Sunday, June 4, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ከአለቃቸው ተደውሎ በተሰነዘረባቸው ወቀሳ የተበሳጩት ክቡር ሚኒስትሩ ለእርሳቸው ተጠሪ ለሆነ አንድ ተቋም ኃላፊ ደውሉ

  • ሃሎ፡፡ 
  • ጤና ይስጥልኝ አለቃ እንደምን አሉ?
  • አንተ እያለህ ምን ጤና አለ?
  • ምን አጠፋሁ ክቡር ሚኒስትር?
  • እንደለመድከው አስጠበስከኝለመሆኑ ምንይነት መግለጫ ነው ያወጣኸው ሰሞኑን? 
  • ሰሞኑን ያወጣነው መግለጫ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንትን ለማዘመን ያሰብነውን አዲስ አሠራር የሚመለከት ነው። 
  • አዲስ አሠራር ምናምን የምተለውን ትተህ ምን እንደሆነ ንገረኝ፡፡
  • የግል ተሽከርካሪዎች በሥራ መግቢያና መውጫ ሰዓቶች ትራንስፖርት አጥተው ለተቸገሩ ነዋሪዎች ጣምራ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድድ አሠራር ነው። 
  • ጣምራ ማለት?
  • ኮድ ሁለት እና ሦስት ቁጥር የሆኑ ተሽከርካሪዎች በሥራ መውጫና መግቢያ ሰዓት መንገደኞችን አሳፍረው እንዲሄዱ የሚያስገድድ በመሆኑ ነው ጣምራ ያልነው። እንደዚያ ካላደረጉ በሥራ መግቢያና መውጫ ሰዓት እንዳይንቀሳቀሱ ክልከላ ይጣልባቸዋል። 
  • ወይ ግሩምጤንነትህ ነው የሚያሳስበኝ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር በመላው ዓለም የተለመደ አሠራር እኮ ነው፡፡ በእርግጥ መግለጫውን ስናወጣ ትንሽ ስህተትርተናል፣ ለዚያ ነው ትንሽ ጫጫታ የተፈጠረው፡፡ 
  • ምን ዓይነት ስህተት ነው የሠራችሁት?
  • የመግለጫው መግቢያ ላይ በጠቅላዩሳብ አመንጭነት የሚል አላካተትንም…. እሱ ቢኖርሳቡ ይሰምር ነበር፡፡ 
  • ልክ ነውእኔን ገደል የመክተት ዕቅድህ ይሰምርልህ ነበር፡፡
  • ያደጉገሮች ጭምር ውጤታማ የሆኑበት ዘመናዊ አሠራር እኮ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡ 
  • የግል ንብረት ላስተዳድር ማለት ነው ዘመናዊ አሠራር?  ከዓላማችን እንደሚጣረስ እንኳ አይገባህም? 
  • እንደዚያ እንኳን አይደለምበፓርቲ ደረጃ ከያዝነው አቋም የሚጣረስ አልመሰለኝም ክቡር ሚኒስትር፡፡ 
  • ደግሞ ምንድነው በፓርቲ ደረጃ የያዝነው አቋም? 
  • በብልፅግና ዘመን የእኔ የአንተ የሚባል ነገር የለም አላልንም እንዴ ክቡር ሚኒስትር?
  • አሃ…. እንደዚያም ብለናል ለካ? ጥሩ ፖለቲከኛ እየወጣህ ነውባክህ? 
  • ተጠሪነቴ ለእርስዎ ሆኖ ደካማ ፖለቲከኛ ከሆንኩማ ጥሩ አይመጣም። 
  • ጥሩ ይዘሃል። እንዲያውም ይህንንሳብ ትንሽ ለወጥ አድርገህ አስተዳደሩ የመኖሪያ ቤት ችግርን እንዲፈታበት ብታቀርበው ጥሩ ነበር፡፡
  • እንዴት? ለቤት እጥረት ይሆናል ብዬ እንኳን አላሰብኩበትም ነበር፡፡
  • ትንሽ ለውጥ አድርገህ ግዴታ እንዲጣልባቸው ማድረግ እኮ ነው፡፡
  • ማን ላይ? 
  • ከአንድ መኝታ ክፍል በላይ ቤት ያላቸው ላይ?
  • ምን ዓይነት ግዴታ? 
  • ጣምራ አይደል ያልከው? የጣምራ ኑሮ ግዴታ መጣል ነዋ፡፡
  • ያስኬዳል ብለው ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የጣምራ ኑሮ የሚለው ተቃውሞ ከተነሳበት ለወጥ አድርገህ ታቀለዋለህ፡፡
  • ምን ብዬ?
  • ዕለታዊ ጣምራ…. ወይም እንደዚያ ነገር፡፡
  • እርስዎ እኮ መለኛ ነዎት፡፡
  • መላው እንኳን ነገ በደብዳቤ የሚደርስህ ይሆናል፡፡
  • ደብዳቤየምን መላ?
  • በጣምራ ከምንጠፋራስህን ችለህ ጥፋ የሚል መላ! 

[ክቡር ሚኒስትሩ በጠዋት ቢሯቸው ገብተው ማኅበራዊ ገጻቸውን ሲከፍቱ ታችኞቹ ያወጡት መግለጫ መነጋገሪያ ሆኖ ተመለከቱ። ስልካቸውን አንስተው አማካሪያቸው ወደ ቢሮ እንዲመጣ አዘዙ]

  • መግለጫቸውን አየኸው?
  • አይቼዋለሁምሽት ሆኖብኝ ነው ያልደወልኩልዎት፡፡
  • ይኼ ሁሉ ሚኒስትርኤታ እንደነበራቸው አላውቅም ነበር፡፡
  • ሃ.ሃ.ሃ.ሃእኔም አላውቅም ነበርምን አሰደነገጠዎት ግን? 
  • ምን አስደነገጠዎት?
  • ተቆጣጥረውን የለ እንዴ?
  • ተቆጣጥረውናል ሳይሆን ረድተውናል ቢሉ ይሻላል፡፡
  • እንዴት? 
  • አልሰሙም እንዴ ክቡር ሚኒስትር አብዛኞቹ እኮ ጥሪውን አልተቀበሉትም?
  • ምን? 
  • በርካቶቹ ለአገራቸውና ለሕዝብ ያላቸውን ወገንተኝነት አሳይተዋል። 
  • ምን ማለትህ ነው?
  • የታገልነው ሕዝብናገር ለማገልገል እንጂ ፓርቲ ለማገልገል አይደለም ብለው ጥሪውን ውድቅ አድርገውታል፡፡ 
  • እና ይቀጥላሉ ማለት ነው? 
  • አዎ! ለዚያ እኮ ነው አድነውናል ያልኩት፡፡
  • ተው አትቸኩል፡፡
  • እኔ ሳልሆን እነሱ ናቸው የቸኮሉት፡፡ 
  • እነ ማን?
  • መግለጫ ለማውጣት ተጣድፈው በራሳቸው እሳት ላይ የለኮሱት፡፡
  • ምን ተፈጠረ?
  • ከኃላፊነት ልቀቁ የተባሉት አመራሮች ጥሪውን ውድቅ በማድረጋቸው በፓርቲው ውስጥ መከፋፈል ተፈጥሯል፡፡
  • ተው አትቸኩል፡፡ 
  • የቸኮሉት እነሱ ናቸው፡፡ 
  • እንዴት?
  • ፌዴሬሽን ምክር ቤት የፌዴራልንም ሆነ የክልል መንግሥታትን ሥልጣን አራዝሞ ሳለ እነሱ ግን ቸኩለው አንድ ቦታ ላይ አነጣጠሩ። 
  • የት ላይ?
  • አራት ኪሎ ላይ፡፡ 
  • ባይቸኩሉስ ኖሮ?
  • ባይቸኩሉ ኖሮማ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔን ተቃውመው መንግሥት የለም ማለት ሌላውንም እንደሚመለከት ይገባቸው ነበር።
  • ሌላ የሚመለከተው ማን አለ?
  • ሁሉም የክልል መንግሥታት፡፡
  • እንዴት? 
  • የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሰጠውን የሕገ መንግሥት ትርጉም ተቃውሞ ከመስከረም 25 በኋላ መንግሥት የለም ማለት የክልል መንግሥታትም የሉም ማለት ነው።
  • የክልል መንግሥታትን የሉም ማለት ደግሞ እነሱንም ይጨምራል?
  • እነሱንም ይጨምራል ብቻ ሳይሆን ዓላማቸውገር ማፍረስ ሆኖ ይቆጠራል፣ ይህ ደግሞ ይነጥላቸዋል።
  • ከምን ይነጥላቸዋል?
  • ከሕዝብ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

ኢትዮጵያ በ2023 የሚኖራት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለ18 ቀናት ግዢ መፈጸሚያ ብቻ እንደሚሆን አይኤምኤፍ ተነበየ

ኢትዮጵያ በ2023 የሚኖራት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለ0.6 ወር ወይም...

ጦርነቱና ሒደቱ

ሦስት ሳምንታት ያስቆጠረው ሦስተኛው ዙር የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት አሁንም...

የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ ያለው ሦስተኛው ከግል ባንክ ሆነ

የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን ከ100 ቢሊዮን...

ወ/ሮ መሰንበት ሸንቁጤ የአዲስ አበባን ንግድና ዘርፍ ምክር ቤትን በፕሬዚደንትነት ለመምራት በተደረገው ምርጫ አሸነፉ

የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤትን በፕሬዚደንትነት ለመምራት፣...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...

ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመው ራሚስ ባንክ ዛሬ ሥራ ይጀምራል

በኢትዮጵያ ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመው...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...