ወ. ላይ የታየው ትልቅ የዋጋ ጭማሪ ጋትንና መፍጠሩ እንማይቀር ጥናቱ ይጠቁማል። 

መንግሥት የአገር ውስጥና የውጭ የግል ባለብቶች በግብርናው ዘርፍ በመማራት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንዲጫወቱ ሁኔታዎችን አመቻችቶ እንደነበር በሰፊው ስገር እንደነበር እናስታውሳለን። ደን እየተመነጠረና  ዝብ በማፈናቀል ለውጭ ባለብቶች ሰፋፊ እርሻ ማስፋፊያ ተችሮ ነበር። ውጤቱ ግን ያ የተመነጠረውና ለሰፋፊ የግል እርሻ የተዘጋጀው መሬት አገሪቱ ከውጭ የምታስገባውን ምግብ ለመቀነስና የምታርተውንና ወደ ውጭ የምትልከውን በጥራትና በብዛት በማምረት የውጭ ምንዛሪ የምታገኝበት ላይ ያተኮረ ንዳልነበረ ይታወቃል።

እነህ የውጭ ባለ ብቶች ያመረቱትና ለማምረትም የተጣደፉበት የውጭ ገበያ የሚፈልገውንና ላፈሰሱት መዋዕለ ንዋይ በለም ገበያ በአጭር ጊዜ ከፍተኛ ትርፍ አግኝተው፣ ደናችንን ጨፍጭፈው፣ ለዝብ መፈናቀል ምክንያት ሆነው፣ የመሬታችንን ምርታማነት ውድመው፣ የው ብታችንን መርዘውና በእነዚህ ከፍተኛ እርሻዎች ላይ ተቀጥረው በሚሠሩ ወንድና ሴት የዘመናዊ እርሻ ራተኞች ላይ የጤና ቀውስ ፈጥረው፣ ከግብር ነፃ ላስገቡት ንብረት ማንም ሳይጠይቃቸው ከአገር መልቀቃቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው። በምግብ ዋስትና ላይ እንኳን የምርት እንቅስቃሴ የነበራቸውም ቢኖሩም ለምን ያህል ጊዜ እንዳመረቱ መረጃው የለም።

እነህም ባለብቶች ይዘውት ወደ አገራችን የገቡት ‘ምርጥ ዘር’ ምን ያህል በበቂ የተመረመረና ለአገራችንና ለአካባቢው ሥነ ምዳር (Agroecological System) የሚስማማ ወይም የማይስማማ መሆኑ ምንም መረጃ ሳይቀርብበት የተቸረው መሬት እንዳለ ምድረ በዳ ሆኖ ቀርቷል።  ይህን ስናይ በመንግሥት በኩል የምግብ ዋስትናን ለማረገጋጥና ከምግብ አስመጭነትና ተመፅዋችነት ለመገላልገል በሚል የሚጀመረው ሁሉ ዳር ሳይደርስ ተሰናክሎ የሚቀርበት ምክንያት እጅግ የበዛ መሆኑን ያመለክታል። ከዚህ የተነሳ ዘላቂና የአርሶ አደሩን ጥያቄ የታሟላ መር ግብር ተቀርፆ አርሶ አደሩ ያለበት ድረስ ሄዶ ተግባራዊ ማድረግም መከታተሉም ቀላል አይሆንም።

አገራዊ መቆርቆር፣ ቀኝነቱ፣ ግልነቱና የሚያስፈልገው ግብት ተስተካክሎና ተቀናብሮ ከቀረበ፣ ብቃቱና ልምዱ ባላቸው የአገራችን ሙያተኞችና አዋቂዎች ከተራ በግብርናው መስክ ወደፊት የሚማሩ የውጭ ባለብቶች በምግብ ዋስትና ላይ ያተኮረ፣ የተፈጥሮ ብት እንክብካቤ ላይ ያተኮረ ራ እንዲሩ ማድረግ  የማይቻልበት ምንም ምክንያት የለም።  የተባበሩት መንግታት የምግብ ድርጅት ሪፖርት የሚለውን ተከትለን በአገራችን የሚጠበቀው ምርት በአየር ንብረት መለወጥም ሆነ በተባይና አንበጣ መንጋ ምንም ጉዳት ሳያገኘው ይሰበሰባል እንኳን ብንል የኮሮና ወረርሽኙን ርጭት ለመከላከል ሲባል የሰዎችንም ሆነ ምርትን ከቦታ ቦታ የማመላለስ ገዳ ለአጭር ጊዜ ቢሆን መኖሩ በምግብ አቅርቦትና ዋስትና ላይ ትልቅ ጫና መፈጠሩ አይቀርም። ምርት በጊዜው ወደ ገበያ በመውጣት ለሸማቹ ዝብ ሳይደርስ ከቀረ በቀላሉ ሊበሰብስና ሊበላሽ እንደሚችል ሲታወቅ በዚህ በኩል ይበልጥ ተጎጂ የምርት ይነቶች መካከል እንደ አትክልትና ፍራፍሬ ይገኙበታል። ይህ ደግሞ ሸማቹን ብቻ ሳይሆን በተለይም አማራጭ የሌለውን አምራች ገበሬ እጅግ አድርጎ ይጎዳል። ይህ ሁሉ ከምግብ አቅርቦት እጥረት ጋር ተያይዞ ገበያውን የሚያሸር ሁኔታ ስለሚያስከትል የሽሚያ ሸመታን ሊያባብስና የዋጋ ግሽበትን ሊያግዝ  አልፎ ተርፎም ለግጭትና አመፅ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ስለዚህም የኮሮና ወረርሽኝን ተፅዕኖ ከምግብ ዋስትና ምንነትና በርካታ ገታዎች እንዲሁም ከሰላምና ግጭት ጋር ያለውን ተያያዥነት አበክሮ መመልከት ይጠይቃል። 

ትኩረታችን ምንና ማን ላይ መሆን እንዳለበት መወያያ ይሆን ዘንድ

 በዚህ በኮሮና ወረርሽኝና በድሮና ዘመንም ትኩረት ሊሰጥባቸው የሚገባ ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው? ይበልጥ ተጠቂና ተጋላጮቹስ እነማን ናቸው? እነህን ጥያቄዎች ማብላላትና ሳብ መስጠት ተገቢ ነው። ከፍ ብዬ እንዳመለከትኩት ይህ ወረርሽኝ ያስተለው ቀውስና የፈጠረው መሸበር ገና አላከተመም። ስለሆነም  በአጠቃላይ በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ታችን ላይ እስካሁን ያደረሰውንና ወደፊትም ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመገመት ያስቸግራል። ይህም ሆኖ ከችግሩ እንደምንም አገግሞ ለመውጣት በየጊዜው ጥናትና ክትትል ይጠይቃል። ለዚህም አጠቃላይ ሁኔታውን በመገምገም አቅጣጫ ሊጠቁምና በየጊዜው ሊከለስ የሚችል ስትራጂ ወይም አንደ ይነት ፍኖተ ካርታ ማሰብ የሚያስፈልግ ይመስለኛል። 

እስካሁን የኮና ወረርሽኝን በተመለከተ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በኩል የሚሰጠው ገለ ችግሩን ከጤና አንፃር ብቻ የሚመለከት ነው። ስንት ሰው የቫይረሱ ተጠቂ እንደሆነ፣ ስንቱ ከጥቃቱ እንዳገገመና ጨርሶ እንደተሻለውና ስንት ሰው ይወቱ እንዳለፈ በማሳወቅ ላይ ያተኮረ በመሆኑ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በአዋጅ የተሰጠውን የላፊነት ድርሻ ለመወጣት በመድከም ላይ እንደሚገኝ ያስረዳል። ይህ እንዳለ ሆኖ በአገራችን 57 በመቶ ወይም ደግሞ ከ110 ሚሊዮን ዝብ መካከል 62.7 በመቶዮኑ ብቻ ንፅህናውን ለመጠበቅና ለመዳዳት Access (IFRC, July 2019) እንዳለው በጥናት የተደረሰበት ሃቅ ነው። ባለፈው መጋቢት እስከ ታሳስ 2019 (April – December 2019) የኮሌራ በሽታ በአገራችን ጥቃት ማድረሱ ይታወሳል። የመኖርያ ቤት እጥረትና መተፋፈግ ብዙም መሻሻል ባላሳየበት አገር አካላዊ ርቀትን ጠብቆ ለመኖርም ሆነ ይህንን አዲስ ማበራዊና ባህላዊ የአኗኗር ዘይቤ ተቀብሎና ተከላክሎ ውጤት ማስመዝገብ ፈታኝ እንደሆነ መቀበል የግድ ነው።

በአንድ በኩል የዜጎችን በዚህ ወረርሽኝ ከጥቃትና ሞት ለመጠበቅና በሌላ በኩል ደግሞ ከምግብ አቅርቦት እጥረትና ዋጋ ሽቅበት ጋር ተያይዞ በከተማና በገጠር ሊከት የሚችለውን ረሃብ ለመከላከል መንግት ሚዛን ጠብቆ ያለውን ጥሪት (Resource) ለጤናውም ለምግብ አቅርቦትም ለማዳረስ እጅግ ከባድ እንደሚሆንበት መገንዘብ ተገቢ ነው። በዚህ ድንገተኛና አስቸጋሪ ወቅት መንግሥትና ዜጎች ተደማምጠውና ተቀናጅተው በጋራ በመለፍ ለዚህ አገራዊ ጉዳይ ቅድሚያ መስጠት ይኖርባቸዋል። የምግብ ዋስትና ማለት በርካታ ገታዎች (Multiple Indicators) ያሉት መሆኑን በመረዳት እንደ በአገር ደረጃ የተቀናጀ ከኢኮኖሚስት፣ ሥነ መንግትና ፖሊሲ፣ የግብርና ምርምርና ኤክስቴንሽን፣ ከሥርዓተ ታ ወጣቶች ጉዳይ እስከ ምግብ ጥናት ምርምርና ዝግጅት (Nutrition and Food Science Tecknologists) ድረስ ያሉትን የዕውቀት ዘርፎች (Multidisciplinary) ያቀናጀ፣ ለሁሉም እኩል ድል የሚሰጥና የሚያዳምጥ፣ ለዝብ መድረስ ያለበትንም መልዕክት በዝብ ቋንቋ ለማድረስ የሚችል መድረክ መፈጠር ይኖርበታል።

ይህ የተቀናጀ ክህሎት (Expert Capacity) በአገራችን የወረርሽኙ ሙሉ ምን ሊሆን እንደሚችል በትክክል ማወቅ እንኳን ባይችል አቅጣጫ ሊጠቁም የሚችል ፍኖተ  ካርታ መቅረፅ ይችላል። ከዚያም ባሻገር የፕሮጄክት ንድፈ ሳብ ለማቅረብና ለዚህም የሚሆን ግብዓትና ብት ማሰባሰብ እንዲቻል (Resource Mobilization) አመራር መስጠ ይችላል። በዚህ ወረርሽኝ ሁሉም የአገራችን ብረተሰብ ክፍሎች አንድ ወጥ በሆነ መንገድም ባይሆን በሰፊው እንደተጠቁ አያጠራጥርም ለምሳሌ ያህል መካከለኛ ገቢ ያለውንና የምግብ ዋስትና ችግር የሌለበትን ብረተሰብ ክፍል የወሰድን እንደሆነ ይህም ክፍል ቢሆን ምናልባት ለጥቂት ወራት ወይም ዓመት ጉዳቱ ላይ ሰማው ይችል ይሆናል። ምግብ ነክ ባልሆኑና ቅንጦት ጋር በተያያዙ ሸቀጦች ላይ ያወጣ የነበረውን ወደ ምግብ በማዞርና ገቢውን በማብቃቃት ይበልጥ ተጠቂና ተጋላጭነቱን ሊቀንስና ይህ ክፉ ጊዜ እስኪያልፍ እንደምንም አገግሞ ለመውጣት ዕድል ይኖረው ይሆናል። የዚያኑ ያህል ደግሞ በተለያየ ንግድ፣ ሆቴልና ቱሪዝም፣ ትራንስፖርት፣ ጅምላና ችርቻሮ፣ የግምባታና ጥገና፣ ባህልና ኪነት ነክ ሙያ ላይ የተማሩትን ወደ ኪሳራና ሥራ አጥነት ሊከታቸው እንደሚችል መገመት ይቻላል። 

በትምህርት ቤቶችና ሆስፒታሎችም አካባቢ የምግብ እጥረት መኖሩ አይቀርም። በተለይ እናትና አባት የሌላቸውንና የአካልም ሆነ የአዕምሮ ዝግመት ያለባቸውን ልጆች በነፃ ሰብስበው በሚያሳድጉና በሚያስተምሩ፣ ለአቅመ ደካማና ሰብሳቢ ለሌላቸው ወገኖች የዕለት ጉርስና መጠጊያ ያቀርቡ የነበሩ ከትንሽ እስከ ትልቅ የሚደርሱ ተቋማት የዚህ ወረርሽኝ ተጋላጭና በላፊነት የተረከቧቸውን ለመንከባብ የማይችሉት ደረጃ ላይ እንደሚደርሱ ከግምት ውስጥ ማስገባት ይቻላል። በተለይ የአገር ውስጥና የውጭ ግብረ ናይ ድርጅቶች ለመንቀሳቀስም ሆነ ርዳታ ለማድረስ የሚገቱ መሆናቸውና ባጀታቸውንም ወደ ጤናው መስክ በማዞር  ወረርሽኙ እንዳይዛመት ለመከላከል መጠቀማቸው እንደማይቀር መገመት አያዳግትም።

ከዚህ የተነሳ ይህ ትልቅ ሰብዓዊና ማብራዊ ላፊነት የወሰደው ተቋምና ተጠቃሚዎቹ የአገራችን ዜጎች እጅ አድርገው እንደሚጎዱና ምናልባትም ተቋማቱን በመዝጋት እነህ ቀድሞውንም የተገፉ ዜጎች የጎዳና ተዳዳሪ ሊሆኑ እንደሚችሉ ማሰብ አያስቸግርም። በእኔ አስተያየትና እምነት የመንግሥት ትኩርት መሆን አለበት ብዬ የምለው ከዚህ በላይ ያነሳኋቸውን የበረተሰብ ክፍል ጨምሮ በተለይ በከተማም በገጠርም የተረሱ፣ የተገፉና የተፈናቀሉ፣ የምግብ  ጦት በሚያስትለው  የጤና እክል በቀላሉ ለሚተላለፍና ክሮኒክ ለሆነ ተላላፊ በሽታና  የተመጣጠነ ምግብ ጦት (Malnutrition) የተጋለጡት ላይ ነው።

እነ ከላይ የጠቀስኳቸውን ዜጎች ከመጀመያውም የረጅም ዘመን ረሃብተኞች ናቸው። ቀደምም ሲል ከፍተኛ የልሚ ንጥረ ነገሮች እጥረት የተጋለጡ በመሆናቸው ከኮሮና ወረርሽኝም ዘመን በፊት ወደ ጤና ጣቢያዎች በመሄድ አስፈላጊውን ክትትል ለማግኘት ዕድል ያላገኙ ናቸው። በዚህ በኮሮናና ረ ኮርና ዘመን ወንዶችም ሴቶችም እኩል ተጠቂ ቢሆኑም ለተደራረበ ጥቃት የሚጋለጡት ሴቶች፣ ፃናት፣ በእርግዝና ላይ ያሉ ወይም የሚያጠቡ ደሃ እናቶችና አቅመ ደካማ አዛውንት ስለሆኑ መንግትና ሌሎችም ባለ ድርሻ አካላት እነህ ዜጎች ላይ ትኩረት መስጠት ይኖርባቸዋል። ከፍ ብዬ ባመለከትኳቸው ተጋላጭ የብረተብ ክፍል አባላት ላይ ትኩረት መስጠት ሌሎች ዜጎችን መዘንጋት ማለት አይደለም።

ከኮሮና ወረርሽን ቀደም ብሎ ከድህነት ወለል በላይ (Above the Poverty Line) የሚገኘውም ቢሆን የወረርሽኙ መዘዝ ር እየሰደደና ጠቅላላ የኢኮኖሚው እንቅስቃሴ መልሶ ነፍስ ለመዝራትና ለማንሰራራት የተራዘም ጊዜ በወሰደ ቁጥር ይህ ከፍ ብዬ የጠቀስኩትም ኅብረተሰብ ክፍል ወደ ድህነት አዘቅት መውረዱ በምግብና ጤና ዋስትናም ክፉኛ የተጎዳውን ክፍል መቀላቀሉ አይቀርም። በሌላ አነጋገር በቀጥታ አምራች ባይሆኑም በምርት አካባቢ የሚገኙ፣ በጅምላም ሆነ  ችርቻሮ ንግድ ላይ የተማሩ፣ ተቀጥረውም ሆነ ለራሳቸው ጥረው የሚኖሩ፣ ከኑሮ ውድነት የተነሳ ከእጅ ወዳፍ ካልሆነ በስተቀር ምንም የማይተርፋቸው የኅብረተብ ክፍሎች የኮሮና ወረርሽኝ ባስከተለው ጉዳት በቀላሉ ወደ ድህነትና ጉስቁልና ሊወርዱ ይችላሉ።

ዝቡ ቁጥር ወደ 60 በመቶ የሚጠጋውንና በራ ፈጠራ ዕድል ተጠቅሞ አምራች ዜጋ ለመሆን ዕድል ያላገኘውን ወጣት ጉዳይ በተለይም በዚህ በኮሮና ወረርሽኝ ዘመን በሚገባ መጤን አለበት። ማስታገሻው ሊገኝለት ካልቻለበማንኛውም ጊዜ እንደሚፈነዳ የተጠመደ ቦምብ ማለት እንደሆነ ግል ነው።  ስለሆነም አንዳንድ አገሮች ለወጣቱ ራ መፍጠር ብቻ ሳይሆን ወጣቱ ራሱ የራሱ ራ ፈጣሪ እንዲሆን ለማስቻል የዱበትን ጎዳና በመርመር ለአገራችን እንዲመች አድርጎ መቅረፅ ይጠይቃል። የግብርናው መስክ ብቻውን የወጣቱን ሥራ አጥነት ሊያቃልል ይችላል የሚለው ግምት (Assumption) በሚገባ መመርመርና በጥናት ላይ የተመረተ ምኞትን ሳይሆን ዕድሉን ያካተተ መረጃ ሊቀርብበት ይገባል። 

አካላዊ ርቀት የሚጠብቅ አርሶ አደርነትና አርብቶ አደርነት እንዴት ሊሆን እንደሚችል ለማሰብ በበኩሌ ያስቸግራል። ተራርቀው በሚኖሩ፣ የቤተሰብ ቁጥራቸውም እጅግ አነስተኛና ዘርዛራ አሰፋፈር ባላቸው (Sparsly Populated)፣ ተለይተው በሚኖሩ ማህብረሰቦች (Isolated communities) ላይ ያተኮረ፣ “ለክፉ ቀን” (“Survival Crops”) ተብለው በተለዩ አዝርዕት፣ ብዙ የሰው ጉልበት ማሰባሰብ የማይጠይቅ የግብርና ቴክኖሎጂም ለዚሁ የሚስማማና ለዚያው አካባቢ ውስን ገበያ አቅርቦትን ሊያስታግስ የሚችል የተሰባጠረ አስተራረስን የሚያግዙ (Mixed Farming Technologies) የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎች ጥቅም ላይ ያዋሉ ማበረቦች ላይ ያተኮረ ጥናት እንዳለ አውቃላሁ (IDRC)። ይህ ግን ምን ያህል ተገምግሞ አሁን ላለንበት የኮሮናና ድረ ኮና ዘመን ሊረዳ እንደሚችል ማወቅ ያዳግታል።

በቅድሚያ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት አርሶ አደሩን በተመለከተ የእርሻ መሬትን አዘጋጅቶ ለማረስ፣ ለመዝራት፣ ለማጨድና ለመከመር ሊያውክ የሚችል የጤና ችግር ለማጋጠሙ አሰሳ በማካሄድ መረጃ መሰብሰብ ይጠይቃል። አሁን ለጊዜው ለመገመት የሚቻለው ችግር የተዘራውን ለመሰብብ፣ ወደ ገበያ ለማድረስ የሚያስፈልገው የሰው ጉልበትና ትራንስፖርት እጥረት ይመስለኛል። ወደፊት ግን በኤች አይ ቪና ቦላ ወረርሽኝ ዘመን እንደሆነው ወረርሽኙ ወደገጠሩ የተዛመተ እንደሆነ ሊቀሰም የሚችለው ትምህርት ምን ሊሆን እንደሚገባ መወያየት ይቻላል።

በኤች አይ ቪና ቦላ ወረርሽኝ ዘመን የተራው ስኬታማ ራ ለገጠሩም ለከተማውም ትምህርት ሊሆን ይችላል። ኤች አይ ቪና ቦላ ወረርሽኝ በብዙ መቶ ሺ የሚቆጠር አምራች ይል እንደቀሰፈ ይታወሳል። ከነዚህም መካከል እጅግ አድርገው የተጎዱት ሴቶች፣ ፃናት፣ በእርግዝና ላይ ያሉ ወይም የሚያጠቡ ደሃ እናቶችና አቅመ ደካማ አዛውንት፣ አልፎ ተርፎም የግብርናና ጤና ሙያተኞች  ይገኙበታል። የኤች አይ ቪና ቦላ ወረርሽኝ ከፍተኛ ጥቃት ባደረሱባቸው የምዕራብ፣ ምራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር ከጤናው ዘርፍ ጋር በመቀናጀት የተገኘውን ውጤቱ ለአገራችን መልሶ ሊጠቅም በሚችል መንገድ  መመርር ይቻላል።

ለምሳሌ ያህል የፕሮቲን፣ (Iron: Zinc Vitamin A & B) ሌሎችንም (Micornutirents) እንደበቆሎ፣ ድንች፣ አኩሪ አተር (Soyabean)፣ ስኳር ድንች፣ ካሳቫና ሙዝና (Banana Planatin) በመሳሉት ላይ (Biofortify) በማድረግና ከግብርናና ጤና (Extension Services) ጋር እንደ አንደ ዘርፈ ብዙ ክህሎቶችን ያቀፈ ቡድን (Multidisciplinary Team) አብሮ በመራት የተገፉ፣ የተረሱ፣ የምግብም የጤናም ዋስትና ያልነበራቸውን ሰዎች ይወት መለወጥ ተችሏል። እነህ በእነህ የብረተሰብ ክፍሎች ድካምና ብርታት ላይ ያተኮሩት የግብርና ምርት ዝርያዎች ተዘርተው በቶሎ የሚደርሱ ተባይን፣ ውርጭና ድርቅን መቋቋም የሚችሉ፣ በምግብ የማዘጋጀቱ ደት ከፍተኛ የማገዶ ፍላጎት የማይጠይቁና በምግብ ዝግጅቱም ደት የልሚ ንጥረ ነገሮች (Micornutirent) ይዘትና ጠቀሜታ የማይባክንበት ዘዴ ማረጋገጫ የተገኝቶላቸው ነበሩ።

 ሥርዓተ ፆታን፣ ድህነትና (Social Inclusiveness) ላይ (Focused)፣ (Sensitive) ያደረገ የፕሮክት ሥራ የሆነው የግብርና ቴክኖሎጂ ያስገኘው ውጤት ገና ለረጅም ዘመን ክትትል የሚጠይቅ ነው። ቢሆንም በተለይም የተጠቃሚዎቹ የጤና ሁኔታ እየተገመገመና አስተማማኝ ደረጃ ላይ መድረሱ እየተረጋገጠ ወደ አምራችነት በማሸጋገር፣ ራሳቸው በሚያመርቱት ላይ ተጨማሪ ሴት በማከል የገበያ ተፎካካሪነትና አትራፊነትን ያስገኘላቸው ነበር። በኤች አይ ቪና ቦላ ወረርሽኝ ዘመን ዘመን የጠፋባቸውን (Livelihood Assets) መልሰው ለመገንባት ለልጆቻቸው አስተማማኝ ትምህርትና ጤና ለማብቃትና ተቀማጫቸውን በማሳደግ (Small Scale Agroprocessing Centers) በግልም በጋራም ባለቤት እስከ መሆን ደርሰዋል።  

የተገኘው ልምድ በዋና ዋና ከተሞች በተለይም በአዲስ አበባ እየከፋ የደውን የከተማ ድህነት ለመቀነስ ይረዳል። የከተማ ግብርና (Urban Agriculture)፣ (Promote) ከማድረግ ጋር ተያይዞ የዚህ የከተማ ግብርና ተጠቃሚዎች በምግብ  ጦት ለረጅም ዘመን ረሃብ የተጋለጡትና ከፍተኛ ለይወት አስፈላጊ የሆኑ ንጥረ ነገሮች እጥረት ያጋጠማቸውን ወገኖች ላይ በማተኮር ተመሳሳይ ውጤት ማግኘት ይቻላል።   

መደምደሚያ

ይህ የኮሮና ወርርሽኝ ያደረሰው ጉዳይ  በታሪክ አቻ የማይገኝለት በመሆኑ  በለም አቀፍ ኢኮኖሚው ላይ እስካሁን ያስከተለው ጉዳት ገና በትክክለኛ ሌትም አመርቂ ትንተናም (Quantified and Qualified) አልቀረበበትም። ቢሆንም ጉዳቱና መዘዙ በቀላሉ እንደማይገመት አገሮችንና መንግታትን ከዳር እስከ ዳር ያስማማ ጉዳይ ሆኗል። ይበልጥ ተጎጂና ተጋላጭ የሆኑት ከኮሮና ወረርሽኝ መከሰት ቀደምም ብሎ ለዝባቸው የምግብ፣ የጤናና የሰላም ዋስትና ማቅረብ ያልቻሉት እንደ ኢትዮጵያ የመሳሰሉ አገሮች ናቸው። በተለይም አገራችን ከድርቅና አየር ንብረት ለውጥ ጋር በተገናኘ ከሚደርስባት ተደጋጋሚ ጉዳት እንዳ ሆኖ የሰላምና መረጋት ችግር ከኮሮና ወረርሽን መዘዝ ጋር ሲዳመር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ፈተናዋ የበዛ እንደሚሆን አያጠራጥርም (See Global Report on Food Crises 2020)።

ከዚህ ወረርሽኝ ሁሉም አገሮች ብታም ይሁኑ ደሃ ምናልባት የሚቀስሙት ትምህርት ነጣይና የኔ ብቻ የሚል (Isolationist and Protectionst) ፖሊሲ ምርጫ ሊሆን ይችላል። ሁለተኛው አዲስ ይነት ለም አቀፍ ትብብርን  ከመቼውም ጊዜ ይበጥ አስፈላጊነቱን የተቀበለ፣ ማንኛችንም ከሌላው ተነጥለን ራስችንን ልንጠብቅና ልናድን ማንችል የሚገዘብ፣ ለም አቀፍ ደንብና ሥርዓት (Global Order) ሊሆን ይችላል። የመጀመያው ሁሉንም አገሮች በተለይም አገራችንን የሚጎዳ እንጂ የሚጠቅም እንደማይሆን የሚያከራክር አይመስለኝም። ሁለተኛው ማለትም አዲስ ይነት ለም አቀፍ ትብብር የምንመኘው አማራጭ ማለት ይቻላል።

ይህን የመሰለ ለም አቀፍ/ግሎባል ትብብር ፍትዊ በሆነ መንገድ ሁሉንም የሚያስተናግድ ከሆነ ወደፊት ተመሳሳይ ወረርሽኝም ይሆን ሌላም ይነት ለም አቀፍ መቅሰፍት ቢከስት የተሻለ ቅንጅት በመፍጠር ችግሩን በጋራ ማቃለልና መፍትውንም በተሻለ ለሁሉም ማዳረስ ያስችላል። ጥያቄው ግን እውነት ይህን ይነት አዲስ የአመለካከት ለውጥ ማለትም ሚዛኑን የጠበቀና ለም አቀፍ (Global) ግዴታን ያገነዘበ አዲስ ይነት ግንኙነት እንደ ኢትዮጵያ ለመሳሰሉ አገሮችና ዝቦች ምን ዕድል ያስገኝላቸዋል የሚለው ነው። ይህ በራሱ ትልቅ ምርምር የሚጠይቅ ስለሆነና የምርምሩም ውጤት መቼ ተጥናቆ ለውይይት እንደሚቀርብ ለማሰብም እጅግ ሩቅ ስለሚሆን ለጊዜው ወደ ጎን ማድረግ ይቻላል። 

ኢትዮጵያ ለም አቀፍ ንግድ ላይ ተፅዕኖ የማሳደር አቅሟ እጅግ ውሱን  ነው። እንኳንስ በተናጠል እንደ አጉር በአፍሪካ ብረት በክሉ በጋራ ለመደራደርና ለም አቀፉም የንግድ ስምምነት ለአጉሩ ምርት ፍት (Terms of International Trade Agreement Favourable to the Continents Products) ለማድረግ በርካት ድርድሮች ቢደረጉም ውጤቱ እዚህ ግባ የሚባል እንዳልሆነ ይታወቃል። አሁንም ይህ ቀውስ ካለፈ በኋላም ቢሆን የአፍሪካ አጉር በጋርም ሆነ  እንደ ኢትዮጵያ የመሳሰሉ አገሮች ለም አቀፍ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለታዊ ርዓት (Globalsources of Food Supply Chain) ላይ ጥገኝነቱን በመቅረፍ፣ በምግብ ራስን በራስ መቻል ላይ ትኩረት እስካልሰጡ ድረስ ነገም ተነገ ወዲያም ለተመሳሳይና ለከፋ ችግር እንደተጋለጡ መቆየታቸው አይቀርም። 

በአገራችን የወረርሽኙ ተፅዕኖ ምን ሊሆን እንደሚችል ገና በትክክል አይታወቅም። ይህ እንዳለ ሆኖ እንደ አገር በተቀናጀ መልክ ጉዳቱንና መዳሰስ ያስፈልጋል። ይህ ዳሰሳ አቅጣጫ ሊጠቁም የሚችልና ለድረ ኮሮና ዘመንና ከዚያም በላ የሚዘልቅ ስትራትጂ ወይም ፍኖተ ካርታ ለመንደፍ ይረዳል። ይህንን የመሰለው ስትራጂ ወይም ፍኖተ ካርታ የቅርብ፣ የመካከለኛ ዘመንና የረጅም ዘመኑን ላማን ግብ ያቆራኘ ሲሆን በመጨረሻው ይህ ስትራጂ ወይም ፍኖተ ካርታ ሊያደርስ የሚገባው ለችግር ደራሽና ዘለቄታ ያለው የምግብ ምርትና አቅርቦት ሥርዓት (Resilient and Sustainable Food System) ግንባታ ላይ ነው። 

በአገራችን የኤች አይ ቪ ኤድስ ወረርሽኝ በከፋበት ዘመን በግብርና ምርምርና ልማት በኩል ሥርዓተ ታን፣ ወጣቶችን፣ አዛውንቶችን ያካተተና በነርሱ ፍላጎትና ጥቅም ላይ ትኩረት ያደረገ ምን ሥራ እንደተውቀቱም መረጃውም የለኝም። ይህም ሆኖ በአገራችን የተራ ወይም የተሞከረና ውጤት ያሳየ ራ የለም ማለት አልችልም። ይህ እንዳለ ሆኖ በሌሎች አገሮች በዚሁ ኤች አይ ቪ ኤድስና ኤቦላ ወረርሽኝ ዘመን የምግብ ዋስትናን ከጤናው ዘርፍ ጋር በማቀናጀት ለገጠሩም ለከተማውም የሚበጅ ራ መራቱን በመገንዘብ፣ ይህም ልምድ በበቂ የተመዘገበ  በመሆኑ ከዚያ ልምድ በመቅሰም የበለጠ ውጤታማ በአገራችንም መራት የማይቻልበት ምክንያት አይታየኝም።

ይህ ልምድ በአንድ ግብረ ይል በኩል ፈጥኖ ሥራ ላይ ማዋል ቢችል ጠቃሚ መሆኑን ስለማምን ይህ ራ በቶሎ አንዲራ ካስፈለገ አመራር መስጠት ያለበት የግብርና ምርምር ወይም ለዚህ የምርምር ተቋም አጋዥ መሆን የሚችሉ ባለድርሻ አካላት ይመለኛል።

የአገራችን ግብርና ምርምር ከአስፈላጊ ድርጅቶችና አካሎች ጋር አብሮ በመራት በዚህ የኮሮና ወረርሽኝ ዘመንና ከዚያም በድረ ኮሮና ዘመን  የራሱን ድርሻ ማረጋገጥ ይኖርበታል። በርካታ የምግብ ዋስትናን የተመለቱ ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በመምከር የገጠሩንም የከተማውም ድህነት ለመቅረፍ የሚያስችል መሪ ሳብ ይዞ መውጣት ይጠበቅበታል። የአገራችንን የግብርና ሥርዓትና የአስተራረስ ባህል ከሥረቱ ለመለወጥ (Revolutionize and Transform) መታሰብ ያለባቸው ጉዳዮች እጅግ በርካታና ርስ በርሳቸው የተሳሰሩ ናቸው። በዚህ በኩል አስተዋጽኦ ለማድረግ የሚችል የለጠነ፣ አገር በቀል ክህሎትን ከለም አቀፍ ልምድና ክህሎት ጋር ያዋደደ የሰው ይል ችግር በአገራችን የለብንም።   ከአስተራረስ ዘዴው እስከ አመጋገብ ባህሉ ድረስ የሚደርሰውን ችግር ለመቅረፍ ካልቻልን የአገራችን ግብርና ከችግር ሊወጣና የምግብ ዋስትናን ሊያረጋግጥልን አይችልም።

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊው በሲኒየር ሶሻል ሳይንቲስት ደረጃ የቀድሞ ዓለም አቀፍ ግብርናና ልማት ድርጅት ተመራማሪ ሲሆኑ፣ ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለከካት ብቻ የሚንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...