Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናአሜሪካ ለኢትዮጵያ 2.9 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ወታደራዊ ድጋፍ አደረገች

አሜሪካ ለኢትዮጵያ 2.9 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ወታደራዊ ድጋፍ አደረገች

ቀን:

አሜሪካ ለኢትዮጵያ የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ግምታቸው 2.9 ሚሊዮን ዶላር የሆነ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችና የሥልጠና ቁሳቁሶች አበረከተች፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካን ኤምባሲ ማክሰኞ መስከረም 19 ቀን 2013 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ዕርዳታውን ያበረከተው የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ነው፡፡ የዕርዳታው ዓላማም የአገር መከላከያ ሚኒስቴር፣ ሶማሊያ ውስጥ የሚገኘውን የአልሸባብንና የሌሎች አሸባሪ ኃይሎችን ጥቃት ለማክሸፍ የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍ መሆኑን ኤምባሲው በመግለጫው አመልክቷል፡፡ በዚህም መሠረት ላንድክሩዘሮች፣ የሠራዊት ማጓጓዣ ካሚዮኖች፣ አምቡላንሶች፣ የጭነትና የነዳጅ ተሽከርካሪዎች፣ የውኃ ታንከሮች፣ ለዘመቻ ማዕከል የሚያገለግሉ ኮምፒዩተሮችና የምሽት መመልከቻ መሣሪያዎች የአሜሪካ ፀረ ሽብርተኝነት አጋር ለሆነው የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ድጋፍ መደረጋቸው ተገልጿል፡፡ አሜሪካና ኢትዮጵያ ለረዥም ዓመታት ሰላም ለማስከበርና ሽብርተኝነትን ለመከላከል አጋር ከመሆናቸውም በላይ፣ የጋራ ወታደራዊ ሥልጠና እንደሚያካሂዱም በመግለጫው ተጠቁሟል፡፡ የአሜሪካ መንግሥት በቅርቡ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድቡን የመጀመሪያ ምዕራፍ የውኃ ሙሌት በማከናወኗ ምክንያት፣ ለተለያዩ ዘርፎች የሚውል ውስን ዕርዳታ ማቋረጡ ይታወሳል፡፡ በምሥሉ ላይ የሚታዩት የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ለአገር መከላከያ ሚኒስቴር ያበረከታቸው ተሽከርካሪዎች ናቸው፡፡ ፎቶ፡-  በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...