Friday, March 24, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

በፓርላማው አዳራሽ መግቢያ ኮሪደር ላይ ሚኒስትሩ ከሌላ ሚኒስትር ጋር እያወጉ ነው

  • እንዴት ይዞሃል ታዲያ? 
  • ትንሽ ችግር አለ እባክህ፡፡
  • ምን ተፈጠረ?
  • የቀድሞው ሚኒስትር ቢሮ እንዲያስረክቡኝ ብጠይቅም የማስረክበው ነገር የለምአልመጣም ብለው ተቸግሬያለሁባክህ፡፡
  • እኔም የአለቃ የሹመት ደብዳቤ ከደረሰኝ ጀምሮ ጥሩ አይደለሁም፡፡
  • ምነው?
  • እንዲሁ ፍርኃት ፍርኃት ይለኛል። 
  • የማላውቀው ነገር አለ እንዴ?
  • የአለቃ የሹመት ደብዳቤ ቢደርሰኝም ፓርላማው አላፀድቅም እንዳይል ሠግቼ ነው!

[የፓርላማው ፕሮቶኮል ሚኒስትሮቹን ወደ አዳራሹ ይዞ በመግባት ላይ ሳለ የሁሉም ዕጩ ሚኒስትሮች ሹመት በድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ መፅደቁን አፈ ጉባዔው ገልጸው ሚኒስትሮቹ ቃለ መሃላ ፈጽመው ከአዳራሹ ወጡ]

  • ፍርኃትህ ጠፋ፡፡ ተገላገልክ አይደል? 
  • አሁን ወደ ቀድሞ ስሜቴ ተመልሻለሁ፡፡
  • እኔ ግን ግር ብሎኛል?
  • ለምን? 
  • የፓርላማ አባላቱ ለምንድነው ድምፀ ተዓቅቦ ያደረጉብን? 
  • ዋናው በአብላጫ መፅደቁ ነው። ከዚህ ወዲህ ክቡር ሚኒስትር ልትለኝ ትችላለህ። እኔም ክቡር ሚኒስትር ብዬ እጠራሃለሁ፡፡ 
  • አንተማ ክቡር ሚኒስትር ብቻ ብለህ አይደለም እኔን መጥራት ያለብህ፡፡ 
  • እና ምን ልጨምርበት?
  • ባለውለታዬ፡፡ 
  • ለምን? 
  • ተዓቅቦህን ስለተጋራሁልህ!

[ክቡር ሚኒስትሩ የፖለቲካ አማካሪያቸው ደወሉ]

  • ሃሎ. . . .ነገሮች እንዴት እየሄዱ ነው?
  • ያለፈው ሳምንት ተልዕኮዎች በሰጡኝ አቅጣጫ መሠረትጥሩ ሁኔታ ተፈጽመዋል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • መልካም። በመጪዎቹ ቀናት ትኩረት የምታደርግባቸውን ተግባራት እንነጋገር፡፡ 
  • ይቀጥሉ ክቡር ሚኒስትር እንዳሉት ይፈጸማል፡፡
  • አንተ በምትመራው ኮሚቴ ከእኛ ሚዲያዎች አመራሮች ጋር የግማሽ ቀን ውይይት ታደርጉና የቀጣይ ሳምንታት አጀንዳዎችን ትነጋገራላችሁ፡፡
  • ጥሩ እየሰማሁ ነው፡፡
  • የእኛ ሚዲያዎች በቀጣይ ሳምንታት አጀንዳቸው አገር አቀፉ ምርጫ ዘንድሮ እንዲካሄድ መወሰኑ ተገቢነት ላይ እንዲሆን አድርጉ፡፡
  • ጥሩ፡፡ 
  • ይህንን አጀንዳ በደንብ አድርገው ማስረፅ እንዳለባቸው ጠንከር ያለ ትዕዛዝ ይሰጥ፡፡ 
  • እንዳሉት ይደረጋል ክቡር ሚኒስትር፡፡ 
  • ለዚህ ይረዳቸው ዘንድ በዋናነት አጋር ፓርቲዎችን ይጠቀሙ . . .
  • አጋር ነው ያሉኝ ክቡር ሚኒስትር? 
  • አዎ፡፡
  • አጋሮች የእኛው አካል ሆነዋል ብዬ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • አዎ! አጋር አልኩ እንዴ? 
  • . . . 
  • ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለማለት ፈልጌ ነው። 
  • ጠርጥሬያለሁ ቢሆንም አልተሳሳቱም፡፡
  • አልተሳሳቱም? 
  • አዎ! ተቃዋሚ ቢሆኑም በአጋርነታቸው ልክ ስለሆነ ወንበር እንዲያገኙ የምንፈቅድላቸው አጋር ብለው መጥራቶ ስህተት አይደለም። አጋር ተፎካካሪ ናቸው። 
  • ይህንን ለራስህም ቢሆን ደግመህ እንዳትለው! [ተቆጡ]
  • አጠፋሁ እንዴ?
  • አጠፋሁ ይለኛል እንዴ? ፈንጂ ከመርገጥ በላይ ምን ስህተት አለ?  
  • ስህተቴ ባይገባኝም ይቅርታ ያድርጉልኝ ክቡር ሚኒስትር? 
  • አድምጠኝ። ኢሕአዴግ አንድ ለአምስት ብሎ የተገበረው ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ውጤታማ ያልሆነው ለምን እንደሆነ ታውቃለህ? 
  • አላውቅም፡፡
  • አንድ ለአምስት የሚለውን እንቅስቃሴ እንደ ቅዱስ ተግባር ቆጥሮ በይፋ ስላስተዋወቀው ነው። ስህተቱ መነገሩ ነው።
  • ገባኝ ክቡር ሚኒስትር ፡፡
  • መስሎህ ነውአልገባህም። 
  • እሺ፡፡ 
  • አድምጠኝ ስለአጋር ተፎካካሪዎች ያልከው ነገር ይተገበራል እንጂ በፍፁም አይነገርም። 
  • ተፀፅቻለሁ ክቡር ሚኒስትር አሁን በደንብ ግልጽ ሆኖልኛል። ይተገበራል እንጂ አይነገርም፡፡ 
  • ትክክል። ሌላው ነገር ሚዲያዎቹ ከአጋር ፓርቲዎች በተጨማሪ. . .
  • እርስዎ ተናገሩት፡፡
  • ምን አልኩ? 
  • አጋር? 
  • አንተ አሳሳትከኝ። ለማንኛውም ሚዲያዎቹ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ውጪ የእኛን ሐሳብ የተቀበሉ ምሁራንንም እንዲጠቀሙ አድርጉ። 
  • ጥሩ፡፡ 
  • ምርጫው ዘንድሮ እንዲካሄድ መወሰኑ ተገቢ እንደሆነእንዲሁም ከሕግና ከዴሞክራሲ ሥርፀት አንፃርም ትክክል ስለመሆኑ ምሁራዊ አስተያየት እንዲሰጡበት ይደረግ፡፡ 
  • እሺ፡፡
  • ጎን ለጎን ደግሞ ለዚሁ ነው እንዴ የሚል ትችት እንዲሰነዝሩ ይደረግ፡፡ 
  • ለዚሁ ነው የሚለው ትችት ግልጽ አልሆነልኝም? 
  • ሕገ መንግሥቱን በመጣስ ምርጫ ያደረገው አካል ጥድፊያ ለዚሁ ነው ተብሎ በምሁራን ይተች፡፡ ለወራት ተብሎ ሕገ መንግሥት አይጣስም ይበሉ ምሁራን፡፡
  • እንዳሉት ይደረጋል ክቡር ሚኒስትር!

[የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ሁኔታ በመከታተል የሚታወቁ የአንድ አውሮፓ አገር የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ኃላፊ ለሚኒስትሩ ደወሉላቸው] 

  • ቢዘገይም እንኳን አደረሰዎት ክቡር ሚኒስትር፡፡ 
  • አመሠግናለሁ ወዳጄ፡፡ 
  • ድንቅ ታሪክና ከዓለም ልዩ የሆነ ባህል ያላት አገር መሪ መሆን መታደል ነው መቼም፡፡
  • እንዴታ! እውነት ብለዋል። 
  • ታዲያ በአዲሱ ዓመት ከእርስዎ ምን እንጠብቅ? 
  • ታሪካዊ ምርጫ ይጠብቁ። እርስዎና መንግሥትዎ ብቻ ሳትሆኑ ኢትዮጵያ በታሪኳ ዓይታው የማታውቀው ምርጫ ነው የሚሆነው። 
  • ግን እኮ አንዳንድ ደስ የማይሉ ነገሮች በኢትዮጵያ እየተከሰቱ መሆኑን እየሰማን ነው? 
  • ከሥልጣን የተወገዱት ኃይሎች ወሬ ነው፡፡ 
  • አዲስ አበባ ካለው ኤምባሲያችን ያገኘነው መረጃ ነው። መረጃው ትንሽ አሳስቦናል ክቡር ሚኒስትር። 
  • ይመኑኝ ያለፈውን በጭራሽ አንደግመውም። ሥጋት አይግባዎት፡፡  
  • ክቡር ሚኒስትር እየደገማችሁት መሆኑ ነው ሥጋት ያጫረብን?
  • የተሳሳተ መረጃ እንዳይሆን? 
  • ፖለቲከኞችን ስለማሰራችሁ የሰማነው ሐሰት ነው?
  • አይደለም፣ የተወሰኑትን አስረናል፡፡
  • ዋነኛ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን የመከፋፈል እንቅስቃሴዎች ስለመኖራቸውም መረጃ ደርሶናል፡፡
  • ተደርጎ ሊሆን ይችላል፡፡
  • ታዲያ ያለፈውን አንደግመውም ሲሉ ምን ማለትዎ ነው ክቡር ሚኒስትር? 
  • ድርጊቱ ቢመሳሰልም የእኛ ዓላማና ግብ ይለያል። 
  • ዓላማው ምንድነው? 
  • የተበታተኑ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሰብሰብ ማደረግ። 
  •  . . .
  • ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ውስጥ ግማሾቹ ወደ ብልፅግና ግማሾቹም ሰብሰብ ብለው ሁለት ወይም ቢበዛ ሦስት ሆነው እንዲወዳደሩ ለማድረግ ነው እጃችንን ያስገባነው።
  • እሺ የአመራሮቹ መታሰርስ?
  • ለጊዜው ነው።
  • ለጊዜው ማለት?
  • ተፎካካሪ ፓርቲዎቹን ሰብሰብ አድርገን እስክንጨርስ ገለል ማድረጋችን ነው፡፡
  • ታሪካዊ ምርጫ ይሆናል ሲሉ በዴሞክራሲያዊነቱ መስሎኝ ነበር፡፡ 
  • በግሌ ምርጫው ዴሞክራሲያዊና ነፃ እንደሚሆን አምናለሁ፡፡ 
  • ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው፡፡
  • ምን አሉኝ?
  • ልድገመው?
  • አይድከሙ ሰምቻለሁ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

አሜሪካ ሕወሓትን በማሳመንና በመጫን በሰላም ሒደቱ ትልቅ ሚና መጫወቷን የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ አስታወቁ

የተመድና የአውሮፓ ኅብረት አበርክቶ አሉታዊ እንደነበር ጠቁመዋል በመንግሥትና በሕወሓት መካከል...

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ በርካታ ሰዎች ወደ ከተማዋ እንዳይገቡ በፖሊስ መከልከላቸውን ገለጹ

‹‹የኦሮሚያ ክልል መፍትሔ እንዲሰጥበት አሳውቀናል›› የአማራ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ‹‹ጉዳዩ...

መንግሥት በግማሽ ዓመት 100 ቢሊዮን ብር ያህል ቀጥታ ብድር መውሰዱ ታወቀ

የአገር ውስጥ ብድር ከ1.6 ትሪሊዮን ብር በላይ ሆኗል የብሔራዊ ባንክ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አድርገው ሾሙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር) አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል...

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...

አወዛጋቢነቱ የቀጠለው የአዲስ አበባ የጤፍ ገበያ

ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤፍ የተከሰተውን የዋጋ ንረት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...