Saturday, September 30, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅዕጣ ክፍሉ መውደቅ የሆነው የአዳማ ድልድይ

ዕጣ ክፍሉ መውደቅ የሆነው የአዳማ ድልድይ

ቀን:

በአዳማ ከተማ በቀበሌ 05 የሚገኘው “ሞኤንኮ ገናናው” በሚል መጠሪያ የሚታወቀው ድልድይ ግንባታው ኅዳር 3 ቀን 2011 ዓ.ም. መጀመሩ ይታወቃል። የድልድዩን ግንባታ በተቋራጭነት የወሰደው እድሪስ አህመድ ጄነራል ኮንትራክተር ሲሆን፣ አሠሪው ባለቤት የአዳማ መስተዳደር ጽሕፈት ቤት ነው። የግንባታው ወጪም 15,058,689.15 ብር ይፈጃል ተብሎ ተገምቷል።

የ25 ሜትር ርዝመት፣ የ10 ሜትር የውስጥ ለውስጥ ስፋትና የ12 ሜትር ቁመት ያለው ይህ ትልቅ ድልድይ፣ የግንባታው ሒደት ሲጓተት ሲራዘም ከርሞ ለፍጻሜ ሊበቃ በተቃረበበት ደረጃ ላይ ሳለ፣ ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም. ከረፋዱ 5 ሰዓት ላይ የድልድዩ አካል ዋነኛው ክፍል ቶፕ ስላብ (Top Slab) ተደርምሷል፡፡ባጋጠመውም መደርመስ በግለሰቦች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት አድርሷል፡፡

ለፈረሰው ድልድይ ተጠያቂው መሆን ያለበት ማን ነው? የተጠያቂነት ድርሻ ፅዋውንም ባለድርሻ አካላት በልክ በልካቸው ሊወስዱ ይገባል። ዕጣ ክፍሉ መውደቅ የሆነው የሞኤንኮ ድልድይ ትንሳዔው መቼ ይሆን? ፎቶዎቹ የድልድዩን ወቅታዊ ገጽታ በከፊል ያሳያሉ፡፡

ዕጣ ክፍሉ መውደቅ የሆነው የአዳማ ድልድይ

ዕጣ ክፍሉ መውደቅ የሆነው የአዳማ ድልድይ

(ስንሻው ተገኘ፣ ከአዳማ)

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...