Saturday, April 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ለየአገሩ 200 ሺሕ ዶላር ሊሰጥ ነው

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ለየአገሩ 200 ሺሕ ዶላር ሊሰጥ ነው

ቀን:

የፊፋ ድጋፍም ይጠበቃል ተብሏል

ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ አገሮች ዓመታዊ የእግር ኳስ መርሐ ግብሮቻቸውን በዓለም አቀፉ ኮቪድ 19 ወረርሽን ምክንያት በሰረዙበት በዚህ ወቅት፣ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ለአባል አገሮቹ የገንዘብ ድጎማ ሊያደርግ መሆኑ ታወቀ፡፡ ኮንፌዴሬሽን ለእያንዳንዱ አገር 200 ሺሕ ዶላር ሊሰጥ ማቀዱ ተነግሯል፡፡

የ54 አገሮች ብሔራዊ ፌዴሬሽኖችን የሚያስተዳድረው ካፍ፣ በየዓመቱ በመደበኛነት ከሚያከናውናቸው ውድድሮች መካከል የአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግና የአፍሪካ ክለቦች ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ይሁንና ሁሉም በወረርሽኙ ምክንያት ውድድሮቹ እንዲሰረዙ አድርጓል፣ የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በሚመለከት አሁን ላይ ምንም ያለው ነገር የለም፡፡

የዘንድሮን የውድድር ዕጣ ፈንታ በሚመለከት ብዙዎቹ የአፍሪካ አገሮች ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስ ስለመደረጉ ወይም ስለመሰረዙ ውሳኔ ላይ ባይደርሱም፣ 16 አገሮች መደበኛ ውድድሮቻቸውን መሰረዛቸው ይፋ አድርገዋል፡፡

ኢትዮጵያ የዓመቱን ውድድር ከመሰረዟም በላይ በሚቀጥለው ዓመት በአፍሪካ የክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግና የክለቦች ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ውክልና እንደማይኖራት ለጊዜውም ቢሆን ይፋ አድርጋለች፡፡ የተቀሩት 15 አገሮች ደግሞ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ውድድሩ እስከተቋረጠበት ድረስ በደረጃ ሰንጠረዡ በተቀመጠላቸው ውጤት መሠረት የሚያሳትፏቸውን ክለቦች በማሳወቅ ውድድሮቻቸውን መሰረዛቸው ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ እነዚህም ቡርኪና ፋሶ፣ ጋምቢያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሞሪሸስ፣ አንጎላ፣ ኬቨርዴ፣ ጊኒ፣ ቶጎ፣ ዴሞክራቲክ ኮንጎ፣ ኬንያ፣ ካሜሮን፣ ሩዋንዳ፣ ኒጀር፣ ኮንጎ ብራዛቪልና ላይቤሪያ ናቸው፡፡

አኅጉራዊው ተቋም እንደ አውሮፓና መሰል አኅጉሮች በእሱ ሥር የሚያስተዳድረውን እግር ኳስ ወደ ገንዘብ በመለወጡ ረገድ ክፍተኛ ክፍተት ያለበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁንና ካፍ በየዓመቱ ለአባል አገሮቹ የሚሰጠውን የገንዘብ ድጎማ ሳያቋርጥ ለመስጠት ማረጋገጫ መስጠቱ ታውቋል፡፡ ዘገባዎች የካፍን ድረ ገጽ በመጥቀስ የተቋሙን ውሳኔ ይፋ አድርገዋል፡፡

በሌላ በኩል የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) እንደ ካፍ ሁሉ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ለመሰሉ በእግር ኳስ ደረጃቸው በዝቅተኛ ደረጃ ለሚጠቀሱ አገሮች የሚሰጠው ዓመታዊ የገንዘብ ድጎማ እየተጠበቀ መሆኑ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡

ከፊፋ የሚጠበቀው የገንዘብ መጠን በየዓመቱ በመደበኛነት ከሚሰጠው 500 ሺሕ ዶላር በተጨማሪም ለኮቪድ-19 ወረርሽኝና ለመሳሰሉት አስቸኳይ ለሆኑ ጉዳዮች ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ከዚህ በፊት የተናገሩትን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ከዚህ በተጓዳኝ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የአውሮፓ አገሮች የእግር ውድድር ከተቋረጠበት እንደሚቀጥል ተረጋግጧል፡፡ በኢትዮጵያውያን የሚዘወተረውና የተለመደው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሰኔ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደሚጀመር ሲገለጽ፣ የጀርመን ቡንደስሊጋ ግን ከሁለት ሳምንት በፊት መጀመሩ ይታወሳል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...