Friday, June 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ልናገርአሁንስ ዳኛው ማነው?

አሁንስ ዳኛው ማነው?

ቀን:

በዋካንዳ ኢትዮጵያ

“ዳኛው ማነው?” የተሰኘውን በአምባሳደር ታደለች ኃይለ ሚካኤል የተጻፈውን መጽሐፍ አንብቤ ስጨርስ እርሳቸው የጠየቁትን ጥያቄ ለመመለስ ሳወጣና ሳወርድ በመጽሐፋቸው ውስጥ ብዙ ዳኞችን አየሁ:: ጉልበት፣ ጠብመንጃ፣ ባለጊዜ፣አድር ባይነትርዕዮተ ዓለም በአንድ ወገን ሆነው ያሻቸውን ፍርድ ሲሰጡእንደ ኩራዝ ብርሃን ጭል ጭል የምትል በጎ ሊና ደግሞ ግራ ቀኙን በመመልከት ፁብ ድንቅ የሚያስብል ዳኝነትን ስትሰጥ ትታያለች፡፡ አምባሳደር ታደለችም ይህችን በጎ ሊና ሲያዩ “እንዴት ሊሆን ቻለ?” በማለት አግራሞትና ጥያቄ እንደ ፈጠረባቸው ተገንዝቤያለሁ፡፡ እኔ እንደገባኝ የእርሳቸው የ“ዳኛው ማነው?” ጥያቄ በመግቢያው ላይ የፍትሕ በመውጫው ላይ ደግሞ የታሪክ ዳኝነትን ነው::

ዳኛ ግራ ቀኙን መመልከት መበየን እንዲችል መል ላይ ያለሰው ወይም ተቋም ነው:: መል ላይ ያለ ሰው ወይም ተቋም ሚዛናዊ፣ መረጃዎችን መሰብሰብ፣ማጥለል፣ ማገናዘብና መተንተን የሚችል፣ በመረጃና በማስረጃ ላይ ተንተርሶ ብይን የሚሰጥ ነው፡፡ ነገር ግን በአገራችን የፖለቲካ ምዳር ውስጥ መል መሆን ተወዳጅ አይደለም፡፡ በደርግ ዘመን “መል ሰፋሪዎች ሚናችሁን ለዩ!” በማለት መል ላይ የቆመ ዳኛ እንዳይኖር ተደርጓል፡፡ ይህ በጊዜው የነበሩ ለቲካ ድርጅቶች የጋራ ባህሪ እንጂ የደርግ ብቸኛ ጠባይ አልነበረም፡፡ ስለዚህ መል ላይ የነበሩ ልክ “ከወንድሞቿ በላይ ከፍ እንዳለች ማሽላ ወይ ለወፍ አለበለዚያ ለወንጭፍ” እንደሚባለው ለአንዱ ሲሳይ ሆነዋል፡፡ በኢአዴግ ዘመንም ቢሆን መል የሚባል የለም:: አንድ ሰው በቅንነት ለአገርና ለወገን ይጠቅማል ብሎ የሚናገረውን ሳብ የነ እገሌ ሳብ ነው በማለት ይፈረጃል:: ምንም ውቀት ቢኖረው እንዲህ ዓይነት ሰው ለከፍተኛ ኃላፊነት አይፈለግም፡፡

 የአንድ ጎልማሳ ሰውን ድሜ ያ በአገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ ጭል ጭል ከምትለዋ በጎ ሊና በስተቀር ተቋሟዊ የሆነ እውነተኛ ዳኛ አለ ለማለት ያስቸግራል:: ይህ ልምምድ ምሳ ዓመታት እንደ ሸረሪት ድር አምሯችንን ተብትቦ ስለያዘውዳኝነትን የምናየው ከራሳችን አቋም አንር ብቻ ነው:: ስለዚህ በዳይና ተበዳይን በትክክል ለመለየት አልተቻለም:፡፡ ባለጊዜ የወደቀውን ጥፋተኛ ያደርጋል፡፡ እርሱ ሲወድቅ ደግሞ በሌላ ባለጊዜ ጥፋተኛ ይባላል፡፡ ያ በመጀመሪያ ጥፋተኛ የተባለው ደግሞ ከወደቀበት አንሰራርቶ እኔ ጥፋተኛ አልነበርኩም ይላል:: እንዲህ እንዲህ እያለ እስከ ዛሬ ደርሰናል:: በታሪክም ሆነ በትርክት መግባባትና መስማማት አዳጋች ሆኗል:: መወገን እንጂ መል ላይ ቆሞ እንደ ባለ አምሮ ማሰብ እንደ ክፉ ነገር ተወስዷል::

ከእውነተኛ ዳኝነት ይልቅ “ሕጋዊነትንና ሕገወጥነትን” ቀላቅሎ መሄድ እንደ ትክክለኛ የትግል አቅጣጫ ይታያል:: ከዚህም የተነሳ ዳኝነትን የሚያዛቡ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ ድርጊቶችን ለት ተለት ሕይወታችን ማየት እንግዳ አይደለም:: ከእኛ በተቃራኒ የቆሙት ላይ ሕጋዊ ርምጃ ሲወሰድ መንግሥትን ማወደስ በእኛ ላይ ሲሆን ግን መንግሥትን መኮነን፣ መሳደብ ወይም የሽምግልና ጋጋታ ማብዛት ልማድ ሆኗል:: ለራስ የለቲካ ግብ ጥቅም ይሁን እንጂ ሕገ መንግሥትን ማክበርም ሆነ መጣስ ምንም ልዩነት የላቸውም:: ሕዝብን ለማደናገር ሕገ መንግሥት ሲጣስም ሳይጣስም ተጣሰ ብሎ መጮህ ለጆሮ የሰለቸ “ሙዚቃ” ነው:: ሰዎች በግፍ ከቀዬአቸው ሲፈናቀሉ ዝም ያለ ድርጅትና “አክቲቪስት” አፈናቃዮች በቁጥጥር ር ሲውሉ ሰብዊ መብት ተጣሰ ይላል::

ምርጫ በራሱ ለችግሮቻችን ሁሉ መፍትሔ የሚያመጣ ይመስል ምርጫ ካልተደረገ ኢትዮጵያ ትጠፋለች ብሎ ሕዝብ ሲሸበር፣ በታጣቂዎች ንፁኃን ሲገደሉ፣ በምናምንቴዎች የሰው ሕይወትና ንብረት ሲጠፋ፣ በፕሮፓጋንዳ ስም ውዥንብር በመንዛት የሕዝብ ሥነ ልቦና ሲሰለብ፣ የሕዝብ አመኔታን ገደል ከቶ በጮሌነትና በሕገወጥ መንገድ አገርንና ሕዝብን የሚጎዳ ተግባር ሲፈጸም፣ በዚህች አጭር ጽሑፍ ዘርዝሬ የማልጨርሰው የመከራ መዓት በአገርና ወገን ላይ ሲደርስ“አሁንስ ዳኛው ማነው?” ያስብላል:: ል ላይ የቆሙ ሰዎችና ተቋሟት በሌሉባት ኖረውም በማይደመጡባትና በማይከበሩባት አገር “ባለጊዜ” እንጂ “ዳኛ” ሊኖር አይችልም::

ከሁለት ዓመት በፊት የተጀመረው ለውጥ ሲመጣ “ተደምረሃል?” የሚለው ጥያቄ በተራው ሰው ዘንድ በስፋት ይጠየቅ የነበረውል ላይ መሆን ትክክል አይደለም ከሚለው አጉል አባዜ የመነጨ ነው:: ለለውጡ ድጋፉን ለመግለጽ አዲስ አበባን ያጥለቀለቀው የሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. ልፍ ተሳታፊ በአገር ውስጥ ከሚኖሩትም ሆነ ከውጭ ከመጡ ግለሰቦችና ድርጅቶች “ኪስ” ውስጥ ለመግባት ብዙም ጊዜ አልወሰደበትም:: ምክንያቱም የለመድነው ጎራ ለይቶ መጎሻሸም እንጂ ወደ ግራም ሆነ ወደ ቀኝ ፈጥኖ ከመግባትል ላይ ቆሞና መዝኖ የሚበጀውን መምረጥ አይደለም::

እንግዲህ የፍትሕና የታሪክ እውነተኛ ዳኛ የምንፈልግ ከሆነ መል ላይ የቆሙ ግለሰቦችና ተቋሟት ያስፈልጉናል:: ጠቅላይ ሚስትር ብይ አመድ (ዶ/ር) ከሲቪክ ማኅበራት ተወካዮች ጋር በነበራቸው የውይይት ጊዜ “ሲቪክ ሶሳይቲ ሚዛን የሚያስጠብቅ” ነው በማለት መል ላይ ያለ ተቋምን አስፈላጊነት ተናግረዋል:: ይህ መ ላይ ላሉና ለመሆን ለሚፈልጉ ትልቅ ተስፋ ነው:: ምክንያቱም ከረጅም ዓመታት በኋላ መ ላይ መቆም ጥሩ መሆኑን ከገው ፓርቲና መንግሥት በይፋ ስለሰማን ነው:: ይህ መልካም ጅምር ከግብ እንዲደርስ የለቲካ ፓርቲዎችና መንግሥት መል ላይ ያሉ ተቋማትን ለራስ ፍላጎት መጠቀሚያ ከማድረግ መቆጠብ ይኖርባቸዋል:: ተቋማቱም የመንግሥትና የለቲካ ፓርቲዎች መጠቀሚያ ከመሆን ራስን ማዳት ይጠበቅባቸዋል:: በትክክል መል ላይ የቆሙ ተቋሟትን ማዳመጥና ማክበር ተገቢ ነው:: ይህ ሲሆን በአገራችን ኢትዮጵያ ዳኛ ይኖራል፣ ዴሞክራሲም ያብባል፣ በጎ ሊና ያላቸው “ትልቅ ሰው” የምንላቸውም ይበዛሉ::

ከዚህ በተጨማሪ ብዙ የተባለለት የፍትሕና ርት አካል መሆን እጅግ አስፈላጊ ነው:: በዚህ አካል ላይ የፓርቲዎችም ሆነ የመንግሥት ጣልቃ ገብነት ለቡድን እንጂ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ላም፣ መልካም አስተዳደር፣ድገትና ዴሞክራሲ ጥቅም የለውም:: በጎ ሊና ያላቸው፣ ል ላይ የቆሙ፣ ለእውነት ተገ የሆኑ፣ ለገንዘብ የማይጓጉ፣ እግዚአብሔርን የሚፈሩ፣ ሰውን የሚያከብሩ፣ በሙያቸውና በናቸው የተከበሩ ሰዎችን በዚህ ተቋም ውስጥ ማብዛት እውነተኛ ዳኛ እንዲኖረን ያደርጋል::

ይማኖት ተቋማትም መ ላይ የቆሙ ነበሩ ማለት አይቻልም:: ባለጊዜና ጉልበተኛ ወደፈለገው ሲጎትታቸው፣ እንደፈለገው ሲያምሳቸው ብዙ ዓመታትን አስቆጥረዋል:: ዛሬም ቢሆን ሳይጎተቱ ለመጎተት ራሳቸውን ያዘጋጁ፣ ጭርስኑ ጎራ ለይተው ከለቲከኞች የማያንስ የመከፋፈል ሥራ የሚሠሩ የይማኖት መሪዎች ይስተዋላሉ:: በግላቸው የፈለጉትን መሆን ይችላሉ፡፡ ተቋሙን ግን መል ላይ እንዲቆም መተው ለይማኖቱም ለአገርም ይጠቅማል:: ምክንያቱም የይማኖት ተቋማት መል መሆን በጎ ሊናና ሚዛናዊነት ያላቸው ዜጎችን በማዘጋጀትና በማፍራት እውነተኛ ዳኞች እንዲኖሩን ያደርጋል:: በእኔ ይታከታዋቂ የይማኖት መሪዎች መካከልእስካሁን ድረስ በሙስሊሙም ሆነ በክርስቲያኑ ዘንድ የዳኝነትን ማዕረግ የተጎናፉ ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር እድሪስ ይመስሉኛል:: እርሳቸውን ያነሳሁት ታዋቂ ስለሆኑ ነው እንጂ ሰው የማያውቃቸው፣ ሚዛናዊ የሆኑ፣ የሚመሩትን ምዕመን በጎ ሊና እንዲኖረውና እንዲያመዛዝን የሚያስተምሩ መኖራቸውን አውቃለሁ:: እንደ እነዚህ ዓይነት ያሉ መሪዎችን በሁሉም የእምነት ተቋማት ፈጣሪ እንዲያበዛልን ምኞቴ ነው::

ሰው አምሮ ያለው ፍጡር ነው:: የተፈጠረውም ማመዛዘን እንዲችል ሆኖ ነው:: ስለዚህ የሰው ልጅ የሆነ ሁሉ መል ላይ በመቆም የሠራቸውንና የሄደበትን ጎዳና ለማየት ከሊናው ጋር የሚሟገትበት ጊዜ ሊኖረው ይገባል:: በራሱ ላይ ዳኛ ያልሆነ እንዴት ብሎ ሌላውን ሊዳኝ ይችላል? ሊናን የጣለ ሰው መሪ ከሌለው መርከብ ጋር ተመሳሳይ ነው ከአደጋ አያመልጥም:: ሲሳሳት የማይፀፀት ሰው ሊናውን ጥሏልና ከሰው ተራ ወጥቷል:: መ ላይ የቆሙ ሰዎች ብዙዎችን ከስህተት ይታደጋሉ:: በጎ ሊና ያላቸውና መል ላይ የቆሙ በርካታ ሰዎች ኖረው ቢሆን ኖሮ ብዙ ወገኖቻችን በሕይወት ይኖሩ ነበር:: ስለዚህ የታሪክ ተመራማሪዎች፣ ሐኪሞች፣ መምህራን፣አገልግሎት ሰጪዎች፣ በአጠቃላይ በሙያቸው የሚያገለግሉ ሁሉ መል ላይ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ል ላይ እንዲሆኑም ከመንግሥትና ፓርቲዎች ተፅዕኖ ሊላቀቁ ይገባል::

በመጨረሻም የተጀመረው ለውጥ ግንባር ቀደም መሪዎችና ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከላይ የዘረርኳቸው ተቋማት ፍሬ እንዲያፈሩ የድርሻቸውን ይወጣሉ የሚል እምነት አለኝ:: ነገር ግን እንደ ቀደምቶቹ ባለጊዜዎችና ጉልበተኞች መል ላይ የቆሙትን በማሸማቀቅየሰውም የተቋማትም ዳኞች ማፍራት እንዳንችል ቢያደርጉ የታሪክ አቅጣጫን የሚዘውር፣ መንግሥታትን የሚያስነሳና የሚጥል ፈጣሪ የምንጊዜም ዳኛ መሆኑን መርሳት የለባቸውም:: የእርሱ ዳኝነት በዚህም በወዲያኛው ዓለም ነውና በተቻለን መጠን በእርሱና በሰዎች ዘንድ በጎ ሊና እንዲኖረን መትጋት ለሁላችንም ይበጃል::

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...