Thursday, December 7, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበትግራይ ክልል ላይ የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በፓርላማ ጸደቀ

በትግራይ ክልል ላይ የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በፓርላማ ጸደቀ

ቀን:

–  ጄነራል አደም መሐመድ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ግብረኃይል ይመራሉ

የሚንስትሮች ምክር ቤት በትላንትናው እለት በትግራይ ክልል ላይ ተግባራዊ እንዲደረግ ያወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የህዝብ ተወካዮች ምር ቤት አጸደቀ፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥቅምት 26 ቀን 2013 ዓም ባካሄደው ስብሰባ፣ በትግራይ ክልል ላይ ለስድስት ወራት እንዲጣል የተወሰነውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጽድቋል፡፡
አስቸኳይ አዋጁን የሚያስፈጽም ግብረኃይል የሚቋቋም ሲሆን ተጠሪነቱም ለጠቅላይ ሚንስትሩ እንደሚሆን በአዋጁ ተደንግጓል፡፡
ግብረኃይሉ በጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል አደም መሐመድ የሚመራ መሆኑም ታውቋል፡፡   
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.ም ባደረገው  ልዩ ስብሰባ፥ በትግራይ ብሔራዊ ክልል ውስጥ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን እንዲሁም የሕዝብን ሰላምና ፀጥታ አደጋ ላይ የሚጥሉ በተለይም የሀገርን ሉዐላዊነት የሚገዳደሩ ጉዳዮችን በሚመለከት፣ የፌደራል መንግሥት በሕገ መንግሥቱ የተሰጠውን ሥልጣንና ኃላፊነት በክልሉ እንዲወጣ እና ሀገሪቷን የጦር አውድማ የሚያደርጉ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔዎችን ጭምር በመጣስ በርካታ ሕገ ወጥ ተግባራት እየተፈፀሙ በመሆኑ፤ ይህን ሁኔታ በመደበኛው የሕግ ማስከበር ሥርዓት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የማይቻልበት ደረጃ ላይ መደረሱን በመረዳት፤ በሕገ መንግሥቱ በተደነገገው መሠረት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመጠበቅ ልዩ እርምጃዎችን መውሰድ የሚያስችል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 93/1/ሀ ድንጋጌ መሰረት አውጇል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...