Tuesday, November 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊከመማር ማስተማር እስከ ደሃ ጎጆ                

ከመማር ማስተማር እስከ ደሃ ጎጆ                

ቀን:

ተጎሳቁለዋል፡፡ ጉዳታቸውን ሰውነታቸው ይናራል፡፡ ዕድሜያቸው ወደ ሰባዎቹ የሚጠጋው አቶ ገና አማረ አላገቡም አልወለዱም፡፡ ከደርግ ጊዜ ጀምሮ መሬት እየተኙ እንደኖሩ ይናገራሉ፡፡ ለዕለት ጉርስ የሚሆናቸውን ገንዘብ ሳር እየሸጡ ቢያገኙም፣ ከ40 ዓመታት በላይ ያሳለፉት ቤት ውስጥ አልነበረም፡፡

የአካባቢው ነዋሪዎች ልብ ሸራም እየሰቸው ክረምትና በጋን ፀሐይና ዝናብን በሸራቸው ውስጥ ለዓመታት አሳልፈዋል፡፡ በደቡብ ክልል የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ጂንካ አልጋ ቀበሌ ነበር ያገኘናቸው፡፡ ስናገኛቸው  አንድ ክፍል ቤት ውስጥ ብቻቸውን ተቀምጠው እየተከዙ ነበር፡፡ አቶ ገና የሚጎበኛቸው ልጅ የላቸውም፡፡ ከጎናቸው የምትሆን ባለቤትም እንዲሁ፡፡ ይህ ደግሞ ሕይወትን በብቸኝነት እንዲያሳልፉ አድርጓቸዋል፡፡

ያለፉት ሁለት ዓመታት ግን ለእሳቸው መልካም ነበር፡፡ ከሦስት ዓመ በፊት የተቋቋመው ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ሒደቱ በተጨማሪ ወደ ማኅበረሰቡ በመውረዱ ተጠቃሚ ካደረጋቸው ሰዎች አንዱ ሆነዋል፡፡

አቶ ገና ለዓመታት ከኖሩበት የሸራ መጠለያ ወጥተው ቤት ውስጥ ገብተዋል፡፡ ‹‹ማንም ያላየኝን ዩኒቨርሲቲው ነው ያየኝ፡፡ ከማረፊያዬ ባለፈ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ዘይትና የመሳሰሉትን ቀለብ ይሰጡኛል፡፡ ለዚህም አመግኜ አልጨርስም፡፡ አሁን ከተወለድኩ ሁለት ዓመት ሆኖኛል፤›› ይላሉ፡፡

አቶ ገና ቤት ማግኘታቸው ብቻ አይደለም ደስታቸው፡፡ ቢያንስ በተወሰነ ጊዜ ቀለብ ለመስፈር የሚመጡ ያገኟቸዋል፣ ያዋሯቸዋል፡፡ ይህ ለእሳቸው ሌላው ደስታ ነው፡፡ 

በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኘው ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት መስጠት ከጀመረ ዘንድሮ ሰት ርሷልበነዚህ ዓመታት ውስጥ የችግረኞችን ጎጆ ከመዳሰስ ባለፈ በዞኑ ያሉ ወረዳዎችን የተለያዩ አካላትን ጎብኝቷል፡፡ ዩኒቨርሲቲ ከተማሪዎቹ ጋር በመሆን አቶ ገናን እና ሦስት አቅመ ደካሞችን ከችግር አንስቷል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ገብሬ ይንቲሶ፣ ‹‹የሠራነው ሐሳብ ካልሆነ በስተቀር የሚያኩራራ አይደለም፡፡ በአካባቢያችን በርካታ አቅመ ደካሞች አሉ፡፡ ሥራችንም የሚቀጥል ይሆናል፤›› ብለዋል፡፡

በመማር ማስተማር ሒደቱ በምርምር ጉዞው ከተቋቋመበትና ካገለገለበት ዕድሜ አንፃር በርካታ ሥራዎችን ያከናወነው ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በማኅበረሰ አገልግሎቱም የሚበረታታ ሥራ ማከናወኑን ሪፖርተር በቦታው ሄዶ ለማረጋገጥ ችሏል፡፡

አቶ አርጋቸው ቦቸና የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ ሰብ ኮሌጅ መምህርና የማኅበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ናቸው፡፡ 2010 .. የተቋቋመው ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማሩን ሒደት ከጀመረ ሦስት ዓመት ቢሆነውም የማኅበረሰብ አገልግሎትና ምርምር ተግባራትን የጀመረው ግን 2011 .. እንደሆነ  ያወሳሉ፡፡ ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በጀት ባለመመደቡ ሥራው ዘግይቶ መጀመሩንም ያክላሉ፡፡

በጀቱ ከተመደበ በኋላ የዳሰሳ ጥናት በማድረግ የትኩረት መስክ ልየታ ወን ለተለያዩ አካላት የአቅም ግንባታ በማድረግ ሰፊ ሥራዎችን ማከናወን ችለናልም ብለዋል፡፡

ከተከናወኑት ተግባራት መካከል ለተቋማት ለተለያዩ ወረዳዎች መረጃን በተደራጀ መልኩ ለማስቀመጥ ይረዳ ዘንድ 300 ኮምፒዩተርና 75 ፕሪንተር ድጋፍ ማድረግ፣ ከተማዋ የብዙ ቱሪቶች መናኸ ከመሆኗ አንፃር ለሆቴል አስተዳዳሪዎች፣ ለአስጎብኚዎች፣ ለምግብ አዘጋጆች፣ ለእንግዳ ማረፊያ አገልግሎት ሰጪዎችና   ለተለያዩ አካላት ሥልጠና መስጠት፣ 35 የመጀመርያሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መሠረታዊ የኮምፒውተር ችሎታን ማስገንዘብና የ950 ኮምፒውተሮች ድጋፍ ማድረግ ከዚሁ ጋር በተያያዘም የመጽሐፍት እጥረት በሰፊው ስለሚታይ በኮምፒውተሮቹ ላይ መጽሐፍ በመጫንና ለተማሪዎች የመጽሐፍ ተደራሽነትን በማረጋገጥ ማዕከል ላይ ካለው ተማሪ ጋር ተወዳዳሪ ማድረግ የሥራዎቹ አካል ናቸው፡፡

‹‹አንድ ቀን ለሕዝቤ›› በሚል መሪ ቃልም ለሦስት አቅመ ደካሞች ቤት ገንብቶ ማስረከብ፣ የከተማዋን አረንጓዴ ልማት ማስፋፋት፣ በገበያዎች አካባቢ የመፀዳጃ አገልግሎቶች መክፈት፣ ትምህርት ቤቶችን ማደስ እንዲሁም ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ ሳኒታይዘር ማምረትና የመመርመሪያ መሣሪያዎችን መግዛት ይጠቀሳሉ፡፡ የአንበጣ ወረርሽኝ፣ የኮሌራ በሽታና የጎርፍ አደጋ በተከሰተ ጊዜም ዩኒቨርሲቲው ድጋፍ አድርጓል፡፡

እንደ አቶ አርጋቸው እነዚህን ተግባራት ለማከናወን 14 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል፡፡ የተከናወኑትን ሥራዎችም እንደ ሞዴል የተመረጡ ቦታዎች ላይ በመገኘት ሪፖርተር ለማየት ችሏል፡፡

የመጀመ መዳረሻችን የነበረው በዞኑ ከሚገኙ ወረዳዎች አንዱ በሆነው የበና ፀማይ ወረዳ ነው። የበና ፀማይ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደሞ በዛብህ ይባላሉ፡፡  ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከመምጣቱ በፊት ምን እየታሰበ ነበር? ከመጣስ በኋላ ምን ዓይነት ውጤቶች ተገኝተዋል? የሚለውን ገልጸውልናል፡፡

ደቡብ ኦሞ ዞን ድንበር አካባቢ ከመሀል ከተሞች በርቀት የሚገኝ ነው፡፡ በዚህ አካባቢ የሚኖሩ በረሰቦች አርብቶ አደሮች ናቸው፡፡ በትምህርት ኋላ ቀር ኅብረተሰብን ያቀፈ አካባቢ ነው፡፡ የአካባቢው ነዋሪ የትምህርት ዕድል በሰፊው አላገኘም፡፡ ነገር ግን ዩኒቨርሲቲው ወደዚህ ሲመጣ ያልተማረው ማኅበረሰብ  ትምህርቱን የማግኘት እንዲሁም ስለ ትምህርት ዕውቀት እንዲጨብጥ አድርጓል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ወደ ዞኑ ሲመጣ፣ ዕድሉ ከተገኘ ከሥር የተማረ የሰው ኃይል እንፈጥራለን ብለን ነበር፡፡ በዚህም ረት እኛ እንደ ወረዳ በርካታ በመንግሥት ሥራም ሆነ ከመንግሥት ሥራ ውጪ ያሉ ሰዎችን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ዕድሉን አግኝተው እንዲማሩ አድርገናል፡፡

የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ማሟላት ላልቻሉ የአርብቶ አደር ልጆች ገንዘብ እየከፈልን ዩኒቨርሲቲ እንዲማሩ ዕድል አመቻችተናል፡፡ በአሁ ሰዓትም ስምንት የአርብቶ አደር ልጆችን ከፍለን እያስተማርን እንገኛለን፡፡ የአመራር አካላት ትምህርታቸውን ከዲፕሎማ ወደ ዲግሪ እንዲያሻሽሉ አድርገናል፡፡ ይኼም ለእኛ አጠቃላይ የተማረን የሰው ኃይል ከመፍጠር አኳያ ትልቅ ዕድል ነው ብለዋል፡፡

የጂንካ ዩኒቨርሲቲ በማበረሰብ አቀፍ እንቅስቃሴው ላይ የወረዳውን አቅም ከማጎልበት ትልቅ ሚናም ተጫውቷል ይላሉ፡፡ ትኩረቱን ከላይ ላለው የተማረ ክፍል ብቻ ሳይሆን ከታች ለሚመጣው ትውልድ ጭምር በማድረግ በወረዳ በሚገኙ ሁለት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የኮምፒውተር ድጋፎች አድርገዋል፡፡ እንዲሁ መጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከዩኒቨርሲቲው ጋር በጋራ ለሚሠሩ ተቋማት ተመሳሳይ ድጋፍ ተደርጓል፡፡ ወረዳ 18 ኮምፒውተሮችም ተበርክቷል፡፡

ከዩኒቨርሲቲው ጋር በመተባበር የኔትወርኪንግ ሥርዓት በመዘርጋት ወረዳ ከወረዳ ጋር ለማገናኘትና ጥናት ለመሥራት እየሠራ ነው፡፡ ‹‹የጥናት ቦታዎችን መርጠናል፡፡ በከተማው አቅራቢያ የሚገኘው ማኅበረሰብም ለጥናት ይረዳ ዘንድ 36 ሔክታር መሬት አዘጋጅቶ ለዩኒቨርሲቲው በነፃ ለማስረከብ ዝግጅት ላይ ይገኛ›› ብለዋል፡፡

አቶ ደሞ ዩኒቨርሲቲ ጉዞ ምንጠብቀው ነገር አለ ይላሉ። ሌሎች ቅርንጫፎችን ቢከፍትና ለየወረዳው በቅርበት ተደራሽነቱን ቢያሰፋ ወረዳ ውስጥ የሚገኙትንና የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው የበኔ፣ ፀማይና ብራይሌ ብሔረሰቦች መታደግና  በኢኮኖሚ የማኅበረሰቡን አቅም ከማጎልበት አኳያም ብዙ ሚና ቢጫወት የሚለውን ያነሳሉ፡፡

ቀጣይ መዳረሻችን በጂንካ ከተማ የሚገኘው የጂንካ ሚሊኒየም ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነበር፡፡ 2001 .. የተመሠረተው ይህ ትምህርት ቤት ሰፊ ቦታ ላይ ያረፈ ነው፡፡ ነገር ግን የያዘው ጥቂት ክፍሎችን ነው፡፡ ዚያ በደረስንበት ሰዓት ቅጥር ግቢ እየታረሰየተለያዩ ዘሮችም እየተበተኑ  ነበር፡፡ ከዘጠነኛ እስከ አሥራ አንደኛ ክፍሎችን የያዘው ይኸው ትምህርት  ቤት 935 ተማሪዎች አሉት፡፡ ነገር ግን ለዚህ ሁሉ ተማሪዎች ያሉት ስምንት ክፍሎች ብቻ ናቸው፡፡ የክፍል እጥረት ለጂንካ ሚሊኒየም ትምህርት ቤት ሥጋት እንደሆነ  የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ካሳሁን ኃይሉ ይገልጻሉ፡፡

ሁለት ዓመታት በፊት ከክፍል እጥረት በተጨማሪ የኮምፒውተር፣ የላይብረሪና የላራቶሪ ቁሳቁሶች እንዲሁም የመጽፍት እጥረት በዋነኝነት ሊጠቀሱ የሚችሉ የትምህርት ቤቱ ችግሮች ነበሩ፡፡ በመማር ማስተማሩ ሒደት ላይም ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሮ ነበር የሚሉት አቶ ካሳሁን ‹‹ነገር ግን 2011 .. በኋላ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ በርካታ ሀብት በመስጠት እነዚህ ችግሮች እንዲቀረፉልን አድርጓል፤›› ብለዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው መማር ማስተማሩ ሒደት እንዲፋጠን 50 ኮምፒውተሮችን በመግዛትና መጽሐፍት በመጫን ለተማሪዎችና ለአስተማሪዎች ሥልጠና በመስጠት የትምህርት ሒደቱን እንዲቀላጠፍ አድርጓል። ተማሪዎች ላይብረሪ ውስጥ ሚጠቀሙበትን 20 ጠረጴዛ፣ 50 የተማሪ ወንበርና ጠረጴዛ የመጽሐፍ መደርደሪያዎች፣ 500 የሚጠጉ ማጣቀሻ መፅፍት አበርክቷል። ለእያንዳንዱ ቢሮ መቀመጫና ጠረጴዛ፣ ለቢሮ የሚያገለግል ሁለት ኮምፒውተርና ፕሪንተር፣ 152 ሺሕ ብር የሚያወጣ የማባዣ ማሽንም አበርክቷል።

እንደ አቶ ካሳሁን ዩኒቨርሲቲ በአካባቢው ራቱ በረሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን አድርጓል። ከክፍል እጥረት ውጪም አብዛኛው ችግራቸው መቀረፉንም ገልፀዋል።

ሁሉም አካል እንደ ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ሁላ ለትምህርት ትኩረት ቢሰጥ ጥሩ ፍሬን ማግኘት እንደሚቻል አቶ ካሳሁን ጠቁመዋል፡፡

ዩኒቨርስቲው በ2011 ዓ.ም. የደቡብ ኦሞ ባህል ፌስቲቫል ጀምሯል። የፌስቲቫሉ ዓላማ በደቡብ ኦሞ ያሉ 16 ብሔረሰቦች ቱባ የሙዚቃ፣ የምግብ እንዲሁም የዕደ ጥበብ ባህል ስላላቸው ይህን ለተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ማስተዋወቅና የገቢ ምንጭ ማምጣት ነው።

የቀይ አፈር ወረዳ ነዋሪውና የወረዳው የቀድሞ አስተዳዳሪ አቶ መለስ ማያ በዩኒቨርሲቲው ሥራ በጣም እንደተደሰቱ ገልጸውልናል፡፡ ‹‹ዩኒቨርሲቲው መከፈቱ ለብዙ ዘመናት በማበረሰቡ የነበሩ ጥያቄዎች መልስ እንዲያገ እያስቻለ ነው፤›› ብለዋል፡፡ የዩኒቨርስቲው ፕሬዳንትም ወደ ማበረሰ ዝቅ ብለው በመግባትና የነበሩ ችግሮችን በመፍታታቸው አመስግነዋል።

የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኢትዮጵያ ከተከሰተ ዩኒቨርሲቲው እጁን አጣጥፎ አልተቀመጠም። ከክልሉ ጤና ኢንስቲትዩት ጂንካ ቅርንጫፍ ራቶሪ ጋር በመተባበር ሳኒታይዘር ማምረት ጀምሯል።

የሳኒታይዘር ማምረቻው የሚገኘው በኢንስቲትዩቱ ራቶሪ ቅጥር ግቢ ውስጥ ነው። የላቦራቶሪው  ተወካይ አቶ መስፍን ታምራት የጥራት ቁጥጥር ኦፊሰር  አቶ ወንድምነህ መርሻ ስለሳኒታይዘር ምርት ማብራሪያ ሰጥተውናል፡፡

የላቦራቶሪው ኃላፊዎች፣ ከጂንካ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ሳኒታይዘር እያመረቱ ጥሬ እቃም  ጂንካ ዩኒቨርሲቲ እጠቀረበላቸው መሆኑን ነግረውናል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ከኬሚስትሪ ዲፓርትመንት ባለሙያዎችም በትብብር እየሠሩ ነው፡፡ 1,000 ሊትር ሳኒታይዘር ለማዘጋጀት አራት ቀን እንደሚፈጅባቸውና ጥራቱ ለም ጤና ድርጅት ያወጣው ፈርት ሟላቱ አረጋግጠው እንደሚያከፋፍሉ  ልጸዋል፡፡ ኦሞ የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ  ሳኒታይዘር በመጀመ ዙር የተመረተው 2,000 ሊትር በነ ብረተሰቡ ታድሏል። ቀጣይ የተመረቱትም በተመጣጣኝ ዋጋ እየተከፋፈ ይገኛ

ዩኒቨርስቲው ከጂንካ ቅርንጫፍ ጤና ራቶሪ ጋር በመተባበር አምስት ሚሊየን ብር ያህል በማውጣት የኮቪድ-19 መመርመ ማሽን በመግዛትና ዚህ የሚሆኑ ግንባታዎችን በማከናወንና ያሉትንም በማደስ ሥራ ሊያስጀምር ነው፡፡ የማሽኑ ሲጀምር 24 ሰዓት ውስጥ 500 በላይ ሰዎች ለመመርመር እንደሚያስችል ተገልጿል።

የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመው 2010 .. ሲሆን 2013 .. ለአራተኛ ጊዜ ተማሪዎችን ይቀበላል። ዩኒቨርሲቲው አራት ኮሌጆችና 14 ዲፓርትመንቶች አሉት። አራቱ ኮሌጆች የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ፣ ማኅበረሰብ ሳይንስ፣ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ እንዲሁም የግብርና ሳይንስ ናቸው። የተፈጥሮ ሳይንስና የግብርና ሳይንስ ኮሌጆች እያንዳንዳቸው አራት ዲፓርትመንቶች አሏቸው። የተቀሩት ሁለቱ ደግሞ እያንዳንዳቸው ሦስት ዲፓርትመንቶች አሏቸው፡፡ 2013 .. አሥር ዲፓርትመንቶችን ለመጨመር ዝግጅት በማድረግ ላይም ይገኛል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ ሲኒመር ትሬዲንግ...

የባህር በር በቀጣናዊ ተዛምዶ ውስጥ

በበቀለ ሹሜ መግቢያ በ2010 ዓ.ም. መጋቢት ማለቂያን ይዞ ዓብይ አህመድ በጠቅላይ...

ሥጋት ያስቀራል ተብሎ የሚታሰበው የጫኝና አውራጅ መመርያ

በአዲስ አበባ ከተማ በሕገወጥ መልኩ በመደራጀት ማኅበረሰቡ ላይ እንግልትና...

ማወቅ ወይስ አለማወቅ – ድፍረት ወይስ ፍርኃት?

በአሰፋ አደፍርስ ወገኖቼ ፈርተንም ደፍረንም የትም አንደርስምና ለአገራችን ሰላምና ክብር...