Tuesday, September 26, 2023

ማረሚያ

- Advertisement -spot_img

በብዛት የተነበቡ

ነሐሴ 6 ቀን 2012 ዓ.ም. ‹‹የመከላከያ ሚኒስትሩ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸው መነሳታቸው ታወቀ›› በሚል ርዕስ ያወጣነው ዘገባ ሙሉ በሙሉ የተሳሳተ መሆኑን የሪፖርተር ጋዜጣ የዝግጅት ክፍል እየገለጸ፣ አንባቢያንንና የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤትን ይቅርታ ይጠይቃል፡፡ የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ መገርሳ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትን በመወከል አሁንም የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል መሆናቸውን የክልሉ ምክር ቤት የገለጸልን ሲሆን፣ ዘገባውን በዚሁ መሠረት ማረማችንን ለአንባቢያን በትህትና እናስታውቃለን፡፡ የክልሉ ምክር ቤት ሐምሌ 19 ቀን 2012 .. ባካሄደው 12 መደበኛ ጉባዔው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል ሆነው እንዲተኩ አቶ ፈቃዱ ተሰማ፣ አቶ ሳዳት ነሻና አቶ አብዱል ሐኪምን የመረጠ ቢሆንም፣ እነዚህ አባላት በትምህርት ምክንያት የተጓደሉ ሦስት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላትን እንዲተኩ መሆኑን ጨፌው አስታውቋል። በትምህርት ምክንያት በተጓደሉትና እንዲተኩ የተወሰነባቸው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነትም አቶ ሙክታር ከድርአቶ እሸቱ ደሴና አቶ በከር ሻሌ መሆናቸውን ጨፌው ካደረሰን መረጃ ለመረዳት ችለናል። ጨፌው ለሪፖርተር የላከውን ደብዳቤ ሙሉ ይዘት ለማንበብ እዚህ ይጫኑ::

spot_img
- Advertisement -

ትኩስ ጽሑፎች

ተዛማጅ ጽሑፎች

- Advertisement -
- Advertisement -