Monday, May 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
እኔ የምለዉየዘር ውርስ ይዘታቸው የተለወጡ አዝርዕት ለአገራችን ግብርና ሥር ነቀል መፍትሔ ዕድል ወይስ...

የዘር ውርስ ይዘታቸው የተለወጡ አዝርዕት ለአገራችን ግብርና ሥር ነቀል መፍትሔ ዕድል ወይስ ሥጋት? (ክፍል ሁለት)

ቀን:

አማረ ተግባሩ (ዶ/ር)

የዘር ውርስ ይዘታቸው የተለወጡ አዝርዕት (Genetically Modified Organisms) በተመለከተ ገዳው ተነስቶላቸው ይገቡ ይሆናል ተብለው የሚጠበቁትን የዘር ውርስ ይዘታቸው የተለወጠ ጥጥ፣ በቆሎ ወይም እንሰት ላይ ስንነጋገር መርሳት የሌለብን የምንገኘው አሁንም በኮና ወረሽኝ ዘመን መሆኑን ነው። ይህ የኮሮና ወረርሽኝ በተናጠል የማይታይ፣ ግዙፍና ውስብስብ (Compounded) ከሆነው የምግብ ዋስትና ችግር ጋር የተገናኘ ነው። ይልቁን  መገንዘብ የሚያስፈልገው ይህ የኮሮና ወረሽኝ ካለፈም  በኋላ ጉዳቱ በድረ ኮሮና ዘመን ጭምር የሚከተለን መሆኑ ነው። እንደ ኮሌራና የአንበጣ መንጋ የመሳሰሉትና ሌላም ይነት ተመሳሳይ ወረርሽኝ  ወይም ተፈጥሯዊና ተፈጥሯዊ ያልሆነ መቅሰፍት በድጋሚ ሊከት እንደሚችል መገመት ይቻላል። በዚህ ይታና ግንዛቤው ውስጥ ሆነን የዘር ውርስ ይዘታቸው የተለወጡ አዝርዕ ላይ የሌሎች አገሮች ልምድ ገና ለረም ጊዜ መዘዙ ለሚከተለን የምግብና ጤና ዋስትና፣ የገቢ ምንጭና ሥራ ፈጠራ ላይ ምን ሊያስተምን እንደሚችል ሊያግዘን ይችላል። 

የህንድ ልምድ ምን ይመስል ይሆን?

ከዚህ በታች የማቀርበው በህንዱ ሳይንቲስት ኬ.አር. ክራንቲና ምዕራባዊው ባልደረባው ግሌን ዴቪስ ስቶን “Long-term Impacts of Bt Cotton in India” በሚል ርዕስ(Nature Plants 6(3):188-196· March 2020)ካሳተሙት ጥናት (DOI: 10.1038/s41477-020-0615-5)፣ እንዲሁም ማርክ ላይናስ፣ “Why Did India Abandoned the Production of GM Cotton?” በኮርኔል ዩኒቨርሲቲ (Alliance for Science Journal) ላይ እ.ኤ.አ. ኦገስት 2 ቀን 2018 ካቀረቧቸው ጥናቶች የተገኘ ነው።

በቅድሚያ ለማስገንዝብ ያህል ጥጥ እንደ አገራችን ቡናና ጤፍ በህንድ የተገኘና በዝርያ ባለቤትነትም የተመዘገበባት ነች፡፡ የምዕራቡ ዓለም የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ የበላይነቱን እስከጨበጠ ድረስየህንድ በጥጥ ላይ የተመረተ የጨርቃ ጨርቅ መለስተኛ የምርት ቴክኖሎጂ ድንበር ተሻጋሪና ትልቅ ደረጃ ላይ የደረሰ ነበር፡፡ አሁንም በዝቅተኛ ገቢ ባላቸው አርሶ አደሮች ይዞታ ከሚዘሩ የገቢ ምንጭ ማስገኛ አዝርዕ መካከል ጥጥ ሰፊውን ቦታ ይይዛል። ከላይ በጠቀስኳቸው ጥናቶች እንደተመለከተው የዘር ውርሱ እንዲመች ተደርጎ የተለወጠው ወደ ዝቅተኛና መለስተኛ ገቢ ላቸው የህንድ ገበሬዎች ማሳ እንደገባከአገር በቀሉና በአርሶ አደሩ እጅ ከነበረው የጥጥ ዝርያ ጋር ሲወዳደር በእርግጥም እጥፍ የምርት ድገት አስመዝግቧል፡፡

ይህም የምርት ድገት ሲያሽቆለቁል ለስድስት መቀጠሉ ይህ “ተዓምረኛ” ስኬታማ የጥጥ ዝርያ በበዙ ዮን የሚሆየህንድ አርሶ አደሮችን ቀልብ ሊስብ ችሏል። ከዚህም የተነሳ ከፍተኛ የባንክ ብድር በመውሰድ ይህንን የጥጥ ዝርያ ተቀብለውትና ሌሎች የምግብና የገቢ ምንጭ የሆኑትን አዝርዕ በመተካት አስፋፍተውት ነበር። ለ20 ዓመታት የተሰሰበው መረጃ በሚገባ ሲመረመር ግን እውነታው ሌላ ሆኖ ተገኝቷል። ከስድስት ምርታማ በኋላ የምርት ማሽቆልቆል ተከስቷል። ይኸው የዘር ውርሱ የተለወጠ ጥጥ ድርቅን የመቋቋም አቅሙ እየመነመነና እንደ (Pink Bollworm, Mealybug, Aphids, and Other Sucking Insects Like Leafhoppers) በመሳሰሉት የተባይና በሽታ ይነቶች መጠቃት ብቻ ሳይሆንለእነ በሽታዎች የመፈልፈያና መራያ ቋት እስከ መሆን ደርሷል።

እንደ አዲስ የተከሰቱትን የተባይና በሽታ ይነቶች ለመቋቋም ከፍተኛ ብርታትና መጠን ያለው መድኒት መጠቀም ስለሚጠይቅ ከምርት ማሽቆልቆሉ ጋር ተደርቦ አርሶ አደሮቹን በወደረጃ ለተጨማሪ ኪሳራ ዳርጓቸዋል። የህንድ የጥጥ ዝርያ የነበረውን የተፈጥሮ ብዝነት እስከ ማውደም ከመደረሱ ጋር ተያይዞ አርሶ አደሩ ሌላ መውጫ አማራጭ በማጣቱይህንኑ ጥጥና የተባይ መከላከያ በማምራት ሞኖፖሉ በእቸው ለሚገኝ ኩባንያዎች ጥገኛ ሆኗል፡፡ በጤና ላይ ያስከተለው ጉዳት ይህ ነው የማይባል በመሆኑ ለጤና ጠንቅ የተጋለጡ የህንድ አርሶ አደሮች፣ በጥጥ ማሳው ላይ መድኒት በመርጨት ተቀጣሪ የነበሩ ወጣት ሴቶችና እናቶች የፅንስ መጨናገፍ በተደጋጋሚ እየረሰባቸው የገዛ ይወታቸውን እስከ ማጥፋት እንደ ደረሱ መረጃዎች ያመለክታሉ።

ከዚህ በላይ ከተዘረዘሩት ግዙፍ ጉዳቶች ባሻገር ለሃያ መታት ያህል የተሰበሰበው መረጃ እንደሚያመለክተውየምርት ድገት በተከታታይ ለስድስት መታት ተመግቦበታል የተባለውም የግብርና ሥነ ዳር ቢሆን ንድን እንደ አገር የማይወክል ነበር። በሌሎች በአገሪቱ የተለያዩ የግብርና ሥነ ዳር ተሞክሮ የተገኘው ውጤት ስኬታማነቱን የሚያፈርስ እንጂ የሚደግፍ ባለመሆኑ ይህንን ጥጥ አጠቃሎ አገራዊ መፍት አድርጎ ለማቅረብ የሚያስችል አልነበረም፡፡ ከእጥፍ በላይ የምርት ዕድገት ተመዘገበበት በተባለው የግብርና ሥነ ምዳር ላይም ቢሆን ለረም ጊዜ ተከታታይ የጥናት ክትትል ተደርጎ በቂ መረጃ ያልተሰበሰበበት ነበር። ይህም ቢሆን የምርት ድገት ብቻውን በተናጠል ተወስዶ ድምዳሜ ላይ የተደረሰበት ነበር፡፡ ከሌሎች መለኪያ ጋር ተቀናጅቶ ያልቀረበ በመሆኑ የምርት ተመን በራሱ  ለምርታማነት የስኬት መለኪያ ተደርጎ መወስድ የማይገባውና አሳሳች ድምዳሜ እንደ ነበር ከላይ የጠቀስኳቸው ጥናቶች መስክረዋል።

ይህም ቢሆን የምርት ድገት በተከታታይ መታት አስመዘገበ የተባለው አካባቢ የህንድ ገበሬዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ የተላለፈ የተፈጥሮ ማዳበሪያን የማዘጋጀት፣ የማከማቸትና የመጠቀም ባህል ያላቸው በመሆኑ የምርቱ ዕድገት ከራሱ የዘር ውርሱ ከተለወጠው ጥጥ ብቻ የተገኘወይየማዳበሪያው ገዛ ተጨምሮበት ይሁን አይሁን ማረጋገጥ እንደማይቻል ጥናቱ አምሮበታል፡፡ ከሁሉም የሚገርመው ከአንድ ውስን ከሆነ የአካባቢ ሥነ ምዳር ተነስቶ ያውም በበቂ መረጃ ሳይረጋገጥ በርካታና ውስብስብ በሆኑት የተለያየ ተፈጥሮ፣ የግብርና ባህልና ችግር ላለባቸው ሥነ ምዳር እንደ ጅምላ (Blanket) መፍት ተወስዶ አርሶ አደሩ እንዲቀበለው መደረጉ በህንድ የህንድ ጥጥ ግብርናና ሥነ ምዳር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለመድረሱ ምክንያት ሆኗል። 

አንዳንድ የህንድ ሳይንቲስቶች የዘር ውርሱ በተለወጠ ጥጥ ላይ የተደረደረው ወቀሳ ሚዛኑን የሳተ ነው በሚል የራሳቸውን መከራሪያ ያቀርባሉ። እነሱ እንደሚሉት በርካታና የአቅርቦት ምንጫቸውን በትክክል ማረጋገጥ የማይቻል ጥጥ ወደ ግብርናው ሥነ ምዳር በመግባታቸው የትኞቹ ትክክለኛ የትኞቹ ደግሞ በማስመል (Counterfeit) የተፈበረኩ እንደሆኑ ሳይጣራ በጅምላ የዘር ውርሱ በተለወጠ ጥጥ ላይ የጨለመ ድምዳሜ ላይ መድረስ ተገቢ አይደለም የሚል ነው። ይህም ሆኖ እነዚህ ወገኖች ትክክለኛ የማረጋገጫ ሰርተፊኬት የተሰጣቸውም ጥጥ ቢሆኑ ከተወሰነ ዘመን በኋላ የምርት ማሽቆልቆልም ሆነ ለአዲስ ይነት በሽታ ተጋላጭ የሆኑበትን ምክንያት ለመደበቅ አልሞከሩም። ከመጀመያውም ቢሆን የዘር ምህንድስናው ስህተት እንደነበረው ተረድተናልና ዕድሉ ተሰጥቶን ከስህተቱ በመማር ችግሩን እንድንፈታ ተጨማሪ የምርምር ዕድል ሊከፈትልን ይገባል እንጂ ገዳ ሊደረግብን አይገባም የሚል ነው።

በማስመሰል የተፈበረኩና የተመረቱ ጥጥና በቆሎ ወይም የምግብና መድኃኒት ይነቶችን የህንድ ገበያን ማጥለቅለቃቸውና በአርሶ አደሩ ላይ ኪሳራ ብቻ ሳይሆን የጤና እክልና ራስን በራስ እስከ ማጥፋት የደረስ ችግር መከስቱና ከዚያም አልፎ የጥጥ ዝርያ ብዝነትን በማጥፋት አማራጭ እስከ ማሳጣት የደረሰ ሁኔታ ሲፈጠር የአገሪቱን የባዮ ሴፍቲ መመርያ (Biosafety Regulation) ለማስከበር ላፊነትና ግዴታ የተጣለባቸው ወገኖች የት ነበሩ? የሚል ጥያቂ ማስነሳቱ አልቀም። ህንድ እንዲህ ይነት አጣብቂኝ ውስጥ ከወደቀች የኛስ ዕጣ ምን እንደሚሆን መገመት አያስቸግርም። 

እነዚህዘር ውርሱ የተለወጠ ጥጥ አሻሻይህ ዝርያ ባስከተለው መዘዝ  በሴቶች ላይ የፅንስ መጨናገፍም ቢሆን አስፈላጊውን ጥንቃቄ ከማድረግ ጉድለትየተከሰተ ነው በሚል ይህ አደጋ ያጋጠማቸውንና ይወታቸውን እስከ ማጥፋት የደረሱትን ወጣት ሴቶችና እናቶች መልሶ ተጠያቂ በማድ GM (Bt) Cotton) ጥጥ አምራች ለም አቀፍ ኩባንያዎችን ከተጠያቂነት ነፃ እንዲሆኑ ተከራክረዋል። አልፎ ተርፎም በህንድ የታየውን ራስን በራስ እስከ ማጥፋት የተደረሰበትንም ክስተት በተመለከተ የፀረ የዘር ውርስ ለውጥ አክቲቪስቶችና አረንጓዴ ልማት ንቅናቄ መሪዎችውን በማለት ውድቅ አድርገውታል። ለዚህ ያቀረቡትም መከራሪያ በህንድ የታየው ራስን በራስ የማጥፋት ክስተት በሌላው ለም ራስን በራስ ከማጥፋት ጋር ከተያያዙ ውስብስብ ችግሮች ጋር የተገናኘ እንጂ ይህ ጥጥ ያስከተለው ኪሳራ፣ የእርሻ መሬታቸው ወደ በዳነት መቀየርና ለችግር ጊዜ ያስቀምጡትና ከዘመን ዘመን ሲያገላብጡት የኖረው የጥጥ ዝርያ ውድመትና የተባይና በሽታ መቆጣጠሪያው ድኃኒት ያስከተለው ችግር በራሱ ምክንያት ሊሆን አይችልም የሚል ነው።

ይህ ጉዳይ በህንድ የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ተከራካሪዎችንና የዚህን ጥጥ አምራች ለም አቀፍ ኩባንያዎችን እስከ ፍርድ ቤት ያደረሰ ጉዳይ ሲሆንእስከ ቅርብ ድረስም ቢሆን ረቺና ተረቺ የሌለውና መቋያልተገኘለት ጉዳይ ነው። በዚህ ጽሑፍ አቅራቢ አስተያየት የፈረጠመ ለም አቀፍ (Global) የገንብና የፖለቲካ ጉልበት ያለውን በሎቢስቶች የተደገፈ እንደ ሞሳንቶ የመሰለውን ኩባንያ በግ ፊት በመርታት ፍትገኛለን ማለት ዘበት ነው። 

የዘር ውርሱ የተለወጠ ጥጥ አሻሻች እንደሚሉት ከላይ የተጠቀሱት በህንድና በሌሎችም አፍሪካ አገሮች የታዩት እንደ (Pink Bollworm, Mealybug, Aphids, and Other Sucking Insects Like Leafhoppers) የመሳሰሉት የበሽታ ይነቶች በቻይና፣ አውስትራ፣ በካናዳ ተከሰተም ባዮች ናቸው። ያልተከሰበትምክንያት ሲዘረዝሩ እንደ ህንድና በርካታ የአፍሪካ ሮች ሐሰተኛ (Counterfeit) የዘር ይነቶች በብዛት የሚገቡበት ዕድል ባለመኖሩና የባዮ ሴርቲ ግና ቁጥጥር ተቋማት በሚገባ የተዘረጉና ለምንም ይነት ልልነትም ሆነ ሙስና ያልተጋለጡ በመሆናቸው ነው የሚል ነው። ይህንን ምክንያት እንደ እውነት እንውሰደው ብንል ኢትዮጵያበመሰለች አገርአንድ ጊዜ በዘረመል ምህንድስና ላይ የተጣለው ገዳ ቢነሳ ሊያጋጥም የሚችለውን ችግር ማሰብ አያግትም። የቻይና፣ አውስትራና የካናዳ ስኬት ሊገርም አይገባም፡፡ ምክንያቱም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ይጨምራል፡፡

የጥጥ እርሻው የተያዘው ከፍተኛ የካፒታል አቅም ባላቸው ባለ ሰፋፊ እርሻ ባለቤቶች መሆኑ ዋነኛ ምክንያት ሆኖ ይገኛል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የገቢም የኑሮ ረታቸው በዚሁ በጥጥ ተክል ላይ ብቻ ያልተመረተና የዓመቱ ሌላም ይነት ብል የሚያመርቱ፣ በጠንካራ ማበር የተደራጁና የተኮረጀ ወይም ጊዜ ያለፈበት ዝርያም ሆነ የተባይና በሽታ መከላከያ መድኒት ወደ ማሳቸው እንዳይገባ ውቀቱም የሚቆምላቸውም ተከራካሪ ያላቸው መሆናቸው ተጠቅሷል።

አንድ የጥጥ ዝርያን ለማጥቃት የሚፈለፈለውን በሽታ ለመግታትየመሬቱን ምርታማነት ከማሽቆልቆል ለመጠበቅ እንዲያስላቸው በበቂ በማፈራረቅ፣ ወይም መሬቱን ለተወሰነ የምርት ዘመናት በማሳደር (Fallow) የምርት ማሽቆልቆልን ለመግታትና የበሽታው የመፈልፈያ አዙሪት ለመስበር አስችሏቸዋል፡፡ በሽታውም ቢያጋጥማቸው ማዳበሪያም ሆነ የተባይና በሽታ መከላከያውን በሆነው ዋጋ የመግዛት አቅም ያላቸው ናቸው፡፡ ምርቱ የሚሰበሰብበትም እንደ ህንድና የአፍሪካ ጥጥ አርሶ አደሮች በሰው እጅ ሳይሆን ዘመናዊ ክኖሎጂ በመጠቀምና አልፎ ተርፎም ራሱን ችሎ እንደ ሮቦት በጥጥ ማሳው ላይ ራሱን ችሎ የሚንቀሳቀስ (Strippers and Pickers) ያለው መሰብሰቢያ (Cotton Harvester) የተገጠመለት በመሆኑ የጥራት ችግር አይገጥማቸውም፡፡

ከዓለም አቀፍ የጥጥ አቅርቦት ሰንሰለት (Supply Chain) ጋር ጠንካራ ትስስር ስላላቸው የጥጥ ምርታቸው በዓለም ገበያ ተመራጭና አትራፊ አድርጓቸል።  የቡርኪና ፋሶም ሆኑ የህንድ ደሃ ገበሬዎች የጥጥ ማሳቸውን በየምርት ዘመኑ የማፈራረቅ፣ ወይም ለአንድ መት እንኳን የማሳደር አቅም የላቸውም፡፡ የጥጥ እርሻቸው እንደ ቡና፣ እንሰትና ሌሎችም (Tree Crops) አንድ ጊዜ የተተከሉና በየዘመኑ ምርት የሚሰበስቡባቸው (Perennial Crop) እንጂ እነሱን አስወግደው በሌላ የምግብ ዋስትና ወይም የገቢ ማስገኛ አዝርዕት በመተካት የተባይና በሽታ የመፈልፈያውን አዙሪት መስበር የሚችሉ አይደሉም። ለምርታማነት የሚያስፈልጉትንም ግብዓቶች ለመሸመትም ሆነ የዘመነ (Agronomic Practice) ለመጠቀም እንዲችሉ የመንግሥት ኤክስቴንሽን ድጋፍ በበቂ የማያገኙ ናቸው።

ይህ በራሱ ለምርት ማሽቆቆልም ሆነ ምርቱ በበሽታ ለመጠቃት ያጋለጠ መሆኑ ሲታወቅ ማዳበሪያና የተባይ በሽታ መቆጣጠሪያ መድኒት የመግአቅም የሌላቸው፣ በሰው ጉልበት ካልሆነ በስተቀር መለስተኛ የሰብል መሰብሰቢያ ሪያ መግዛትና መጠቀም የማይችሉ ገበሬዎች ይህንን ብዙ ወና ጉዳት ሊያስከትል የሚችል ዝርያ እንዲቀበሉ ማድረግ መረታዊ ስህተት እንደነበረውርኪና መንግሥት በመገንዘብ ገዳ አድርጎበታል። ህንድ ደግሞ መውጫው የማይታወቅ አጣብቂኝ ውስጥ እንዳለችና ድም አልባ በሆኑት ደሃ ገበሬዎችና የዚህ የዘር ውርሳቸው የተለወ አዝርዕት (GMO)፣ ማዳበሪያና መድኒት አቅራቢ ኩባንያዎችና የጥቅሙ ተካፋይ የሆኑ የአገሪቱ ፖለቲከኞች በፍርድ ቤት እንደ ተፋጠጡ አሸናፊውና ተሸናፊው በውል ባለየበት ሁኔታ ውስጥ ትገኛለች፡፡ (ክፍል ሦስት ሳምንት ይቀጥላል)

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊው በሲኒየር ሶሻል ሳይንቲስት ደረጃ የቀድሞ ዓለም አቀፍ ግብርናና ልማት ድርጅት ተመራማሪ ሲሆኑ፣ ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ወይም [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመስቀል አደባባይ የመግቢያ ክፍያ ለምን?

ወጣቶች፣ ሕፃናትና አረጋውያን ሳይቀሩ መንፈሳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሐሳባቸውን በነፃነት...

በሕገ መንግሥቱ የተዋቀረው ‹‹የብሔር ፖለቲካ›› እና ‹‹ሥርዓቱ›› ያስከተለው መዘዝና መፍትሔው

(ክፍል አራት) በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ) ባለፈው ጽሑፌ (በክፍል ሦስት) አሁን ያለው...

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብና የመንግሥት መሪ ምሥል

በበቀለ ሹሜ በ2015 ዓ.ም. መጋቢት ወር ውስጥ ይመስለኛል በ‹ሸገር ካፌ›...

ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ያደረገው አዋጅ የፍትሐዊነት ጥያቄ አስነሳ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ተቋማዊና...