Thursday, June 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ዳኛውማ “ደርግ” ነው

ነሲቡ ስብሐት (ሰሜን አሜሪካ ቨርኒያ)

ክፍል አንድ

  • የመጽሐፉ ርዕስ “ዳኛው ማነው?” የብርሃነ መስቀል እና የታደለች ሕይወት

      በኢሕአፓ የትግል ታሪክ

     ደራሲ ታደለች ኃይለ ሚካኤል

     የኅትመት ዘመን፡ 2012 ዓ.ም.

     ገጽ ብዛት 442

  • የብርሃነ መስቀል የእሥር ቤት ቃል ምርመራ

ሰኔ 1971 ዓ.ም.

ታሪክ ያለው ይጻፍለታል፡፡ በኢትዮጵያ ዝብ የትግል ታሪክ ኢሕአፓ ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡ ስለኢትዮጵያ የተማሪዎች እንቅስቃሴ፣ ስለየካቲት 1966 አብዮት፣ ስለመሬት ለአራሹ፣ ስለዲሞክራሲያ መብት፣ የብሔር ጥያቄ፣ የሕዝብ መንግሥት ሲነሳ፣ ሲጻፍ፣ ሲነገር ኢሕአፓ ባለ ሁለት ነጥብ ው፡፡ ኢሕአፓ አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ጎኑ በተለያየ መልኩ ተጽፏል፣ ተነግሯል፡፡ ኢሕአፓ ሲባል ወጣቶች ውቅያኖሱ ናቸው፣ እናት አባቶች በልጆቻቸው ታሪክ ተቋድሰዋል፣ ታዳጊ ሕናት ወላፈኑ አግኝቷቸዋል፡፡ ስለኢሕአፓ ሲነገር ሕዝብ፣ ዓላማ፣ ናት፣ ትግል፣ ሥነ ፍ፣ ኪነት የመሳሰሉት ስለሚነገሩ ተወርቶ አያልቅም፡፡ አፈሳው፣ እሩ፣ ግርፊያው፣ ግድያው፣ ስደቱ፣ መቆዘሙ፣ ጀግንነቱ፣ መስዋዕትነቱ፣ ደፋርነ፣ አጅሃብ! እስኪያሰኝ ይደመጣል፣ ይነበባል፡፡ ፍርት፣ ቀላባጅ፣ አስመሳይ፣ ወሬኛ የራሳቸው ድርሻ ነበራቸው፡፡

ኢሕአፓ በኢትዮጵያ የትግል ታሪክ አምባገነንነትን የተፋለመ፣ ተፋልሞ የተደበደበ፣ ተደብድቦ የተሰናከለ፣ ተሰናክሎ ታሪክ የሠራ ቀዳማይ ፓርቲ ነው፡፡ የኢሕአፓ ታሪክ ለትግል መሠረት ነውና ሁሉም ጠቅሰዋል፡፡ ስለኢሕአፓም ሆነ ስለያ ትውልድ ዘመን ጸሐፊዎች፣ ተራኪዎች፣ ቲያትር ሠሪዎች ሁሉም በትክክል ዘገቡ ወይስ አዛቡ ብሎ መቃኘት በተለይ የዘመኑ አባላት ኃላፊነትና ግዴታ ነው፡፡ ዝም ከተባለ ቀጣይ ትውልድ የሚከራከርበት፣ የሚጠቅሰው ሞጋች ሳብ ያጣልና፡፡ የእኛ ሕይወት ዘለዓለማዊ እንዲሆን ከፈለግን ትውልድ ይመራመርበት፣ ኖ! ይህማ ልክ አይደለም ይልበት፣ ትምህርት ይቀስምበት ዘንድ አሻራችንን ታሪኩ ላይ ማዋል ጠቀሜታው የጎላ ነው፡፡

መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ትንኝ ገድዬ አላውቅም ሲል በመቶ ሺ የሚቆጠረውን የትውልድ ፍጅት በሁለት መጽሐፍና በዘጋቢ ጸሐፊው አማካይነት ካደ፣ ፍቅረ ላሴ ወግደረስ ሽምጥጥ አድርጎ በትውልዱ ተሳለቀ፣ ካደ፣ ፍሥሐ ደስታ በይቅርታ ስም ትውልዱን አንቋሾ ካደ፣ ሌሎች ካዱ፣ ትረካቸው ለነፍሳቸው አደላ፡፡ መጽሐፈ ቀይ ሽብር ዘ መኢሶን ካደ፣ በምስክርና በሰነድ ወንጀለኝነታቸው የተረጋገጠባቸው እንደ ቀልቤሳ ነገዎ፣ ከፈለኝ ዓለሙ ዓይነቶች እንደካዱ ወደ እር ቤት ተወረወሩ፡፡ ‹‹የዘንድሮ ጅብ የሚያውቁት ገርም ዶ ቁርበት አንጥፉልኝ ይላልና›› የትንት ወንጀላቸውን ደብቀው ዛሬ ስለሞክራሲ መብትና ስለሕዝብ ብሶት መድረኩን ያጣበቡ የዕድሜ ባለጋ ባለ ነጭ ጉሮችና ጉር አልባዎች ምን ያህል ልባቸው ለጭካኔ ቢደነድን ነው ፀፀትን የዘነጉት ያሰኛል፡፡

“ዳኛው ማነው?” መጽሐፍን ከሥነ ጽፍ አንር ለመገምገም ሙያውም ችሎታውም የለኝ፡፡ የታሪኩ መጠነኛ ተቋዳሽ ብሆንም ሁሉንም አውቃለሁ ብዬ አልንቦራጨቅም፡፡ ማንበብ፣ ማድመጥ ማወቅ ነውና ነበርን ከሚሉት ያላነሰ ታሪክን የሚዘግቡ፣ ለትውልድ የሚያስተላልፉ መኖራቸውን ያህል በመጠኑም ካገላበጥኳቸው፣ ዕድሜ የሰጠኝን ግንዛቤ በመጠቀም የዛሬዋ አምባሳደር፣ የትንቷ ጓዲት ታደለች ኃይለ ሚካኤል መጽሐፍ ኢሕአፓን በሰፊው ስለሚነካ የተሰማኝን፣ የገባኝን፣ የኮረኮረኝን፣ ያስተከዘኝን፣ ያስቆጨኝን፣ ወይ ኢትዮጵያ! ወይ ገሬ! አይ ኢሕአፓ! እና ሌላም ያሰኘኝን ላስነብባችሁ ወደድሁ ፈለግሁ፡፡

“ዳኛው ማነው?” በቅርብ ቀን በገበያ እንደሚውል ማስታወቂያ ስመለከት ከርዕሱ የመጽሐፉን መልዕክት ጠረጠርሁ፡፡ ያም ሆነ አንድ መጽሐፍ ሳይነበብ፣ የአንድ ሰው ቃለ መጠይቅ ሳይደመጥ ትችት አይሰጥምና በጉጉት የተጠባበኩት መጽሐፍ እጄ ገብቶ ወረድኩበት፡፡ መጽሐፉን ገና ሳላነበው አምባሳደር ታደለች በትግል ያገኙትን የወጣትነት ፍቅረኛቸውን፣ በውጭ ገር፣ በገር ቤትና በእር ቤት ያወላለድ ታሪክ ያላቸውን የሦስት ልጆቻቸውን አባት ብር መስቀል ረዳን በኢሕአፓ በተሰጠው “የአንጃ መሪ” ተቀላ ሊከላከሉ እንደሚችሉ ገምቻለሁ፡፡ ግና በምን መልኩ? በአሳማኝ ነጥቦች በማስቀመጥ፣ ነገሮችን ግራ ቀኝ በመመልከት? ወይስ እንደ አንዳንድ ጸሐፊና ተናጋሪዎች በሆነው ባልሆነው ኢሕአፓን ጥላሸት በመቀባትና በማንቋሸሽ? በሌላ መልኩ ጥርጣሬም ቢኖራቸው የማያውቁት ላይ ድምዳሜ ከመስጠት ተቆጥበው የኢሕአፓውን መሥራች ብርሃነ መስቀል ረዳ ባህሪ፣ ችሎታና፣ አስተሳሰብ አስታከው በተሸፋፈነና ግልጽ ባልሆነ መልኩ የተደረሰበት የአንጃ ፍረጃን የሚያውቁትን አስቀምጠው “አንባቢ ሆይ! እናንት ፍረዱኝ” በሚል በሩን ከፍተው

‹‹ከስህተታችን እንድንማር ለጊዜያችን ዳኝነት ለመስጠት ሁሉም በየራሱ ቡድንና ድርጅት የተከሰተውን ችግር ነቅሶ በማውጣት ችግሮቹን እንዳሉ መቀበል፡፡ ተነቅሰው የወጡትን ችግሮች ልዩነታቸውንና ተመሳሳይነታቸውን በመገንዘብ ብሔራዊ ተግባቦት ለመፍጠር መትጋት ያስፈልጋል፡፡›› (ዳኛው ማነው? ገጽ 424) በሚል ያቺ ለሞት የታጨች የያ ትውልድ ወጣት እንደስሟ ታድላ ዛሬ ላይ ሆና አንቱ ልበልና አስነብበውናል፡፡

የመጽሐፉን የመጀመያ ምዕራፍ አንድ የመጀመያ ዓረፍተ ነገር አንብቤ ሦስት ገጽ እንደተጓዝሁ “ጥላሁን ግዛው የሞተ ጊዜ” በሚለው ርዕስ ሥር ያለውን የዓመተ ምረት መዛባት ገና ከጅምሩ ሳይ ስህተቱ ከእኔ አነባበብ ነው ብዬ መልሼ መላልሼ ባየው ያየሁት መዛባት ያው ነው፡፡ ማንበቤን አቋርጬ ዘጋሁትና ይህ እውነተኛ ታሪክ መጽሐፍ፣ ለአሁኑና ለነገው ትውልድ ተቀማጭ፣ በመረጃ ተደግፎ ተጽፎ ለነገ በመረጃነት የሚያገለግል ገና ከጅምሩ በዓመተ ምረት ሲጣላ ገባ ሲባልማ መሣሪያ እንዳይማዘዝ ጋሁ፡፡ ከደራሲዋ በበለጠ በምጋና የተወደሱት አንባቢያን ላይ አዘንሁ፡፡ 12 አንባቢያን 24 ዓይኖች እንዴት ዘለሉት አልኩ? አንብበዋል እንጂ አላስተዋሉም አልኩ፡፡

ወጣት ታደለች ዳር 5 ቀን 1962 ዓ.ም. በ19 ዓመት የልደት ቀኗ ዕለት ወደ ስዊዘርላንድ ለትምህርት ተጓዘች (ገጽ 3) ከ3 ገጽ ጉዞ በኋላ ታኅሣሥ 19 ቀን 1962 ዓ.ም. ጥላሁን ግዛው የተገደለ ዕለት “እኔም ከጥቂት ጓደኞቼ ጋር እዚያው ታድሜያለሁ” ትለናለች፡፡ ስዊዘርላንድ በሄደች በወር ከ14 ቀን ማለት ነው፡፡ ጥላሁን ግዛው ረፈበት ዕለትና ዓመት ትክክል በመሆኑ ለቀጣይ ትመት ወደ ስዊዘርላንድ የተጓዘችው ዳር 5 ቀን 1963 ዓ.ም. በሚል ቢስተካከል ሳልጠቁም አላልፍም፡፡ ቀላል ሎጂክ??? በጥቅሉ መጽሐፋቸውን በቃላት ለቀማ እጅግ የተዋጣለት ሥራ ተርቷል፡፡ ቋንቋቸውና አጻጻፋቸውም ጭንቅላቴን ገና በገና “የአንጃ ሚስት” ብዬ በጥላቻ ሳይሆን በምን መልኩ አቀረቡት? የሚለውንና ምን አገኝበታለሁ? በሚል ጉጉት ስለአነበብኩት ቋንቋቸውንና አገላለጻቸው ከዘመኑ ወጣቶች ቃላት ልዋስና ለእኔ ተመችቶኛል፡፡

በፖለቲካ ብስለትና ፍላጎት እምብዛም የሆነችው ታደለች በስዊዘርላንድ ይወቷ የኢሕአፓውን መሥራች ተስፋዬ ደበሳይን (ዶ/ር)፣ አክሊሉ ህሩይ በአጋጣሚ በገር ልጅነት ተዋውቃ እንዴት ወደ ፖለቲካው ልትሳብ እንደቻለች ደቱን ስትተርከው የ ተስፋዬን ትዕግት፣ የአክሊሉን ብልጠት አስታኮ ምን ያህል ሴቶችን በትግሉ ለማሳተፍ የነበራቸውን ጥረት ያሳያል፡፡ እውነትም ተሳክቶላቸዋል፡፡ ኢሕአፓ ሴቶችን ከቤት እመቤትነት ወደ ትግል እመቤትነት ያወጣ ጠንካራ ፓርቲ ነበርና፡፡ “ተዋት! በርግጠኝነት አንድ ቀን ትመጣለች” (ገጽ 21) ይል የነበረው ተስፋዬ ደበሳይ (ዶ/ር) “የማትመጪው ፈርተሽ ነው አይደል?” (ገጽ 17) በሚል በሞራሏ የሚጫወተው አክሊሉ ህሩይ በውይይት መድረካቸው “ፍቅር እስከ መቃብር”ን በማቅረብ አስጀምሮ ወደ ተማሪዎቹ ስብሰባ እየተጎተተች፣ እየተሳበች ሳታስበው ጥልቅ እንዳለች ስታስቀምጠው በወቅቱ የነበሩ ሴቶች ኢሕአፓውያን እንዴት ድርጅቱን እንደተቀላቀሉ መለስ ብለው የ46 ዓመት ካሴት ወደ ኋላ እንዲያጠነጥኑ ታደርጋለች፡፡ ለአዲስ አበባ ዩቨርቲ የበቁትና የውጭ ዕድል አግኝተው በትምህርት መስክ ያሉት በኢሕአፓም ሆነ በመኢሶን በኩል የተለፉት ወጣት ሴቶች በወቅቱ በኑሮ ደረጃም ሻል ያሉ ነበሩ፡፡

ታደለች በውጭ ትምህርቷ ተከራይታ የምትኖርበትን ቤት ተስፋዬ ደበሳይ ለአንድ ቀን እንድትፈቅድለት በጠየቃት መሠረት ታዋቂው ብርሃነ መስቀል በእንግድነት መጥቶ ከወጣት ታደለች ለመተዋወቅና የትዳር ጓደኛ የመሆንን ደት በጥሩ መልኩ ገልጻዋለች፡፡ በነሐሴ ወር 1961 ዓ.ም. ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር የአውሮፕላን ጠለፋ ላይ ተማርቶ ወደ አልሪያ ካቀናው ቡድን ውስጥ ብርሃነ መስቀል ረዳ ከዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ጋር ለመገናኘት ወደ ሲዊዘርላንድ በመጣ ወቅት የጋራ ውይይታቸው በታደለች የትምህርት መኖሪያ ቤት ተካሂዷል፡፡ ሁለቱ ዝነኛ ታጋዮች በያዙት የገር፣ የዝብ፣ የድርጅት፣ ሌላም ሌላ ጉዳይ ውይይት ሁኔታ ታደለች በዚህ መልኩ ትገልጸዋለች

‹‹. . . እኔ አዘገጃጅቼ እስክጨርስ ምንም አላቆሙም በለሆሳስ አፍ ለአፍ ገጥመው ያወራሉ፡፡ አንደኛው ሲያቆም ሌላኛው ይቀጥላል፡፡ . . .” (ገጽ 39) “. . . እቤት ደርሼ ቁልፉን ስከፍት እንደዚያው ጥያቸው እንደሄድኩት ወሬያቸውን ጠምደዋል፡፡ ምግቡን በልተው አላነሱትም፡፡ ወይኑንም ጥቂት ቀምሰውታል እንጂ አልጠጡትም፡፡›› በሚል ለታላቅ የገርና የዝብ ገድል ረዥሙን ጉዞ እንዴት እንደሚጀምሩት? ምን ማድረግ እንዳለባቸው የሚነጋገሩት ሁለቱ አንጋፋ የኢሕአፓ ምሰሶዎች አፍ ለአፍ የገጠሙት ማሳረጊያቸው ሆድና ጀርባ ሲሆን ያማል ያቆስላል፡፡ ለሰው ልጅ ዛሬ በፍቅር፣ በእምነት፣ በናት የተሳሰርንበት ዓላማ ነገ በአንዲት ጠብታ ሤራ እሳትና ጭድ ሊኮን እንደሚችል ይመጣብናል፡፡ ሰዎች ያመኑት ሰዋቸው ሳያቁት ነገ እሚሰምጥ ገደል ላይ (Sinkhole) አቁሟቸው ውስጡ ሲስቅ ይታያችኋል “ሰውን ውደደው እንጂ አትመነው” ቢያቃጭልባችሁም እንዴት ተደርጎ በኢሕአፓ ያለ እምነት? ያስብላችኋል፡፡ ሌላም ሌላ፡፡

ሰው የፈለገ ቢሆን ፍቅርን ይወዳል የተቃራኒ ታ ፍቅር ደግሞ እጅጉን ይወደዳል፡፡ ከምስኪኑ ደሃ እስከ ባለጋው፣ ከመይሙ እስከ ምሁሩ ብቻ የሰው ዘር በሙሉ የተቃራኒ ጾታ ፍላጎት ገደብ የለውም፡፡ ከዚህ አኳያ በትግል ከተለፉ ሴቶች መጽሐፉ ውስጥ በሰፊው ከወሱት ፍቅርተ ገብረ ማርያም፣ አበበች በቀለ፣ አዳነች ፍሥሐዬ  ጀምሮ  ማርታ መብርሃቱ፣ መዝገብነሽ አባዩ፣ ገነት ግርማ፣ ሰላማዊት ዳዊት መሰል ከፍተኛ የኢሕአፓ መሥራች ሴቶች በአብዛኞቹ የአመራር አካሉ ፍቅረኛ ወይም ባለቤቶች መሆናቸው ትግልና ፍቅር መጣመዳቸውን ያሳየናል፡፡

የዛሬዋ አምባሳደር ታደለች መጽሐፍን ካነበብሁ በኋላ በቀጥታ ጉዞ ወደ ብርሃነ መስቀል አደረግሁ፡፡ ከጥቂት ዓመታት በፊት ሁለት ጊዜ አንብቤውና ትዝብት ወርሼ፣ ሀዘኔን ቋጥሬ “ያ ትውልድ” ድረ ገጽ ላይ “ምን ብለው ነበር?” (http://yatewlid.com/images/PDF/MinBlewNeber/Berhanemeskel.pdf) በሚል ምድ ሥር ወደ ተቀመጠው 96 ገጽ የብርሃነ መስቀል ቃል ምርመራ ነድን “ዳኛው ማነው” ከሚለው መጽሐፍ ጋር እያዛመድሁ፣ እያገናዘብሁ ማንበብ ጀመርሁ፡፡ ጸሐፊዋ ይህንን ሰነድ አንድ ጊዜ (ገጽ 271) ብቻ ቢጠቅሱትም መጽሐፋቸውና የብርሃነ መስቀል የምርመራ ነድ አንድ ናቸው፡፡ በመሆኑም መጽሐፉን ከመገምገም ጋር ራሱ የተናገረውን፣ የሰጠውን ቃል ይበልጥ ማየት አስፈላጊ ነው፡፡ ከላይ እንደገለጽኩት አምባሳደር ውድ ባለቤታቸውን፣ የሦስት ልጆቻቸውን አባት እንዴት ብለው ተሳስቷል ይላሉ? እንዴት ብለው ደርግ ፋስት ነው ይላሉ? ብዬ በኢሕአፓ ያለችኝን አንድ ጠብታ ውሎና ዕድሜ ከሰጠኝ ግንዛቤ በመነሳት መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ልጽፍ ፈለግሁ

“ዳኛው ማነው?” የሚለውንም ሆነ ስለሌሎች መጻሕፍት ስለእያንዳንዱ የራስ ግምጋሜ መስጠት ቢቻልም እኔ ያተኮርኩት በብርሃነ መስቀልና የአንጃ ጉዳይ ጋር የተነሱት ነጥቦች ላይ ነው፡፡ ይህ ደግሞ መጽሐፉን አንብቦና አጣጥፎ መጽሐፍ መደርደሪያው ላይ በማስፈር መቋጨቱ በተለይ በኢሕአፓ ጉዳይ በተደጋጋሚ በመጽሐፍም ሆነ በቃለ ምልልስ የሚደናገረው የአሁኑ ትውልድም ሆነ መጪው ትውልድ ይህ ተጽፏል ብሎ ይወያይበት፣ ይከራከርበት ዘንድ ያለኝን ነጥብ ማካፈሉ ከዝምታ ይሻላል ብዬ ወርውሬአለሁ፡፡ 

ኢሕአፓ ፕሮግራሙን ለሕዝብ አራጭቶ ራሱን ይፋ በአደረገበት ነሐሴ 26 ቀን 1967 ዓ.ም. የደርግ አገዛዝ ዓመት ሊሞላው ከሁለት ሳምንት ያነሰ ቀናት ነበር የሚቀረው፡፡ በቀጣይ ዓመት 1968 ማለት ኢሕአፓ ሙሉ በሙሉ የጀመረውን መዋቅሩን በማጠናከርና በሕዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያገኝ ዘንድ ይዟቸው የተነሳውን ወቅታዊ መፈክሮች ማታገያ አደረጋቸው:: ደርግ የካቲት 25 ቀን 1967 ዓ.ም. የመሬት አዋጅን ቢያውጅም የሚያካሂደው መቃና አፈና ጎልቶ መውጣቱ የኢሕአፓ ማታገያ መፈክሮች የኃይል ሚዘኑ ወደ ዝብ እንዲያጋድል ሆኗል፡፡ “የሞክራሲ መብት ያለገደብ” መፈክር ተቀባይነት ማግኘት ከደርግ ይልቅ ኢሕአፓ ተደመጠ፣ “ጊዜያዊ ሕዝባዊ መንግት አሁንኑ” መፈክር ደርግ ወደ ጦር ሠፈሩ ይመለስ ዘንድ በወጣቱና በዝቡ ዘንድ እምቢታን አስከተለ፣ “የብር ብረሰቦች መብት እስከ መገንጠል” ኢሕአፓ ቢቀበልም ቅስቀሳውና ትግሉ የመደብ ትግል ላይ ማተኮሩ በብሔር የተደራጁ ኃይሎችን ተደማጭነት አሳጣ፡፡ ይህ የአንድ ዓመት በተለይ የ1968 ዓ.ም. እንቅስቃሴ ኢሕአፓን እንደስሙ ሕዝባዊ አድርጎታል፡፡ የሕዝብን ስሜት ይዞ ስለተነሳ ተደማጭነት፣ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ከዚህ ደት በኋላ ኢሕአፓ የወጣቱ፣ የሴቶች እህቶቻችን፣ የላብ አደሩ፣ የአርሶ አደሩ፣ የጭቁን ወታደሩ፣ የመምህራን፣ የተማሪዎች፣ የሠራተኛው፣ የእናቶች፣ የአባቶች በጥቅሉ የሕዝብ ሆኗል፡፡ ይህ ነበር የዚያ ጊዜ ዘር ቆጠራው፡፡ ክርስቲያኑን ከሙስሊሙ ለአንድ ዓላማ ያስተቃቀፈ ፓርቲ፡፡ በመዋቅርና በማደራጀት ደረጃ ኢሕአፓ ካስመዘገበው ከፍተኛ ድል በኋላ ኢሕአፓ የብርሃነ መስቀል፣ ኢሕአፓ የጌታቸው ማሩ በሌላ በኩል ኢሕአፓ እንደ መጽሐፉ አባባል “የክሊኩ” (የዶክተር ተስፋዬ ደበሳይ፣ የዘርዑ ክሸንና የክፍሉ ታደሰ) ሳይሆን የገርና የሕዝብ ነው፡፡ ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎች መሥራች አመራር አካላት ድርጅቱን በጋራ መሥርተው ሕዝባዊ እንዳሉት በአጭር ጊዜ ሲሳካላቸው ከዚያ በኋላ ንብረትነቱ የዝብ ነው፡፡ በተለያየ ጊዜ በውስጣቸው ሊከሰት በሚችል አለመግባባት በርካታ አባላቱና ደጋፊዎቻቸው የጥቃቱ ሰለባ ሊሆኑ ባልተገባ ነበር፡፡ እዚህ ላይ ነው የብርሃነ መስቀል ስህተት፡፡

ብርሃነ መስቀል እንደሚለውና ባለቤቱ ታደለች እንዳስነበበችን “በክሊኩ” አንጃ ተብሎ ተፈረጀ፣ ከፖሊት ቢሮ አባልነቱ ተነሳ፣ ከፓርቲው ተገለለ፣ በቀጣይነት ሊገደል ተፈለገ፣ ሸሸ፡፡ ጥሩ ለምን ግን “በክሊኩ” እልህ የኢሕአፓ ልጆች እንዲጠቁ፣ ምንም ሳናውቅ እየታገልን ያለነው በመቶ ሺዎች ሚቆጠሩ ቤተሰቦች ላይ ፈረደ? ውን ትልቅ ገራዊ አጀንዳ ይዞ ያን ያህል ለትግሉና ለኢሕአፓ ትልቅ ስም የያዘ ብርሃነ መስቀል መርቤቴ ገብቶ ከተራ ሽፍታ መንግሥቴ ደፋር ጋር ሲደራደር አያሳፍርም? ብርሃነ መስቀል “በክሊኩ” ንዴት የተነሳ ከሚያውቃቸው ተባባሪዎቹ ጋር (በመጽሐፉ እንደተነገረው ከእርማት ንቅናቄው ጋር) በመሆን የኢሕአፓ ድርጊት እንዳይሳካ ማሰናከልና ምስጢር አሳልፎ መስጠት ማንን እንደጎዳ ሲታሰብ አያሳዝንምን? ውን ብርሃነ መስቀል ያላግባብም ሆነ በአግባብ አንጃ ተብሎ እንደ ጌታቸው ማሩ በእጃቸው ላይ ስላልወደቀ ሁኔታዎች እንዳበቁለት ተገንዝቦ ከገር ለመውጣት ሙከራ ቢያደርግ በተገባ ነበር፡፡ በደርግ ከተያዘም በኋላ ሕይወቱን ለማዳን ሲል ለታሪክ ጥሎ ያለፈውን የምርመራ ቃል ከሚሰጥ በቆራጥ ዓላማው ተተልትሎ ቢሞት ስሙ እጅግ በተለወጠ፡፡

በዓይኑ ያየውን የሸሸበትን መርቤቴ ነዋሪ እህልና ጎጆ የሚያቃጥል፣ የሚያወድም ደርግ እንዴት እኔን ይምረኛል ብሎ ተስፋ አደረገ? ውን ከደርግ ጋር ተቀላቅሎ ገራፊና ገዳይ ካድሬ ከመሆን ሌላ ምን ያተርፍ ነበር? በየከፍተኛው፣ በየክፍለ ገሩ እየከዱ ለደርግ እጃቸውን የሰጡ አንዳንድ የኢሕአፓን ልጆች ለጥፋት በነ ርምጃ ከመሳተፍ ጀምሮ፣ ራሳቸውን ቀይረው ያሉ ኢሕአፓዎችን ከየተደበቁበት በማስያዝ፣ በመግረፍ፣ በማስገደል ድርጊታቸው ነው የሚታወቁት፡፡ በፖለቲካው ረገድ ትልቁን ተንኮልና ሤራ ያለጠኑትን መኢሶኖች የበላ መንግሥቱ፣ ከጎኑ የነበሩትን ኪሮስ ዓለማየሁን፣ ሻለቃ ሲሳይ ሀብቴን፣ ብርጋዴር ጄነራል ጌታቸው ናደውን፣ ሌተና ኔራል አማን አንዶምን፣ ብርጋዴር ኔራል ተፈሪ በንቲን፣ ሌተና ሎኔል አጥናፉ አባተንና በርካታ የደርግ አባላትን መግደሉን በተግባር ያየ የኢሕአፓው መሥራች ብርሃነ መስቀል ውን ከፋስት መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ጋር “ጓድ” ሊባባል ሲያስብ እንኳን ያኔ ዛሬ ያማል፡፡  

የችግሩ መነሻ

ብርሃነ መስቀል ከፖሊት ቢሮው ለመውጣት ዋናው ምክንያት የሆነው ፓርቲው ከመታወጁ ነሐሴ 26 ቀን 1967 ዓ.ም. በፊት በተደረገው ክስ ወይም ውንጀላ እንደሆነ በሰጠው የምርመራ ቃል ገጽ 7 እንዲህ ይላል

 ‹‹. . . የስብሰባው ዋና ተግባር ለመለስተኛ ጉባው መዘጋጀት ሲሆን ሌላው ሰፊ ጊዜ የፈጀው ውይይት ከታጠቀው ቡድን ጠፍተው ስለወጡት ሰባት ሰዎች ነበር፡፡ በዚህም ውይይት ዋናው ዓላማው ሰዎቹ የጠፉት በፖለቲካ መስመር ልዩነት ሳይሆን በኔ አስተዳደር ብልሹነት መሆኑን ለማሳመን ነበር። . . .›› ሰረዝ የተጨመረበት። በማስከተል

 “ . . . ስህተቴን በመጠቆም ፈንታ እኔ ባልተገኘሁባቸው ስብሰባዎች ስለእኔ ሥራ ብዙ ክሶች ይቀርቡ ስለነበር. . . ከጉባው በፊት እውነተኛ ጓዳዊ መንፈስ እንዲሰፍን ሒስና ግለ ሒስ ይደረግ ብል አጣዳፊ ተግባሮች አሉና ከጉባው በኋላ ሒስና ግለ ሒስ እናካሂዳለን ተብሎ ነገሩ በዚህ ተደፋፈነ። . . .››  

የብርሃነ መስቀል መነሻ ልዩነት ከታጠቀው ቡድን ጥለው የወጡት ሰባት ሰዎች ምክንያት መሆኑን ራሱ ይመሰክራል፡፡ ወደ አሲምባ የገባው የመጀመያው የኢሕአቡድን ኤርትራ በረሃ እያለ የካቲት 25 ቀን 1967 ዓ.ም. ከታወጀው የመሬት ለአራሹ አዋጅ በኋላ እዚህ ምን እናደርጋለን? የምንታገልለት ጥያቄ ተመልሷል ዓይነት ጥያቄዎች በቡድኑ ውስጥ ሲነሱ በአግባቡ እንዳልተስተናገዱ ተዘግቧል፡፡ በኤርትራ ቆይታቸው ብርሃነ መስቀል ቡድኑን ትቶ ወደ አውሮፓ መጓዝና በሌላም በኩል ከሻቢያ ጋር በምን ጉዳይ ተስማምቶ ወደ አሲምባ ሊገቡ እንደተፈቀደላቸው ለሚነሱ ጥያቄዎችና ለተነሱ ቅሬታዎች አግባብ መልስ አለመሰጠቱ በአንድ ምሽት ወደ ግማሽ የሚሆኑት ለደርግ እጃቸውን ለመስጠት መሠወር የብርሃነ መስቀልን የአመራር ብቃት ጥያቄ ውስጥ እንዳስገባውና ከሌሎች የፓርቲው አመራር አካላቱ ጋር የቅሬታና የልዩነት አዝማሚያ መነሻ ነው ቢባል ያስኬዳል፡፡ ከዚህ ደት በኋላ ብርሃነ መስቀል ከነሐሴ ወር 1967 ዓ.ም. ቀደም ሲል በተካሄደው የኢሕአፓ እወጃ ኮንፈረንስ ላይ ይሳተፍ እንጂ የጸሐፊነቱን ቦታ ሁሉ ክብር ሳይሰጠው ጉባውን ሊከፍት አለመቻሉ የሚያሳድርበትን የሞራል ድቀት መረዳት አያዳግትም፡፡ ይህንንም ሲገል

 ‹‹. . . መለስተኛ ጉባ ሲካሄድ ለሚቀርቡት ሪፖርቶች ስንነጋገር በየትኛውም ሌላ ማርክሲስት ሌኒንስት ፓርቲ ትራዲሽን የሌለ ፕሮሲጀር አቀረቡ፡፡ ይኸውም በሕጋዊ መንገድ ከኃላፊነቱ ያልተነሳ ዋና ጸሐፊ እያለ ሌላ ተራ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ጉባውን እንዲከፍት የሚል ነበር፣ ኔ በኩል ያኔ በእኔ ላይ ፐርሰናል ቅሬታ ስላላቸው እንጂ ከማዕከላዊ ኮሚቴ በስተጀርባ የተቋቋመው ክሊክ በመመረቻ ጉባ የተመረጡትን የፓርቲው መሪዎች ዘዴኛና ድብቅ በሆነ መንገድ ለማውረድ ማቀዳቸውን አልገመትኩም ነበር፡፡ . . .››  እያለ የሚነበበው የብርሃነ መስቀል የቃል ምርመራ ገጽ 12 መጨረሻና ገጽ 13 መጀመያ እንዲህ ይለናል

 ‹‹. . .  ከዚህ በኋላ ማዕከላዊ ኮሚቴው አዲስ ፖሊት ቢሮ ይምረጥ ተባለና ቀደም ብሎ ይተበተብ የነበረው በመመሥረቻው ጉባ ላይ የተመረጡትን መሪዎች የመለወጥ ሴራ ይፋ ወጥቶ ጋዊ መልክ ያዘ፡፡ በዚሁ ምርጫ መሠረት የሚከተሉት ሰዎች ለፖሊት ቢሮ አባልነት ተመረጡ፡፡ አንደኛ ተስፋዬ ደበሳይ (ዶ/ር) ሁለተኛ ክፍሉ ታደሰ (የኢሠማው)  ሦስተኛ ዘሩ ኪሸን አራተኛ ጌታቸው ማሩ አምስተኛ አበራ ዋቅጅራ ነበሩ፡፡ . . .›› በማለት ከገለጸ በኋላ አበራ ዋቅጅራ በተደረገው ምርጫ ባለመደሰቱ በመም ምክንያት እኔ እንድተካው ቢጠይቅም በፖሊት ቢሮው መግባት እንደሌለበትና ገና ኢሕአፓ ሳይታወጅ የነበረውን ልዩነት እንዲህ ያስቀምጠዋል።

 “. . . በእኔ በኩል ከተቀሩት አራት ሰዎች ጋር የፖለቲካ አስተሳሰብና የርዕዮተ ዓለም ልዩነት (በተለይም በኮሚስት ፓርቲ ምግባር ረገድ) ስለአለኝ የፖሊት ቢሮ ሥራ በየጊዜው በሚነሳ ክርክርና ጭቅጭቅ እንዳይደናቀፍ መግባት የለብኝም፣ . . .››  ሠረዝ የተጨመረበት፡፡

ይህ የብርሃነ መስቀል ቃል ምርመራ የሚነግረን ብርሃነ መስቀል ከአመራሩ አካል ወሳኝ ሰዎች ጋር ቅራኔ/አለመግባባት የገባው ከነሐሴ 26 ቀን 1967 ዓ.ም. በፊት መሆኑን ነው፡፡ ይህ አለመግባባትም ከላይ በሠረዝ እንደተቀመጠው የፖለቲካ ልዩነት ነበር ይለናል፡፡ በመሆኑም ብርሃነ መስቀል በ1968 ዓ.ም. የኢሕአፓ ጣፋጭ የትግል ዓመት በምን ሁኔታ አሳለፈ? የሚለው ለቀጣይ አለመግባባቶች መሠረት ነበሩ ቢባል ያስኬዳል፡፡ የደርግ የግንባር ጥሪ የመጣው ከሰባት ወር በኋላ ሚያዝያ 12 ቀን 1968 ዓ.ም. ሲሆን፣ የመንግሥቱ ኃይለ ማርያም ግድያ ጉዳይ በዓመቱ መስከረም 13 ቀን 1969 ዓ.ም. ሲሆን በዚህ ረገድ ብርሃነ መስቀል ካስመዘገበው ልዩነት በፊት ጉዞው ሁሉ የተነጠለ እንደነበር ያመላክታል፡፡

ብርሃነ መስቀል ከኢሕአሠ ለከዱት ለሰባ አባላት ተጠያቂ አድርጎ ጉዳዩን እጅግ ሞራል በሚነካ መንገድ ከማክረር ለምን በስና ግለሒስ መፍታት አልተቻለም? የብርሃነ መስቀል ኢሕአፓን በመመሥረት አኳያ ያስመዘገበው ጥረት ቀላል አይደለምና ለድርጅቱ አንድነት ሲባል እልህ ከመጋባት በምክርና በግሳ ቢታለፍ ምናለበት? የሚሉ ምኞቶች ይመጣሉ፡፡ እዚህ ጅምር ንትርክ ላይ ነው በአጠቃላይ የአመራሩ ድክመት፡፡ ከዚህ ደት በኋላ ብርሃነ መስቀል የሚናገረውም የማይጥማቸው፣ ተደማጭነቱም እየቀነሰ መምጣቱ ሰብዊ ባህሪውን እየተፈታተነ ቢመጣ ሊደንቀን አይገባም፡፡

ማታገያ መፈክሮች

ብርሃነ መስቀል ስለመስከረም 1968 ዓ.ም. ስለተጠራው የሠራተኛው የሥራ ማቆም ድማ፣ ስለሚጠየቁት ጥያቄዎች፣ ደርግ መስከረም 1968 ዓ.ም. ስለአወጀው “አስቸኳይ ጊዜ አዋጅና” አስከትሎም በተለይ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኞች ላይ ስለአደረገው እርና ፍጅት የሰጠው ቃል (ገጽ 15 እና 16 ዝርዝሩን ተመልከቱ) በእውነቱ አምኖበት ነው ወይስ ሰው ነውና ደርግ ይምረኛል በሚል ተስፋ ራሱን ለማዳን? ያሰኛል፡፡ 

የቀረቡት የጊዜያዊ ሕዝባዊ መንግሥትና የሞክራሲያ መብት መፈክሮች በደርግ ተሳኩ አልተሳኩ ማታገያነታቸውን እንዴት ሊቀበላቸው አልቻለም፡፡ እንደውም ኢሕአፓን ከዝብ ያስተቃቀፉት እነህ ሁለት መሠረታዊ መፈክሮች ናቸው፡፡ እንኳን ያኔ ዛሬም ምላሽ ያላገኙ አታጋይነታቸው ህያው ነው፡፡

 “. . . እኔ እንኳንስ ጊዜያዊ ሕዝባዊ መንግት እስኪቋቋም የሥራ ማቆም ድማውን ቀጥሉ ልንል የሠራተኛው ማበራት መሪዎች ሞክራሲያ መብቶች ካልታወጁ የሥራ ማቆም ድማ እናደርጋለን ማለታቸው ስህተት ነው የሚል ነበር። . . .” እነህን አታጋይ መፈክሮች ለሕዝብና ለሠራተኛው ማስተዋወቂያ አንዱ የሰላማዊ ትግል ዘዴ የሥራ ማቆም ድማ መሆኑን መቃኘት የሚከብድ አይደለም፡፡ ደርግ ጥያቄውን ይመልሳል ብሎ ተስፋ ለማድረግ ሳይሆን ትግሉ እንዲጎመራ ዘልቆ ብረተሰቡ ዘንድ እንዲሰር ሰላማዊ የማታገያ ዘዴ በመጠቀም ተግባራዊ ሲደረግ ባህሪው ነውና ደርግ ያራል፣ ይደበድባል፣ ይገድላል፡፡ ታጋይ እስርና ሞት ከፈራ ትግል መጀመርም የለበትም፡፡ እርና ግድያ ተፈርቶ ላማዊ ልፍ ካልተደረገ፣ የሥራ ማቆም ድማ ካልተጠራ፣ መፈክሮችና በራሪዎች በየግድግዳው ካልተለጠፉ፣ በሕዝባዊ መድረኮች ላይ ቅስቀሳ ካልተደረገ ትግል ምኑን ትግል ሆነ!

በኅዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም. እጁን በደም ያጨማለቀው ደርግ ሙሉውን ዓመት “በፍየል ወጠጤ” ሲያስካካ መክረሙ በቀጣይ ዓመትም 1968 ዓ.ም. ገና በመጀመያው ወር በአየር መንገድ ሠራተኞችና በሠራተኛው ማበራት ላይ ያደረገው እርና ግድያ እየቀጠለ ሙሉው 1968 ዓ.ም. ኢሕአፓ አንድም መሪያ ሳያነሳ አልነበረምን ልጆቹንና አባላቱን ሲገብር የኖረው? ብርሃነ መስቀል ቀጠል አድርጎ ስለደርግ ተራማጅነት እንዲህ ሲል ቃሉን ይሰጣል (ገጽ 16)

  ‹‹. . . በዚሁ ወቅት በአየር መንገድ ሠራተኞች ላይ በጥታ ኃይሎች የተከፈተው ተኩስና ከዚያም ተከታትሎ የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መንግሥት በልዩ ልዩ ምክንያት በተለይም በተጋነነ መረጃ ተሳስቶ ያወጣው ቢመስለኝም ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ፀረ ሞክራሲያዊ እንዲያውም ስታዊ ዝንባሌ ባላቸው ኃይሎች ተፅዕኖ ር የወደቀ መስሎኝ ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ እኔም እንደተቀሩት የፓርቲ መሪዎችና የፓርቲ አባላት በመንግቱ ተራማጅነት ተስፋ ማጣት አድሮብኝ እንደነበር ልሸሽግ አልችልም፡፡ ስለሆነም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በነበረበት ወቅት ይታየኝ የነበረው ዋናው አብዮታዊ የትግል ዘዴ የትጥቅ ትግል ነበር፡፡ ደግነቱ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግት በኋላ የወሰደው ተራማጅ ርምጃ ይህ ስሜት ተጨባጭ የፖሊሲ ርምጃዎችን ከማቅረቤ በፊት ሊያስለውጡኝ ችሏል፡፡ . . .›› ይለናል የኢሕአፓው መራች ብርሃነ መስቀል ረዳ፡፡

ይህንን ቃል ብርሃነ መስቀል የሰጠው በሰኔ ወር 1971 ዓ.ም. ሲሆን እሱ በሸሸበት መር ጨምሮ በመላው ገሪቷ ደርግ ያደረሰውን ልቂትና ሰቆቃ ሰምቷል፣ ተመልክቷል፡፡ በዚህ ወቅት ደርግ ኢሕአፓን ብቻ ሳይሆን አጠገቡ የከበቡትንም መኢሶን፣ ወዝ ሊግ፣ ኢጭአት ሳይቀሩ የበላና አንድ አምባገነን ፈላጭ ቆራጭ ፋስታዊ አገዛዝ ይበልጥ የተንሰራፋበት ወቅት መሆኑን እያወቀ ምን ያህል ነፍሱን ለማዳን ደርግን መሸንገሉ እጅጉን አሳዛኝ ነበር፡፡ ክብርና ስሙን እንደያዘ ቢሰዋ ምናለ ያሰኛል፡፡

ውን የደርግ ተራማጅነትና አብዮት ደርግ ከግ በላይ ገዝፎ በአንድ ምሽት ዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም. 54 የቀድሞ የአፄይለ ሥላሴን ባለሥልጣናት፣ ከደርጉ ሊቀመንበር ጄራል አማን አንዶምና ሌሎች አምስት ተራማጅ ወገኖች ጋር ደባልቆ የረሸነ ዕለት ይበልጥ አክትሞለታል፡፡ ደርግ ማንነቱን ያሳየበት ዕለት ነበር፡፡ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም በዋዜማው የሰጠው የጉድጓድ ቁፋሮ ዝግጅት ምን ያህል በደርጉ ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍን በበላይነት እንደያዘ አመላካች ነበር፡፡ ‹‹. . . እነዚህ ርምጃዎች ከዚያ በፊት ያልነበረኝን ያህል በጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ ተራማጅነት ከፍተኛ ተስፋ አደረብኝ፡፡ . . .››  (ገጽ 17) የሚለን ብርሃነ የእስረኞች መፈታትን እደ አብነት ከሚጠቅሳቸው ውስጥ ናቸው፡፡ ደርግ ገና ከሥልጣን ጅምሩ ማር፣ መፍታት ዋናው ተግባሩ ነው የቀረው ቢኖር “የእርና ግድያ ሚስትር” አለማቋቋሙ ብቻ ነው፡፡ ድሜ ለመኢሶን ባንዳ ምሁሮች ደርግ የኢሕአፓን ሕዝባዊ ቅላ በግልባጩ በመለፈፍ ለፕሮፓጋንዳ የሚጠቀም ብሔርተኛ አይደለምን? ስለባንዲራና ገር እየለፈፈ አይደል እንዴ ትውልድ የቀበረው? እርጉዝ አስገድሎ ንፁኃን ሠራተኞችን በአደባባይ አስረሽኖ የሕዝብ ቁጣ ሲያይልና ለአጎ ሲል ግርማ ከበደን ቢረሽን “ደርግ ተራማጅ ሆነ” ልንል አግባብነት አለውን? ይህ ነው እንግዲህ አምባሳደር ታደለች መመልከት የሚገባቸው፡፡ በወጣትነት ድሜያቸው በአፍላ ትግሉ ወቅት ሲዊዘርላንድ ከዚያም መርሐ ቤቴ ቢሆኑም የገራችን ልቂትና የደርግ ፍጅት በንፁኃን አርሶ አደሮች ላይ ሳይቀር ክምር እህልና ቤታቸውን ማጋየት እንደነበር በገጽ 330 ሲገልጹት እንዲህ ብለውናል፡፡

‹‹እጅግ አሳዛኝ የነበረው ጉዳይ በጎተራ የተሞላ እህል ሲያሻቸው በእሳት አለዚያም ቁልቁል በገደሉ በማፍሰስ፣ ከብቶችን በማረድና በመግደል ካልሆነም በመንዳት፣ ዝቡ እንዲማረር መደረጉ ነው፡፡

‹‹ከአንድ ከባድ አሰሳ በኋላ ደህና የተደራጀ የገበሬ ቤት እየመረጡ ገብተው ያለውን በማደፋፋት ጎጆዎችን ያቃጥላሉ፡፡ የዚህ የጭካኔ ዓላማ ‹‹ገበሬው በንብረቱና በጎታው ከመጡበት የተሸሸጉትን አማፂዎች አሳልፎ ይሰጣል›› በሚል ሌት እንደሆነ ይታሰባል፡፡ ይህን ተግባር የሚፈጽሙት ግለሰቦች ግን ከዚያም ያለፈ አረመኔያዊ ባህርያቸውን፣ የሰውን ስቃይ በማየት የመርካት ጥማቸውን የሚወጡ ለመሆናቸው በይኔ ያየሁት ድርጊት ምስክር ነው፤›› በሚል የትንቷ ወጣት ታደለች ስታስነብበን ደርግ ሰጥ ለጥ አድርጎ ለመግዛት ፍጅት ዋናው መመያው እንደነበር ያሳየናል::

የግንባር ጥሪ

ሚያዝያ 12 ቀን 1968 ዓ.ም. በደርግ ስለታወጀው የብሔራዊ ሞክራሲያዊ አብዮት ፕሮግራምና በመንግሥቱ ኃይለ ማርያም የተደረገው የግንባር ማቋም ጥሪ ግንባሩ ተግባራዊ ይሆን ዘንድ በኢሕአፓ በኩል እንዲሟሉ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን ብርሃመስቀል ሲወነጅል፣ ‹‹ . . . ክሊኩ ስምምነት ላይ የተደረሰበትን ውሳኔ ትርጉም ለማሳሳት ሥራዬ ብሎ መንግሥት ሊቀበላቸው የማይችላቸው ጥያቄዎችን መደርደር ጀመረ፡፡ . . .›› ይለናል፡፡

መቼም ኢሕአፓ በወቅቱ በእያንዳንዱ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማበረሰባዊ ጉዳዮች ላይ ጨምሮ በተከሰቱ ሁኔታዎች በሞክራሲያ ዕትሙ ያልዳሰሰው ጉዳይ አልነበረም፡፡ እነህ የሞክራሲያ ዕትሞች “የክሊኩ” ናቸው ካልተባሉ በቀር ዛሬም አሉ፤ ‹‹የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ በብረት ግንባር ላይ ያለው አቋም››  ሞክራሲያ ልዩ ዕትም ቁጥር ሦስት ግንቦት ወር 1968 ዓ.ም. (ሙሉውን ለማንበብ http://yatewlid.com/images/PDF/Democracia/Demo_01/Demo_Vol_1_LeyuEtim_No_03_Hibret.pdf) ባወጣው ዕትሙ፡-

 ‹‹. . . ወታደራዊው መንግሥት ሚያዝያ 12 ቀን 1968 ዓ.ም. ለአብዮታዊ ግንባር መቋቋም ያቀረበውን ጥሪ በመሠረተ ሳቡ የምንቀበለው ለዚህ ነው፡፡ . . .›› በሚል አቋሙን በመግለጽ ካስቀመጠ በኋላ ስለግንባሩ ከመንግሥት ጋር ውይይት ለመጀመር በቅድሚያ በግዴታ መሟላት አለባቸው በሚል የተዘረዘሩት ነጥቦች እንደሚከተለው አስቀምጧል፡-

‹‹ሀ. ሞክራሲያዊ መብቶች የረ ፊውዳል፣ የረ ኢምፔሪያሊስት፣ ረ ቢሮክራሲያዊ ካፒታሊስት አብዮት ደጋፊ ለሆኑት መደቦች (ላብ አደር፣ አርሶ አደር፣ ንዑስ ከበርቴ) እነዚህን ለሚወክሉ ቡድኖችና እንቅስቃሴዎች ሁሉ ያለገደብ እንዲታወጅ:: አብሮም ሞክራሲያዊ መብቶች ለመገደብ ተብለው የወጡት ግፈኛ ደንቦች ሕጎችና አዋጆች ሁሉ እንዲሻሩ፡፡

ለ. በኤርትራ ላይ የሚካሄደው ማናቸውም የክተት ዝግጅት በፍጥነት እንዲቆምና እንዲሻር፣ ሌሎች ጭቁን ብሔሮች ላይ የሚደረገው ዘመቻ እንዲቆም፡፡

ሐ. የወታደራዊው መንግሥት በሰፊው ሕዝብ ላይ የሚያካሂዳቸው ጭፍጨፋዎች ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመሩና ይፋነታቸው እየተባባሰ እንደሄደ ሰሞኑን በኪነት ሠራተኞችና በሜይ ዴይ ተሠላፊዎች የተወሰዱት የግፍ ርምጃዎች እንኳን በቂ ማስረጃዎች ናቸው፡፡ በአዋሽ ሸለቆ የእርሻ ሠራተኞች መሪዎች ላይ አስበ ተፈሪ ውስጥ የተደረገው ፍጅት ሳይበቃ አሁንም አርሶ አደሮችና ላብ አደሮች በየቦታው ይረሸናሉ፡፡ ያለፍርድ የሚገደሉት እስረኞች በተለይም ኤርትራውያን ቁጥር እጅግ ትልቅ ነው፡፡ እነዚህና እነዚህን መሰል በፊው ሕዝብ ላይ የሚካሄዱ የጭፍጨፋ ርምጃዎች ያለአንዳች መወላወል ባስቸኳይ እንዲቆሙ፡፡

መ. የታሩ አብዮታውያንና ሞክራሲያውያን በሙሉ በነፃ እንዲለቀቁ መንግቱ በተራማጆች ላይ የሚያደርገው ማሳደድና መከታተል በፍጥነት እንዲቆም፣ ይህም ከላብ አደሮች ከመምህራን ከተማሪዎች ከዘማቾች ሌላ የገበሬ ማበራት መሪዎችና አባላትን በየትኛውም የብሔር እንቅስቃሴ የታሩ ታጋዮችንና በታጋይነታቸው ምክንያት የታሩ ወታደሮችንና ፖሊሶችን የግዴታ ማጠቃለል ይኖርበታል፡፡

ሠ. መንግሥቱ በነዚህ ነጥቦች ላይ መስማማቱና በሥራም ላይ ማዋሉ በሬዮ በጋዜጦችና በሌሎች የመገናኛ ዘዴዎች በይፋ እንዲገለጽ፡፡ ከመንግሥቱ ጋር ለውይይቱ ከመቅረባችን በፊት እነዚህ አምስት ነጥቦች አንዳቸውም ሳይጓደሉና ሳይጣመሙ በሙሉ ግዴታ መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ . . .›› በማለት ነበር ሞክራሲያ የፓርቲውን ግልጽ አቋም ያስነበበችው፡፡

ውን ይህን “የክሊኩ” አቋም ብሎ መፈረጅ አባላቱንም ሆነ የሕዝቡን ትግል አለማገናዘብ ነው፡፡ እንደ መኢሶን ምንም ጥያቄ ሳናቀርብ ከደርግ እንተቃቀፍ ካልተባለ በቀር ይህ የወቅቱ የኢሕአፓ አቋም ልዩነት ፈጣሪ ይሆናልን? ውን ብርሃነ መስቀል በዚህ የእር ቤት ቃለ ምርመራ እንደምንም የሚለውን ብሎ ሕይወቱን ሊያተርፍ ፈልጓል ወይም እጅጉን ፖለቲካው ተምታቶበታል ያሰኛል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ መስጠት ቢቻልም አንባያን ለግንዛቤ የብርሃነ መስቀልን ቃለ ምርመራና ከላይ የጠቀስኩትን የሞክራሲያ ዕትም ማንበቡ እንደሚረዳ በመጠቆም ወደ ሌላው ጉዳይ ልገስግ፡፡

ኢሕአፓ በዚህ የግንባር ጥሪ ዕትሙ የተቃወመውንና የማይቀበለውንም በግልጽ አስቀምጦታል እንዲህ ይነበባል ‹‹ይህን ጥሪ በመሠረተ ሳቡ ብንቀበለውም የወጣውን ፕሮግራም እንደ ብረት ግንባር ፕሮግራም አድርገን አንቀበለውም:: ከፕሮግራሙ ጋር አብሮ የወጣውን የአደራጅ ጽሕፈት ቤት ልንቀበል አንችልም፡፡ ጽሕፈት ቤቱ በመንግሥት ቀጥተኛ ቁጥጥር ሥር የሚገኝ ከመሆኑም ሌላ በአመራረጡ ሞክራሲያዊ ያልሆነ፣ ስለዚህም አራሩ አብዮታዊና ሞክራሲያዊ ቅድ የማይኖረው ይዘቱም የተለያዩትን ተራማጅ ክፍሎች በውከላ መልክ ያልያዘና ግፋ ቢል የአንድ ጠባብ ቡድንን ድምና ጥቅም ብቻ የሚያስተጋባ በመሆኑ መቋቋሙን አጥብቀን እንቃወማለን፡፡ . . .›› በሚል በሕዝብ ድርጅት ጉዳይ ጽሕፈት ቤት አማካይነት በወቅቱ 900 ብር የወር ደመወዝ የሚያስከፍለውን (የመኢሶኑ አቶ አንዳርጋቸው አሰግድ በነገራችን ላይ ከደረጀ ኃይሌ ጋር ያደረጉት ውይይት) የመኢሶንን ዕቅድና አካሄድ አጋልጧል፡፡

 ይቀጥላል

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_imgspot_img
- Advertisment -

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

Related Articles