Thursday, December 7, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየሚኒስትሮች ምክር ቤት በትግራይ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በትግራይ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ

ቀን:

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ረቡዕ ጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ፣ በትግራይ ለክልላዊ መንግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለስድስት ወራት በትግራይ ክልል ላይ ታውጆ እንደሚቆይ የገለጸ ሲሆን፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማስፈጸም የሚቋቋመው ግብረ ኃይል በሚያወጣው መመርያ አዋጁ የሚፈጸምበት አካባቢ ሊሰፋ ይችላል፡፡

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማስፈጸም ግብረ ኃይል የተቋቋመ ሲሆን፣ ግብረ ኃይሉን የሚመሩት የአገር መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም እንደሚሆኑና የሌሎች አስፈላጊ ተቋማት አመራሮችም በአባልነት ይሳተፉበታል፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ግብረ ኃይል ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚሆን፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማውጣት ምክንያት የሆነው የትግራይ ክልል ሕገወጥነትና ጠብ አጫሪነት እንቅስቃሴዎች፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የጣለ በመሆኑ ነው ሲል የጠቅላ የሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...