Friday, March 24, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
እኔ የምለዉእሽኮለሌ በጉራማይሌ!

እሽኮለሌ በጉራማይሌ!

ቀን:

መስፍን ብቱ

የአንድን አገር የፖለቲካ ‘ዳይናሚክስ’ ለመረዳት የፖለቲካ ክስተቶቹን ብቻ ነጥሎ መረዳት ብቻ አይበቃም። በተለይም የፖለቲካ ትንተና የሚያደርጉ ተንታኞችና የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች/አክቲቪስቶች ብረሰባዊ ዳይናሚክሱን (ሶሻል ዳይናሚክስ) ካልተረዱ ትክክለኛ ትንተና ወይም ፖሊሲ ለማውጣት ሊቸግራቸው ይችላል። በኢትዮጵያ በሁሉም ብረሰቦች ውስጥ አዎንታዊ ሊባሉ የሚችሉ አያሌ ብረሰባዊ ወጎች (Values) እንደ መኖራቸው አሉታዊ የሆኑ አያሌ ወጎችም አሏቸው። የኢትዮጵያ ብረሰብ መሳ በመሳ ልማዳዊ (Traditional) በመሆኑ ዘመናዊ መንግት ለማቋቋም ከተደረገው ሙከራ ጋር ተያይዞ ቅንጣት በምታክለዋ የኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ ዘመናዊ ንግድና በተለይም በዘመናዊ ትምህርት ምክንያት እነዚህ ልማዳዊ ወጎች መቀየር ጀምረው ነበር። በዚህ ረገድ ወደ ዘመናዊነት ለሚደረገው ሽግግር ትልቁ እንቅፋት የራሱ የገው መደብ አባላት መሳ በመሳ ልማዳዊ በመሆናቸው የኑሮ ዘይቤያቸውም ልማዳዊ ነበር።

ምንም ሚኒስትር ወይም ዳኛ ቢሆን፣ መምህር ወይም የጦር መኮንን ቢሆን በግል ኑሮው ልማዳዊ ከመሆኑ የተነሳ እንኳን ለወጣቱ ትውልድ አርያ ሊሆን ከልጆቹ አንዳንዴም ከባለቤቱ ጋር በሚገባው ቅራኔ (ወጎች ላይ የተመረቱ ቅራኔዎች) ምክንያት የራሱንም ቤተሰብ በሚገባው መምራት ያልቻለውም ነበር። ከዚህ የተነሳ የገው መደብ አንድ እግሩ ዘመናዊነት ላይ ያረፈ ቢመስልም እንዳለ ልማዳዊ ነበር ማለት ይቻላል። ለዚህ ነው አገሪቱንም በሙሉ ልብ ወደ ዘመናዊነት ሊመራት ያልቻለው። ራስ ካሳ ንጉ ‹‹ን ሁሉ የደሃ ልጅ አስተምረህ ኋላ ራስህ ላይ እባብ ይጠመጥምብሃል›› ያሉትን ልብ ይሏል። ያኔ ገንነው የነበሩት ወጎች የልማዳዊው ወጎች ነበሩ። ከነዚህም ወጎች በርካታ አሉታዊ ገጽታዎች ያላቸው ቢሆኑም ተገቢና ምን ጊዜም ጠቃሚ የሆኑ ወጎችም ነበሩ። በዚህ ረገድ አንዳንድ ሰዎች የነበሩት ልማዳዊ ወጎችን ያለ ምንም ሂስ እንዳለ ልንኮራባቸው የሚገቡ ወጎች ናቸው ማለታቸውና አንዳንድ የምራባዊው ዘመናዊነት ላይ ጫና የሚያደርጉ ደግሞ ልማዳዊ ወጎችን መሳ በመሳ “ኋላቀር” ብለው መደፍጠጣቸው ተገቢ አይደለም።

ይህ ሁኔታ የሚያሳየው አገሪቱ የሽግግር ጅማሮ ላይ አንደ መሆኗ በባህልም ረገድ ሽግግር ላይ እንደነበረች ነው። የዓለም ሁኔታ በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በማያወላዳ መንገድ መላው ዓለም ወደ ዘመናዊነት ዓለም ለመግባት ሽግግር ላይ ነበር ማለት ይቻላል። እዚህ ላይ እንደ ሶሻል ሲስተካፒታሊዝምም ሶሻሊዝምም የዘመናዊ መንግት ፕሮጀክቶች መሆናቸውን መገንዘብ ያስፈልጋል። በሁለቱ ሶሻል ሲስተሞችል በነበረው እሽቅድድም በተለይም የካፒታሊስቱ ወገን ተሰሚነቱን ከሚያስፋፋበት ዘዴ አንደኛው ምራባዊነትን በባህላዊ ዘዴ ማራገብ ነበር። በዚህ ረገድ የምራቡ ዓለም መሪ የሆነው ዩናይትድ ስቴትስ በሆሊድ ፊልሞች፣ በሮክ ዘፈኖች፣ በሚዲያ፣ በመጽቶች፣ ፋሽን ዲዛይኖች እንዲሁም በዘመናዊ ትምህርትና በሌሎችም ባህል ነክ ዘዴዎች በአንድ በኩል እንደ አሜሪካ ሞክራሲና ነነት የሰፈነበት፣ የለጠነ፣ ሁሉም በሽ በሽ የሆነበት፣ እንዲያውም ወርቅ የሚታፈስበት እስኪመስል ድረስ እጅግ መጠነ ሰፊ ባህላዊ ዘመቻ ሲያደርግ በሌላ በኩል ደግሞ ሶሻሊስት ነን በሚሉ አገሮች (በጊዜው ሶቭየት ብረት፣ ቻይና፣ ወዘተ.) ውስጥ ያለውን ት “የኮሙኒስት ት” እያለ የማጥላላትና የማበሻቀጥ ዘመቻ አካሂዷል። ይህንን ሲያደርግ በራሱ አገር ውስጥ ለሰብዊ መብት የሚታገሉትን ቀደም ሲል በባርነት ተሸማቅቀው የነበሩትን አፍሮ አሜሪካኖች፣ የሶሻሊስት ት የፈለጉትን ሁሉ እያሳደደ እያሰረና እየገደለ ነበር። ይኛውን ድርጊቱን ግን በምንም ዓይነት አይጠቅሰውም።

ሶሻሊስት ነን የሚሉትም በዚያው ልክ የድሮ ት ናፋቂ፣ የአሜሪካ ቡችላ እያሉ በርካታ ሰው አቃይተዋል፣ ገድለዋልም። አሁን እንደ ኢትዮጵያ ያሉት አገሮች ደግሞ የነዚህ ሁለት ኃያላን ወጎች መፋለሚያ ሆኑ። የንጉ መንግት የዩናይትድ ስቴትስ ተከታይ ስለነበር በአገሪቱ ገንኖ የነበረው የውጭ ወግ የአሜሪካኖቹ በተለይም የሆሊድ ወግ ነበር። ልማዳዊ ወጎችን ይፈታተኑ ከነበሩት አንደኛው ይየአሜሪካው ወግ ሆነ። የዚህ ወግ ነብራቁ በብዙ መንገድ ይገለጽ ነበር። ምሁሩ የአሜሪካውን አመለካከት ይዞ ይ ነው መንገዱ ይላል፣ ሚዲያው የዜናና የትንተና ምንጩ የምራቡ ሆነ፣ አንዳንድ ከሆሊድ ፊልሞች ቲፎዞነት ወደ ሙዚቃ የገቡትም ዘፋኞች ኤልቪስ ፕሪስሊ ነን አሉ። በአጭሩ ምራባዊነት እንደ ባህል እንዲህ በመሰለ ጥራዝ ነጠቅነት ገለጽ ነበር። ይህ ሁሉ ሲሆን ከአገሪቱ ዝቦች 90 መቶ የሚሆነው ይኼ የምራቡ ባህላዊ ወረርሽኝ ያልነካው ወይ ገበሬ ወይ አርብቶ አደር ነበር። በዚህ ሁኔታ ውስጥ ነው የደርግ አገዛዝ የመጣው።

የ17 ዓመቱ የደርግ አገዛዝ ይኼን የምራቡን ባህላዊ ወረራ ከላይ በፖሊሲና በፕሮፓጋንዳ ደረጃ ሊቀይረው ቢሞክርም ራሱ በዝቡ ዘንድ እጅግ የተጠላ ስለነበር እንዲያውም “የማያውቁት አገር ይናፍቃል” በመሰለ በርካታ ሰው ጭራሽ የምራቡ በተለይም የአሜሪካ ናፋቂ ሆነ። በወያኔ ጊዜ ደግሞ አገዛዙ የምራቡ ደጋፊ ነኝ በማለቱና “የሶሻሊስቱ” ዓለምም ስላበቃለት ለምራቡ ልማድ ማጎብደዱ በአንድ ጊዜ ተመነደገ። በእዚያ ላይ ዩናይትድ ስቴትስ ዲቪ የሚባል ፕሮግራም ጀምሮ ሰዎችን እያወዳደረ በነ ወደ አሜሪካ ያግዝ ጀመር። አሜሪካ ከመቅበት ወርቅ “የሚታፈስበት” ሆነ። እዚያ የሄዱትም በአብላጫው ስለዓለም ታሪክና የፖለቲካ ሁኔታ እንዲሁም ስለአሜሪካ ታሪክና ፖለቲካ ራሱ በቂ ግንዛቤው ያልነበራቸው ስለነበሩ አዕምሯቸው በአሜሪካ የአመለካከት ሳሙና የታጠበ ሆነ። ገንዘብ እያጠራቀሙ ወደ አገር ለረፍት ሲመጡ በዚህ ደሃ ዝብ ላይ ጉራቸውን ነፉበት፣ የወላጆቻቸው ቤት እያለ ትናንት የኖሩበትን ቤት ረሳነው በመሰለ ያለ ሆቴል አያርፉም። በተለይም ወጣቱ ይን እያየ ዓላማውም ህልሙም አሜሪካ መግባት ሆነ።

ይኼ ሁሉ ሲሆን ማበራዊ ዳይናሚክሱ ደግሞ ምን ንደ ደረሰ ማየት ያስፈልጋል። በደርግ እጅግ ግፈኛ አገዛዝ ምክንያት በተለይም የቀይ ሽብር ብሎ አገሪቱን በሽብር ሲገዛ ያደረገው እጅግ ዘግናኝ ግድያና ድብደባ በሰል መተማመን እንዳይኖር አደረገ። አለመተማመኑ ከፖለቲካ ነ ስላደረገ በሰላም ለመኖር ዓይነተኛ ባህላዊ ወግ ሆነ። ከጣያን ጦርነት ጀምሮ የተገነባው በባልንጀራ መል የነበረው መተማመን ተነነ። ተማምነው ለአገራቸውና ለዝባቸው ነነትና ሞክራሲ የታገሉት የተረፋቸው መረሸንና መገረፍ ሲሆን በሰላም የመኖር አማራጩ እንዲያም ሲል ኑሮን ለመግፋት የሚያዋጣው ማጎብደዱ ሆነ። ሳያምኑበት ለደርግና ለባለልጣኑ ለቀበሌ ሊቀመንበር ሳይቀር ማጎብደዱ “የሚያዋጣ” ሆነ።

በደርግ ጭፍጨፋ አያሌ ምሁራን ስላለቁ ወይም ወደ ስደት ስለሄዱ በአገሪቱ የውቀት ክፍተት ተፈጠረ። ምሁር ነኝ የሚለው ራሱ አጎብዳጅ ሆነ። በወያኔም ጊዜ ይኼው አጎብዳጅነት ቀጠለ። ወያኔም የሚያጎበድዱለትን እንጂ ሳባቸውን የገለጹትን ስለማይፈልግ የአጎብዳጅነት ባህሉ ቀጠለ። ያጎበደደ ይወጣለት ጀመር። በቂ ትምህርትና ልጠና የሌላቸው የወያኔ ባለልጣናትና ካድሬዎች ኢትዮጵያን የምታህል አገር ሲገዙና ሲፈልጡ ከተጠቀሙበት መንገድ አንደኛው ለአገዛዛቸው እንዲመቻቸው ካረቀቁት ገመንግት በላይ ያልታወጀ ‘ግ’ ነበራቸው የጫካ ግ (Law of the Jungle)። ሙስና ለመፈጸም ጉ ሳያመች ሲቀር በጫካው ግ ብዙ ነገር ተርቷል በቂ ትምህርት እንደሌለው እየታወቀ ካድሬው አጭበርብሮም፣ ገዝቶትም ዲግሪ በዲግሪ ሆነ። በተለይም ቢሮክራሲ ውስጥ የተሰገሰገው ንስ ከበርቴ ይህችም አለች ለካ በመሰለ በተራው ዲግሪ በዲግሪ ሆነና የቢሮክራሲው በር እንዲከፈትለት አደረገ። ይህ እንደራ ሲታወቅ በማጭበርበር አርት የተካኑ ሰዎች ብቅ እያሉ ያልሆኑትን ነን እያሉ ልጣንም ብትም አካበቱ። ከጥቂት ዓመታት በፊት አንድ በዚህ የማጭበርበር ዘዴ የተካነ የባለጌ ሊቅ ‹‹ፕሮፌሰር ነኝ፣ አለቃዬም ኦባማ ነው›› ብሎ ስንት ጉድ እንደራ ይታወቃል።

እንዲህ ያለው ሌብነት እየራ ሲታይ በርካታ ሰው ተጨመረበት። ዲግሪ፣ ሰርቲፊኬት፣ የመንጃ ፈቃድ እንዲሁም ሌላውም ማመሳከሪያ ሁሉ በጉቦ ማውጣት ልማድ ሆነ። እንደ ነውርም መቆጠሩ እየቀረ ሄደ ሁሉም እያረገው ነዋ! ይህ አመለካከት ሰ የተለየ ባህ እንዲኖር አደረገው። በቀደም ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ሰ የማይታመን ሆነ ቅሌታሙ በዛ፣ የመንግራተኛው ራውን እንዳያጣ እንጂ ለአገሩ መራት የሚለው በአዕምሮው እንዳይኖር ሆነ አስመሳይነት፣ ያልሆነውን ሆንኩ ባይነት፣ አጭባርባሪነት ነገ። ባህላዊ፣ ልማዳዊና የወጎቻችን እሴቶች እየተቀየሩ ሄዱ። አሜሪካ ልጆቻቸውን ሊጎበኙ የሄዱ አዛውንት እንኳ ሳይቀሩ ሰዎች ለዘመዶቻቸው እንዲያደርሱላቸው የሰጧቸውን ገንዘብ ስንቶቹ ሳይሰጡ እንደቀሩ ‹‹ሽማግሌው ሳይቀር ቅሌታም ሆኗል›› እስኪባል ራሳቸው እንደበሉት የታወቀ ነው። በአገራችን የነበሩ (አሁንም ትንሽ የቀሩ) የሚያስመግኑ የልማድና የወጎ እሴቶቻችን በእንደዚህ ዓይነት መንገድ ተቀያየሩ።

እንዲህ ያለው የእሴቶች መለወጥ አገር ወዳድ ስሜታችን ላይም ተፅዕኖውን አሳረፈ። አሜሪካን ከማምለክ የተነሳ ምንም ነገር ይሁን ከአሜሪካ ከሆነ ይወደሳል። አሜሪካ የሚኖረውም ኢትዮጵያዊ “ዳያስፖራ” በሚል በተሳሳተ ቅል ተጠምቆ ይወደስና ይመለክ ጀመር። ትናንት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ያልጨረሰው አሜሪካም ሄዶ ሳይማር የጉልበት ራ የሚራው ሁሉ እንደ አዋቂ ታይ ጀመር። ይህንን የሚያውቀው በየሆቴሉና በየሐኪም ቤቱ ራው ሽንት ቤት መጥረግ ወይም በየራንቹ የፈረስ ጥርስ መቦረሽ የሆነው ሜሪካ/ካናዳ ነዋሪ ለረፍት አዲስ አበባ ይመጣና ያቺን ያጠራቀማትን ዶላር በርካሽ እየመነዘረ እንደ ሚሊየር ይታይ ጀመር። አሜሪካ እግሬ ይግባ እንጂ እገሌ እንዲህ ከሆነ እኔማ ብዙ ነገር መሥራት እችላለሁ የሚለውም ወጣት በዛ። ስለዚህም በየትም ይሁን በየት አሜሪካ ግባ እንጂ እያሉ ወላጆች ሁሉ ሳይቀሩ ልጆቻቸው በደንበር አሻጋሪ ወንጀለኞች አሜሪካ እንዲገቡ ገፋፉና ብዙ ወጣት በየበረሃውና (ሳሃራ) በየባህሩ (ሜዲራኒያን) ቀረ።

እጅግ አድርጎ በሚያስቅ ወይም በሚያበግን (እንደ ተመልካቹ ስለሆነ) መንገድ ከአሜሪካ ስለመጣ እንደ አዋቂ እንዲያስቆጥር ሙከራ በዚያ ሰሞን የተደረገ ነበር። “በአስቂኝነቱ” በሚታወቀው በሰይፉ ፋንታሁን ሾው አንድ ዜ ኤሊያስ ተባበል የተባለ ዘፋኝ እንግዳ ሆኖ ቀረበ። ዘፋኙ አሜሪካ ከሰላሳ ዓመት በላይ ቆይቶ መምጣቱ ነው። እና እስኪ ገጠመኝህን ተናገር ተብሎ ዘፋኙ ተጠየቀ። ኤሊያስ ሆዬ በአንድ ወቅት ሱፐርማርኬት (ፓርትመንት ስቶር ነው የሚባለው እዚያ) የሆነ ነገር ገዝቶ ለመክፈል ወረፋ ሲጠብቅ ከአንድ አፍሮ አሜሪካዊ ጋር ይላከፋል። አሜሪካኑ ‹‹ጮኸ ጮኸና አላቆም ሲለኝ መንኪ (ዝንጀሮ) አልኩትና አሳበድኩት›› ብሎ በድል አድራጊነት ያንን ጥፍር ውስጥ የሚያስገባ እጅግ አሳፋሪ ገጠመኝ አወራና አረፈው። ኤልያስ ‹‹አገሬ ከተመለስኩ ደርግ ሊበላኝ ሊሰለቅጠኝ ይችላል›› ብሎ ለምኖ ግሪን ካርድ ያገኘ ነው። እንዲህ ያለ ሰው አሜሪካኖችን አመግኖና አክብሮ እንደመኖር እጅግ አያፊ በሆነ መንገድ አንደኛ አፍሮ አሜሪካኖችን መሳደብ በራሱ የቅሌት ቅሌት፣ የበላበትን ወጪት ሰባሪነት ነው። ሁለተኛ አንድ አፍሪካዊ አንድ አፍሮ አሜሪካንን ልክ አንደ ኬኬኬ ፋሺስት ዘረኞች “ዝንጀሮ” ብሎ መሳደቡሱን የዓለም ድንቁርና ከማሳየት ያለፈ ሌላ ነገር የለውም። ኤሊያስ ነጭ የሆነ ዘረኛ ቢያጋጥመው እሱንም “ሄይ ኒገር ቦይ” ሊለው እንደሚችል አለማወቁ ራሱ ያሳዝናል። ‘ዳያስፖራው’ ኤልያስ ከአሜሪካ ስለመጣ ብቻ ራሱን አዋቂ አድርጎ ስለቆጠረ አላውቂነቱን አውጆ አረፈው። ኤልያስ እንኳ አላዋቂ ሆኖ ነው እንበል፣ የሚገርመው ደግሞ ‘ስቂኙ’ የሰይፉ ራ ነው። ያ ፕሮግራም የቀጥታ ርጭት (ላይቭ) እንዳልነበረ ሁሉ ኤዲት መደረጉ አልቀረም። ግን ሰይፉም የኤልያስን አላዋቂነት ተጋርቶ ይንን አሳፋሪ ገጠመኝ ተመልካቹን “እንዲያስቅ” እንዳለ ለቀቀው። 

ስለዘረኝነት ካወራን አይቀር በብዙ አፍሪካ አገሮች ‹‹እናንት ኢትዮጵያውያን ዘረኞች ናችሁ›› የሚሉን መብዛታቸውን ማስተዋል ተገቢ ነው። አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ነነቷን ጠብቃ የጣያን ፋሺስቶችን ድል ያደረገች መሆኗን ስለሚያውቁ ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ክብር አላቸው። ይህንን ክብር ግን እኛው ራሳችን እየሸረሸርነው ነው። ደርግ ሊበላኝ ነው ወይም ወያኔ ሊገለኝ ነው ብሎ የፖለቲካ ጥገኝነት አግኝቶ ተከብሮ በሚኖርበት አገር አመግኖ እንደ መኖርእዚያን አገር ሰው “ባሪያ” የሚለው ኢትዮጵያዊ በርካታ ነው። ለምሳሌ ኡጋንዳ ውስጥ በተለይም ካምፓላ በርካታ ኡጋንዳውያን ከኢትዮጵያውያን የሚሰነዘርባቸውን የዘር ጥቃት እያስተዋሉ የህንዶቹ ዘረኛነት ሳያንስ ኢትዮጵያውያንን ያመጣብን ሙሴቬኒ (ፕሬዚዳንቱ) በመሆኑ ‹‹ቆይ ያ ጊዜ ሲመጣ እናሳችኋለን›› የሚሉ በርክተዋል።

እንዲህ ያለው አመለካከት በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ብቻ ሳይሆን እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥም የሰፈነ ነው። ይኼን አ ማለት አይቻልም። እንዲያውም ምሌ 27 ቀን 2012 ዓ.ም. በፋና ቴሌቪዥን በሚተላለፈው ተወዳጁና አስቂኙ “ዘጠነኛው ሺ” በተባለው ድራማ ላይ አቡሽን ሆኖ የሚራው ወጣት ፍቅረኛው ስላኮረፈችው በተለምዶ “ለምቦጭሽን አትጣይ” የሚለውን ትቶ ጥፍር ውስጥ በሚያስገባ ዘረኛ መግለጫ “እንደ ናይጄሪያ ከንፈር አደረግሽው” ዓይነት ብሎ አረፈው። ይኼን ሳይ ‹‹የዚህ አገር ቴሌቪዥኖች ኤዲሮች የሏቸውም እንዴ?›› እንድል አድርጎኛል።

ውይይት ላይማ ማነው ደፍሮ ‘ከአዋቂው’ (በስህተት ዳያስፖራ የሚባለው) ጋር የሚከራከረው? በርግጥም ትንሽ ትምህርት ያገኘው የተማረውን አካብዶ አካብዶ እንደ ከፍተኛ ስኮላር እየተቆጠረ በየሚዲያው የሚጠየቀው፣ ቃለ ምልልስ የሚደረግለትም ከሱ ጋር ነው። ስሙን ሰምተን የማናውቀው አሜሪካ አለ የተባለ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ተመራማሪ ነው እተባለ ይደመጣል። ሚዲያውና ሌላውም ማመሳከር የሚባል በአዕምሯቸውም ሽው አይል። በርግጥ ሰውየው/ሴትየዋ እንደምትለው ‘ኤክስፐርቲዙ’ አለው/አላት ወይ ተብሎ መጠየቅ ነውር ይመስል ሚዲያውም፣ የመንግት ቢሮዎችም አይጠይቁም። ለምሳሌ እስካሁን ድረስ እንደ ታላቅ ኮኖሚስት የሚታይና በሚዲያው ቃለ ምልልስ የሚደረግለት አንድ ግለሰብ እሱ አንደሚለው ካሊፎርኒያ ካለ አንድ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪ እንደሌለው ዩኒቨርሲቲው ይንን ግለሰብ እንደማያውቀው አሜሪካ ያለው ጋዜጠኛ አበበ ገላው ደርሶበታል። ሌላ ጊዜ ደግሞ አንድ የከባድ ሚዛን ቦክሰኛ ነኝ፣ አሜሪካም በዚህ በዚህ አሸንፌያለሁ ብሎ እንደ ተለመደው አሜሪካ አምላኩ የሆነው ሚዲያ አሞካሽቶ አሞካሽቶ በኋላ ሰውየው የወጣለት ቀጣፊ፣ ቦክሰኛም እንዳልሆነ ታወቀ። ካምፓላ (ጋንዳ) ከጥቂት ዓመታት በፊት አንድ ሌባ ከካናዳ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ካናዳ እንዲሄዱ ለመርዳት ነው የመጣሁት ብሎ ስደተኛውን የማመልከቻ ፎርም እያስሞላ ጠቀም ያለ ገንዘብም እያስከፈለ በደንብ ከነደፋቸው በኋላ አንድ ጠዋት ተሰወረና ያ ሁሉ ስደተኛ ገንዘቡን ተበልቶ ቀረ። እንዲህ የመሳሰሉ የቅጥፈት ራዎች ከላይ ከጠቀስነው የባህላዊ እሴቶች መቀየር የመጣ ነው። አንድ ፈረንጅ ከሰሞኑ ‹‹እናንት ኢትዮጵያውያን ጥሩ ሰዎች ነበራችሁ አሁን ግን. . .›› እንዳለው ነው።

የጣያን ፋሺስቶች አገራችንን ወርረው በዝባችን ላይ ካሄዱት ጭፍጨፋና ያደረሱት ግፍ በድ ያን ወረራ የነበረው ትውልድ በአገር ወዳድነት ተኮትኩቶ ያደገ ነበር። አገር ወዳድነት አገር ስትወረር ብቻ የሚገለጽ እሴት አይደለም። አገር ወዳድነት ሁልጊዜ ለአገር ጥሩ ነገር ማሰብና መራት ማለት ነው። በዚህ ረገድ አገር ሲባል ተራራውና ንተረሩ አይደለም ዝቡ ነው። ስለዚህ በሰላምም ጊዜ አገር ወዳድነት ለዝብ ጥሩ ነገሮችን መራትን ይመለከታል። ወጣቶችም በዚህ አቅጣጫ መኮትኮት አለባቸው። ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ማንነት መኩራት አለባቸው። በተለያየ የብር ማንነታቸውም መኩራት አለባቸው። አንደ ቀስተ ደመና የተዥጎረጎረው ባህላዊ እሴቶቻቸው ማንነታቸውን ይገልጻል። የወላይታውን ባህላዊ ልብስና ጭፈራ የሌላው ብረሰብ አባላት እንደ ራሳቸው አድርገው መውሰድ፣ ነሱም የሌላው እንደሆነ መቁጠር ይኖርባቸዋል። ለጠኑ የተባሉት ፈረንጆች እኮ እንዲህ ያለው አንደ ቀስተ ዳመና የተዥጎረጎረው ባህልና ማንነት ያስደንቃቸዋል። እኛ ደግሞ በዚህ መኩራት አለብን። የአንዳችን ባህል ከሌላው ይበልጣል ሳንል ሁሉንም በእኩልነት ማየት አለብን።

ሁለተኛው አገር ወዳድነት የሚገለጸው ለፈረንጁ ባህልና እሴቶች አለማጎብደድን ይመለከታል። በራሳችን ባህል፣ ልማድ፣ ወጎችና እሴቶች መኩራት አለብን እንጂ የኛ እሴቶች ከፈረን ‘ዝቅ ያሉ’ ወይም ‘ያልለጠኑ’ ናቸው ብለን በፍም ማመን የለብንም። እንዲህ ስንል በርግጥ ከፈረንጁ እሴቶች ደግሞ ጠቃሚ ጎኖች የሉም ማለት አይደለም። ለነገሩ በዓለም ያሉ ዝቦች በሙሉ የራሳቸው ባህላዊ እሴቶች አሏቸው። የኛ ባህላዊ እሴቶች በሙሉ አዎንታዊ እንዳልሆኑት ሁሉ በሌሎችም ባህሎች የፈረንን ጨምሮ ጎጂ እሴቶች አሉ። የማንኛውም ዝብ እሴቶች አዎንታዊ ጎኖች እንዳሉት ሁሉ ለኛ የሚጠቅሙ ከሆነ እነዚህን እሴቶች መጋራት እንችላለን። የምንጋራው የፈረንጁን ብቻ አይደለም።

ከላይ እንደጠቀስነው በሁለቱ ኃያላን መንግታት የሽኩቻ ዘመን የአሜሪካው ኃያል ተሰሚነቱን ለማስፋፋት ባህላዊ ዘመቻም እንዳደረገ ገልጸናል። በዚህም በመላው ዓለም “አሜሪካ አምላኩ” የሆኑ ግለሰቦችን ማፍራት ዓላማው ነበር። ዘዴው የተለያየ እንደሆነም ጠቅሰናል። ከነዚህ አንደኛው በጽሑፍና (ፊልሞች፣ ጋዜጣና መጽት፣ ሙዚቃ፣ ወዘተ.) በሚዲያ በኩል የሚደረገውን ነው። በነዚህ አውታሮች ከሚነዛው ፕሮፓጋንዳ አንደኛው ውበትን የሚመለከት ነው። ቆንጆ የሚባለው ቆዳው ያልጠቆረ እንዲያውም ነጣ ያለ፣ አፍንጫው ቀጥ ሰልከክ ያለ፣ ጉሩም ሉጫ የሆነ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል። ንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች (ምናልባት ኒጄር ውስጥ እንዳለው አንድ የፉላኒ ብረሰብ በተቀር)  ባለው ባህላዊ ወግ ደግሞ ቆንጆ መሆን የሚጠቅባቸው ሴቶች ናቸው። ሴቶቹም ቆዳቸው የነጣ፣ አፍንጫቸው ሰልካካ፣ ጉራቸው ሉጫ እንዲሆን መከራቸውን ያያሉ። የቆዳ መንጣቱና የአፍንጫው ሰልካካነት እስካሁን በሰው ራሽ መንገድ ሊቀየር ተሞክሮ ብዙ ጉዳት አስከትሏል። ጉር ግን ተፈጥሮ ቢሆንም ሰው ራሽ ወይም ደግሞ የታከመ ሂውማን ሄር ተርቶለታል። ቁንጅናን ፈረንጅ አምሯችን ውስጥ እንደ ቀረቀረው በሉጫ ጉር ተርጉመን ሴቶቻችን ይው ለሰው ራሽ ወይም ሂውማን ሄር ሲጋደሉ እናያለን። አፍሪካዊ ማንነታችን አሳፍሯቸው ነው? ወይስ ያ ዊግ ወይም ሂውማን ሄር የሷ እንዳልሆነ መንገደኛው ሁሉ እያወቀ “የሷ ያልሆነውን የሷ ነው” እንዲባል ነው? በጣም የሚያሳስበው ግን በባህልና በባህ ተምሳሌት መሆን የሚገባቸው የመንግት ባለልጣናት የሆኑ ሴቶች ሚኒስትሮችም ጭምር ይህንኑ ሂውማን ሄር መጠቀማቸው ነው። ከጥቂት ዓመታት ጀምሮ በአገራችን ገንኖ ያለ ዋነኛ የጉራማይሌ ተምሳሌት ይ ሴቶቻችን የሚራኮቱበት ሰው ራሽ ጉር ነው። ሌላው በቅርብ የተጀመረው ጉራማይሌ ደግሞ ሴቶች ቆዳቸው እንዲነጣ የሚጠቀሙበት ክሬም ተፈጊነቱ እየተስፋፋ መምጣቱ ነው። ይህ ተግባር በሴቶች ላይ ጉዳት በማስከተሉ እንደ ጋና ያሉ አገሮች ከልክለዋል። በኢትዮጵያም በዚህ ጉዳይ መንግት ጣልቃ ገብቶ ብዙ ጉዳት ሳይደርስ ማስቆም መቻል አለበት።

ጉራማይሌው በሴቶች ብቻ የሚገለጽ አይደለም። ወጣት ወንዶችም የፋሽን ሰለባዎች ናቸው። ከጉር ይጀምራል። የአፍሮ አሜሪካን ራፕ ዘፋኞችን ተከትለው ጉር ማንጨብረር፣ በጣም አስቂኝ በሆነ ስታይል መቆረጥ፣ አስቂኝ በሆነ ስታይል ሰላም መባባል፣ ወዘተ. ሌላው አስቂኝ ስታይል ደግሞ ከጉልበት በታች ሹጥጥ ያለ ሱሪ መልበስ ነው። አንዳንድ በመነሳት ላይ ያሉ ዘፋኞች ንዲህ ያለ ሱሪ ለብሰው በቴሌቪዥን ይታያሉ። በዚህ ጉዳይ ላይ የአለባበስ ነ ምግባር በቴሌቪዥንም መኖር አለበት።

ሌላው የጉራማይሌ አባዜ ደግሞ ብዙም ያልተነገረለት ስምን አሜሪካዊ የማድረግ አባዜ ነው። በተለይ ታዋቂ የሆኑ ግለሰቦች ስማቸውን አሜሪካዊ አድርገው ምንም ሂስ ሳይቀርብባቸው ሲቀር ወጣቱ ሁላ ተነስቶ ስሙን በተቻለ መጠን አሜሪካዊ ሊያደርግ ቆረጠ። የታወቁ ሰዎች ብረሰባዊ ላፊነት (Social Responsibility) ስላለባቸው ከህ ያለ ከንቱ ራ በመቆጠብ በራሳቸው ማንነትና በባህላቸው መኩራታቸውን በማሳየት ተምሳሌት መሆን አለባቸው።

ስለኢትዮጵያ እየዘፈኑ ስማቸው እንኳ ኢትዮጵያዊ እንዳይሆን ማድረግ እርስ በሩስ የሚቃረን ነው። በዚህ ምክንያት የቴዎድሮስ ካሳሁን አባት አቶ ካሳሁን መሆናቸው እስከዚህ አይታወቅ ይሆናል ሰውየው “ቴዲ አፍሮ” ነኝ ስላለ። ጎሳዬ የሚባለው ደግሞ “ጎሲ ነኝ” አለ። ዮሴፍም “ጆሲ” ሆነ፣ አንዱ ደግሞ ትንሳን የመሰለ ቆንጆ ስም ይዞ “የለም. . . ቲኑ ነኝ” አለ (እውነትም “ቲኑ”!) ሌሎችም በርካቶች አሉ። ከሁሉ የሚገርመው ሚዲያው ራሱ እነዚህን ቅል ስሞች እንደ ደንበኛ ስም ተቀብሎ በተለይ በቴሌቪዥን ያስተዋውቃቸዋል። አንዱን ተዋናይ “ቤቢ” ይለዋል። ሌሎችም በርካቶች አሉ።

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ግኘት ይቻላል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...