Saturday, January 18, 2025
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየህዳሴ ግድብ ድርድር በግብፅ እንቢተኝነት ያለ ውጤት መቋረጡ ተገለጸ

የህዳሴ ግድብ ድርድር በግብፅ እንቢተኝነት ያለ ውጤት መቋረጡ ተገለጸ

ቀን:

spot_img

በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ ሲካሄድ የነበረው ድርድር በግብፅ እንቢተኝነት ያለ ውጤት መቋረጡን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታወቀ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዓርብ ጥቅምት 27 ቀን 2013 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ፣ ኢትዮጵያና ሱዳን ያቀረቡትን አዲስ የድርድር መንገድ ግብፅ ባለመቀበሏ ድርድሩ መቋረጡን አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያና ሱዳን ያቀረቡት አዲስሳብ በህዳሴ ግድቡ ላይ ያለውን አለመግባባት ለመፍታት የአፍሪካ አገሮች ሚና እንዲጨምር የጠየቁ መሆኑን የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ ይህ ሐሳብም ለአፍሪካ ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ በሚለው የአፍሪካብረት መርህ መሠረት መቅረቡን ገልጸዋል።

የህዳሴ ግድቡን አስመልክቶ በቀጣይ ፍሬያማ ውይይት እንዲካሄድ ከሁሉም የአፍሪካ አገሮች ሁለት ሁለት ባለሙያዎችን ባካተተ መንገድ ውይይት እንዲደረግ የሚጠይቅ ነው። ሱዳን በኢትዮጵያሳብ የተስማማች ቢሆንም፣ ግብፅ ግንሳቡን ውድቅ እንዳደረገች አምባሳደር ዲና ተናግረዋል።

የሱዳን መንግሥት  ባወጣው መግለጫም የአፍሪካ አገሮች ባለሙያዎችገዛ የሚያደርጉበትን የድርድር መድረክ ለመፍጠር የቀረበውን አዲስ ሐሳብ ግብፅ ውድቅ በማድረጓ የሦስተዮሽ ድርድሩ መቋረጡን አስታውቋል።

በመሆኑም ድርድሩ የደረሰበትን ደረጃ አስመልክቶ ሦስቱም አገሮች ለአፍሪካብረት የወቅቱ ሊቀመንበር ለሆኑት የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎዛ ሪፖርት በማቅረብ ቀጣይ አቅጣጫ እንዲሰጡበት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው...

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው...

ባንኮች እየፈጸሙት ያለው አቅርቦትንና ፍላጎትን ያላገናዘበ የውጭ ምንዛሪ ግዥ

የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ ዋጋ እንዲገበይ የወጣው ሕግ ተግባራዊ...

አሳረኛው ኑሮ!

የዛሬው ጉዞ ከቦሌ ወደ ፒያሳ ይሆን ዘንድ ግድ ሆኗል፡፡...