Friday, March 24, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ በአፍሪካ ኦሊምፒክ ማኅበር ዕውቅና አገኙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ በአፍሪካ ኦሊምፒክ ማኅበር ዕውቅና አገኙ

ቀን:

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ለስፖርትና ለኦሊምፒክ እንቅስቃሴ ላሳዩት ምሳሌነት ከአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር (አኖካ)፣ ‹‹አኖካ ኦርደር ኦፍ ሜሪት›› (ANOCA ORDER OF MERIT) የተሰኘ ዕውቅና አገኙ፡፡

የዕውቅና ሽልማቱን ወደፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚያመቻቸው ቀንና ቦታ ለመስጠት እየጠበቁ መሆኑን የአኖካ ፕሬዚዳንት መግለጻቸውን መቀመጫው ናይሮቢ ያደረገው ካፒታል ኤፍኤም በድረ ገጹ ዘግቧል፡፡

ይህ ሽልማት እንዲሰጥ የተወሰነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ የኢትዮጵያን ስፖርት ለማዘመን፣ ከአገሪቱ የልማት ዘርፎች እኩል እንዲታይና እንዲራመድ ማስቻላቸውን ጠቅሰው፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና ስፖርት ኮሚሽን በጋራ ለአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ባሳወቁት መሠረት መሆኑን የአኖካ ፕሬዚዳንትና የኢንተርናሽናል ኦሊምፒክ ኮሚቴ አባል ሙስጠፋ ቤራፊ የላኩት ደብዳቤ ያሳያል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለኢትዮጵያ ቶኪዮ ኦሊምፒክ ቡድንና ለኦሊምፒክ አካዴሚ ግንባታ ሦስት ቢሊዮን ብር ለመስጠት ቃል መግባታቸው ይታወሳል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...