ሪፖርተር በዕለተ እሑድ ጥቅምት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. ባወጣው ዕትም፣ ‹‹የአውሮፓ ኅብረት የፌዴራልና የትግራይ ክልል መንግሥታትን ለማግባባት ጥረት መጀመሩ ተሰማ›› በሚለው ዜና ውስጥ የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ግንኙነትና ደኅንነት ፖሊሲ ምክትል ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ቦሬሌ የተመራ ልዑካን ቡድን ወደ ትግራይ ክልል ሄዶ መነጋገሩን የገለጽን ቢሆንም፣ ‹‹የአውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ ቢሮ ልዑካን ቡድኑ ወደ ትግራይ ሄዷል›› የሚለው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን በትዊተር ገጹ አስታውቋል፡፡ በዚሁ ዘገባ ላይ መረጃ የሰጡት የሕወሓት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ጌታቸው ረዳ ከአውሮፓ ኅብረት ልዑካን አባላት ጋር መነጋገራቸውን ጠቅሰው፣ ልዑኩ በትግራይ ክልል ጉብኝት አካሂዷል የሚለው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ልዑኩ ወደ ትግራይ ክልል በመሄድ ተነጋግሯል በሚል በዘገባው የተጠቀሰው፣ መረጃ በማሰባሰብ ወቅት የተፈጸመ ስህተት መሆኑን ከይቅርታ ጋር እየገለጽን መረጃው ከላይ በእንደተጠቀሰው እንዲታረም እንጠይቃለን፡፡
የዝግጅት ክፍሉ